ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ስለሚኖረው ውጤት


ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ስለሚኖረው ውጤት

አንቀጽ ፵፱ መከባበር መተጋገዝና መደጋገፍ

 

፩. ባልና ሚስት እርስ በርሳቸው መከባበር፣ መተጋገዝና መደጋገፍ አለባቸው፡፡

፪. በጋብቻው ውል ውስጥ ይህንን የሚቃረን ስምምነት ማድረግ አይችሉም፡፡

 

አንቀጽ ፶ የቤተሰብ የጋራ አመራር (፩) ጠቅላላ

 

፩. በቤተሰብ አመራር ረገድ ባልና ሚስት እኩል መብት አላቸው፡፡

፪. ባልና ሚስቱ በማናቸውም ረገድ የቤተሰቡን ደህንነትና ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ለልጆቻቸው በመልካም ሥነምግባር እንዲታነፁ፣ ተገቢ ትምህርት እንዲቀስሙና ኃላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ሆነው እንዲያድጉ ለማድረግ መተባበር አለባቸው፡፡

 

አንቀጽ ፶፩ (፪) ከተጋቢዎቹ አንዱ ቤተሰቡን ለመምራት ስላለመቻሉ

 

፩. ከባልና ሚስት አንደኛው ችሎታ ያጣ፣ የጠፋ ወይም ቤተሰቡን ጥሎ የሔደ ወይም ከመኖሪያ ሥፍራው በመራቁም ሆነ በማናቸውም ሌላ ምክንያት ፈቃዱን ለመስጠት በማይችልበት ሁኔታ በሚገኝበት ጊዜ፣ በአንቀጽ ፶ የተመለከተውን የቤተሰብ አመራር አንደኛው ተጋቢ ብቻውን ይፈጽማል፡፡

፪. ባልና ሚስት በጋብቻ ውላቸው ውስጥ ይህንን የሚቃረን ስምምነት ማድረግ አይችሉም፡፡

 

አንቀጽ ፶፪ ከጋብቻ በፊት ከሌላ ስለተወለዱ ልጆች

 

፩. ከባልና ከሚስቱ አንዱ ከጋብቻው በፊት ከሌላ የወለዳቸውን ልጆች መልካም አስተዳደግ በሚመለከት በራሱ አሳብና መሪነት የፈቀደውን ውሳኔ ለማድረግ ሙሉ መብት ይኖረዋል፡፡

፪. ይህንን የሚቃረን ማናቸውም ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡

 

አንቀጽ ፶፫ አብሮ መኖር

 

፩. ባልና ሚስት አብረው እንዲኖሩ ይገደዳሉ፡፡

፪. ለጤናቸው አደገኛ ካልሆነ በስተቀር ባልና ሚስት ከጋብቻ የሚጠበቀውን መደበኛውን የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸም አለባቸው፡፡

፫. ይህንን የሚቃረን ማናቸውም ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡

 

አንቀጽ ፶፬ የመኖሪያ ሥፍራን ስለመወሰን

 

ባልና ሚስት የሚኖሩበትን ሥፍራ በጋራ ይወስናሉ፡፡

 

አንቀጽ ፶፭ በስምምነት ተለያይቶ ስለመኖር

 

፩. በዚህ ሕግ በአንቀጽ ፶፫ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተመለከተው ቢኖርም ባልና ሚስቱ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተለያይተው ለመኖር መስማማት ይችላሉ፡፡

፪. ስለዚህ ጉዳይ የተደነገገውን ስምምነት መለወጡ የማይገባ ካልሆነ በስተቀር ከሁለቱ ተጋቢዎች አንደኛው አስቦ ሊሰርዘው ይችላል፡፡

 

አንቀጽ ፶፮ የመተማመን ግዴታ

 

ባል ለሚስቱ፣ ሚስት ለባልዋ ታማኝ የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡

 

2 thoughts on “ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ስለሚኖረው ውጤት”

Leave a Reply

Please log in using one of these methods to post your comment:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.