አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (ከፊል የህግ አውጭነት ስልጣን)


አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (ከፊል የህግ አውጭነት ስልጣን)

አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (ከፊል የህግ አውጭነት ስልጣን) ህግ የማውጣት ስልጣን የህግ አውጭው ነው እንላለን እንጂ በተግባር ግን ህግ የሚወጣው በተወካዮች ም/ቤት ብቻ አይደለም፡፡ ይህ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በየትም አገር ያለ እውነታ ነው፡፡ በየጊዜው እያደገ ከሚመጣው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ውስብስብነት የተነሳ ህግ አውጭው ከልሂቅ እስከ ደቂቃ ለእያንዳንዱ ችግር መፍትሄ የሚሆን ህግ በአይነትና በጥራት ማቅረብ ይሳነዋል፡፡ አንድ የህግ ረቂቅ ውጤት ያለው ህግ ለመሆን ከሚፈጀው ረጅም ጊዜና ዝርዝር የስነ-ስርዓት ቅድመ ሁኔታ አንፃር ህግ አውጭው በየጊዜው ለሚፈጠር ችግር በየጊዜው አዋጅ እያወጣ መፍትሄ ለመስጠት በቂ ጊዜ የለውም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ አንዳንድ ዝርዝር ጉዳዮች ልዩ እውቀትን የሚጠይቁ እንደመሆኑ ውስን የሆነው የህግ አውጭው እውቀት የህግ ማውጣት ስልጣን በተግባር በከፊል የተገደበ እንዲሆንና ሌላ አማራጭ እንዲፈልግ ያስገድደዋል፡፡ ይህ አማራጭ በውክልና ስልጣን የሚወጣ ህግ (delegated legislation) ይባላል፡፡ ተግባራዊ ከሆኑት አስፈላጊ ምክንያቶች የተነሳ ህግ አውጭው ከህዝብ የተሰጠውን ህግ የማውጣት ስልጣን በከፊል ቆርሶ ለስራ አስፈፃሚውና ለአስተዳደር መ/ቤቶች ይሰጣል፡፡ በዚሁ መሰረት የሚኒስትሮች ም/ቤት በአዋጅ በሚሰጠው ስልጣን መሰረት ደንብ ይደነግጋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የአስተዳደር መ/ቤቶች በውክልና የህግ አውጭነት ስልጣናቸው መመሪያቸውን ያወጣሉ፡፡ ዋነኛ ስልጣኑ ህግ ማስፈፀም የሆነው ስራ አስፈፃሚው የመንግስት አካል በደንብና በመመሪያ የህግ አውጭነት ስልጣን ደርቦ መያዙ ከስልጣን ክፍፍል መርህ ጋር የሚጣረስ ቢሆንም የህግ አውጭው ጊዜና የእውቀት ውስንነት እንዲሁም የመንግስት አስተዳደርን ብቁና ውጤታማ ከማድረግ አንፃር በተግባር የግድ የሚል እውነታ ሆኗል፡፡ ሆኖም አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት ስልጣን በዚህ እውነታ ብቻ አይቋጭም፡፡ ያልተገደበ ስልጣን መኖር ለዜጐች መብትና ነፃነት መቼም ቢሆን አደገኛነቱ ጥርጥር የለውም፡፡ የአስፈላጊነቱ እውነታ ከዜጐች መብትና ነፃነት ጋር እንዲጣጣም ወይም እንዲታረቅ ተግባራዊ የስልጣን መቆጣጠሪያ መሳሪያ እንዲኖር ግድ ይላል፡፡ እንደ የአስተዳደር ህግ ምሁሩ ዌድ አገላለጽ ‘ከዜጐቹ ላይ ነፃነት ሲቀነስ ፍትህ መጨመር አለበት፡፡’ የመንግስት ስልጣኑ ሲለጠጥ በዛው ልክ የዜጐች መብትና ነፃነት እየተሸበሸበ (እያነሰ) ይመጣል፡፡ ስልጣን ሲጨምር ፍትህም አብሮ መጨመር አለበት፡፡ ከዚህ አንጻረ ስራ አስፈፃሚው ተጨማሪ የህግ አውጭነት ስልጣን ሲሰጠው ስልጣኑን በአግባቡና ፍትሀዊ በሆነ መንገድ እንደሚገለገል የሚያረጋግጥና የሚቆጣጠር የአስተዳደራዊ ድንጋጌ አወጣጥ ስነ ስርዓት ያስፈልጋል፡፡ በሚኒስትሮች ም/ቤት እና በአስተዳደር መ/ቤቶች የሚወጡ አስተዳደራዊ ድንጋጌዎች ከሌሎች የአስተዳደር ተግባራት የሚለያቸው መሰረታዊ ባህሪያት አላቸው፡፡ በዋናነት የሚከተሉትን ነጥቦች ይጠቀሳሉ፡፡ በውክልና የሚወጣ ህግ የተፈጻሚነቱ ወሰን በአንድ ግለሰብ ወይም ድርጅት ላይ ሳይሆን በህብረተሰቡ በአጠቃላይ ወይም በተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል ላይ ነው፡፡ ትኩረቱ በግለሰብና በመንግስት መካከል የሚነሱ የግል ክርክሮችን መፍታት ሳይሆን የህዝብ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚረዱ ፖሊሲዎችን ማስፈፀም ነው፡፡ ወደ ኋላ ተመልሶ ተመልሶ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡ ውጤቱና ተፈጻሚነቱ አስተዳደራዊ ድንጋጌው ከወጣ በኋላ ወደ ፊት ለሚከሰቱ ነገሮች ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ ውጤት ይኖረዋል፡፡ በይፋ ታትሞ ለህዝብ መሰራጨት ይኖርበታል፡፡ ከህትመት በፊት ጉዳዩ የሚመለከታቸውን አካላት የማማከር ቅድመ ሁኔታ ሊሟላ ይገባል፡፡ በአስተዳደሩ የሚወጡ ድንጋጌዎች አብዛኛውን ጊዜ በተግባር እንዲፈፀሙ በተጨማሪ የአስተዳደር ድርጊት /ውሳኔ፣ እርምጃ፣ ቅጣት/ መታገዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ስለዚህም በራሳቸው ምሉዕ አይደሉም፡፡

From the day Prime Minister Abiy Ahmed came to power, the slogan, politics or patriotism that Ethiopia has been saying will not fall apart?


From the day Prime Minister Abiy Ahmed came to power, the slogan, politics or patriotism that Ethiopia has been saying will not fall apart? Who said Ethiopia will be destroyed or Ethiopia will be destroyed? Why did Prime Minister Abiy Ahmed, with his tribute to Isaias Afewerki, repeatedly use slogans unless he himself had the…

A Rebel leader and one of the most sought after men in the country.Now he sits in a mountain village with his satellite phone and plans how the war will continue for the rebels.


a rebel leader and one of the most sought after men in the country. Now he sits in a mountain village with his satellite phone and plans how the war will continue for the rebels. The war in Tigray County began last November when the armed wing of the TPLF, the Tigray People’s Liberation Front,…

Hundreds of thousands of Tigray mothers and children are dying of starvation in Ethiopia. This is an unprecedented massacre in all parts of the country at the behest of dictator Abiy Ahmed.This is how my country became! too bad.! በሃገራችን ኢትዮጵያ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ እናቶችና ህፃናት በአስከፊ ሰው ሰራሽ ረሀብ እየረገፉ/እየሞቱ ነው፡፡ ይህ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እየተፈፀመ ያለው አስከፊ ሰቆቃና ረሃብ ግፍ በ አንባገነኑ አብይ አህመድ መራሹ አንባገነን መሪ ፍላጎት የተፈጸመ የዘርማጥፋት ዘመቻ ነው።ሀገሬ እንዲህ ሆነች! ያሳዝናል።!


Hundreds of thousands of Tigray mothers and children are dying of starvation in Ethiopia.  This is an unprecedented massacre in all parts of the country at the behest of dictator Abiy Ahmed.This is how my country became!  too bad.!   በሃገራችን ኢትዮጵያ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ እናቶችና ህፃናት በአስከፊ ሰው ሰራሽ ረሀብ እየረገፉ/እየሞቱ ነው፡፡ ይህ በሁሉም…