በሕግ እንዲደረግ ያልተፈቀደ፤ የሕግ ክልከላ ያለበት ውል።
አንድ ውል ሕገወጥ ውል ነው የሚባለው ተዋዋዮቹ የተዋዋሉበት መሠረታዊ ጉዳይ ዓላማ በመሠረታዊና ሞራላዊ ይዘቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት በማድረግ መብትና ግዴታ እንዲፈጥሩበት በሕግ ያልተፈቀደ ወይም በሕግ ክልከላ የተደረገበት ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ ለምሳሌ በሕገ መንግሥቱም ሆነ በአገሪቱ የወንጀል ሕግ እንደዚሁም በዓለም አቀፍ የወንጀል ሕግ ማንኛውንም ሰብዓዊ ፍጡር በግዴታ አገልጋይነት መያዝ ወይም በሰው መነገድ የተከለከለ በመሆኑ ሰውን በግዴታ አገልጋይነት ለመያዝ ወይም በሰው ለመነገድ የተደረገ ውል በመሠረታዊ ባህሪውና ሞራላዊ ይዘቱ ሕገወጥ ውል /unlawfull contract/ ነው፡፡ አንድ ውል የተመሠረተበት መሠረታዊ ጉዳይ “object of contract” በሕግ ክልከላ የተደረገበት በሆነ ጊዜ ውሉ በሕግ ፊት የሌለና ምንም አይነት ሕጋዊ ውጤት የማያስከትል /void contract/ ነው፡፡ አንድ ውል በማናቸውም ሰው ወይም አካል ፈቃድና ስምምነት ሕጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ የማይቻልና በማናቸውም መንገድ ለማስተካከልና ሕጋዊ ውጤት እንዲያገኝ ለማድረግ የማይቻል በሆነ ጊዜ ውሉ ከጅምሩ በሕግ ፊት እንዳልተደረገና እንደሌለ “Null or void contract” እንደሚሆን በዘርፉ ከተደረጉ ጥናቶች ለመገንዘብ ይቻላል፡፡
ውል በጠቅላላ የውል ሕግና በልዩ ።
የውል ሕግ ድንጋጌዎች ወይም በሌሎች ህጎች የተደነገገውን መስፈርት የማያሟላና ጉድለት ያለበት ውል
ከባለሀብቱ በቂ የሆነ የውክልና ሥልጣን ሣይኖረው ወይም ንብረቱን ለመሸጥ የሚያስችል መብት በሌለው ሰው የተደረገ የሽያጭ ውል፣ ውሉ በሕግ የተደነገጉ አስገዳጅ መስፈርቶችን የማያሟላ ነው፡፡ የዚህ ጉድለት መኖሩ ቢረጋገጥ ውሉ ባለሀብትነትን በሽያጭ ለማስተላለፍ የተደነገጉትን አግባብነት ያላቸው ድንጋጌዎች የማያሟላ “Illegal or invalid contract” የሚያደርገው ጉድለት ነው፡፡ የውሉን ጉድለት በማቃናት ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ለማድረግ የሚቻልበት መንገድና ሁኔታ ሲኖር ውሉ ከጅምሩ እንዳልተደረገ የሚቆጠር (null or void contract) ሣይሆን ጉድለት ያለበትና ፈራሽ “voidable or invalid contract” ሊሆን የሚችል ውል ነው፡፡