
በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2089/2/ ድንጋጌ መሰረት ጥቅም የሌለው ግንኙነት መኖሩ ቢረጋገጥም የመኪና ባለሃብት ወይም ጠባቂ ጥፋት ማድረጋቸው ከተረጋገጠ በመኪናው በነጻ ተሳፍሮ ሲጓዝ ጉዳት ለደረሰበት ተሳፋሪ ተጠያቂነት አለባቸው፡፡ በድንጋጌው ስር “ጠባቂ” የሚለው ቃል የአማርኛው አቻ የእግሊዘኛ ቃሉ ‘’holder’’ በሚል የተቀመጠ ሲሆን ይህ ቃል በሕግ መዝገበ ቃላት ከተሰጠው ትርጉም አንዱ a person who possesses or uses property በሚል የተቀመጠ መሆኑን ታዋቂው የብላክስ ሎው መዝገበ ቃላት ያሳያል፡፡ ስለሆነም ጠባቂ የሚለው ቃል የሚመለከተው ለራሱ ጥቅም መኪናውን ይዞ የሚገኘውን ሰው ነው፡፡
