የስነስርዓት ጉድለት


የስነ ስርዓት

ጉድለት የአስተዳደር ህግ ከይዘት (ውሳኔ) ይልቅ በስነ-ስርዓት (የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት) ላይ የሚያተኩር የህግ ክፍል ስለመሆኑ ከዚህ በፊት ተገልጿል፡፡ የውሳኔ አሰጣጥ ፍትሐዊነት ሲረጋገጥ የአስተዳደር ፍትህ ይሰፍናል፡፡ ህግ አውጭው አንድ ድርጊት ከመፈጸሙ ወይም ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት መሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ወይም ስነ-ስርዓቶች በግልጽ ከደነገገ በስልጣኑ ተጠቅሞ እርምጃ የሚወስድ አካል መሟላታቸውን በቅድሚያ ማረጋገጥ ይጠበቅበታል፡፡ በህግ የተደነገገ የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ፍርድ ቤቶች ሆኑ ውሳኔ ሰጪዎች ሊከተሉት የሚገባ አስገዳጅ ደንብ ነው፡፡ ከዚህ በተቃራኒ የስነ-ስርዓት ጉድለት ያለበት ውሳኔ በህግ ፊት ዋጋ ወይም ውጤት ሊኖረው አይገባም፡፡ በእንግሊዝ፣ አሜሪካና የእነሱን የህግ ስርዓት በሚከተሉ አገራት የሚገኙ ፍ/ቤቶች በግልጽ ከሚደነገገው የስነ-ስርዓት ቅድመ ሁኔታ ውጭ የግለሰብን መብትና ጥቅም ሊነካ የሚችል ዳኝነታዊ ባህርይ ያለው አስተዳደራዊ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት በህግ ባይቀመጥም እንኳን ፍትሐዊ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት መርሆዎችን ተፈፃሚ ያደርጋሉ፡፡ ስለሆነም ስልጣን በሰጠው አዋጅ ላይ ባይጠቀስም በአስተዳደራዊ ውሳኔ መብቱ የሚነካ ወገን ከውሳኔው በፊት ራሱን የመከላከል ዕድል ሊሰጠው ይገባል፡፡ ውሳኔ ሰጪውም በተከራካሪዎች የቀረበውን ማስረጃና ህጉን መሰረት አድርጎ ያለ አድልዎ ገለልተኛ ሆኖ ፍትሐዊ ውሳኔ መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ የገንዘብ፣ በዝምድና አሊያም ሌላ ተገቢ ያልሆነ ነገር ግምት ውስጥ ገብቶ የተሰጠ ውሳኔ የተዛባና በህግ ፊት ዋጋ የሌለው ውሳኔ ነው፡፡

EFFECTS OF VIOLATIONS


EFFECTS OF VIOLATIONS OF ESSENTIAL CONDITIONS OF MARRIAGE  

Article 31. – Age 1) Without prejudice to Sub-Article (2) of Article 7 of this Code, marriage concluded by a man or a woman under the age of eighteen years shall dissolve on the application of any interested person or the public prosecutor. 2) It may no longer be applied for after the age required by law of marriage is satisfied.   Article 32. – Consanguinity of Affinity. The dissolution of marriage concluded in violation of impediments arising out of consanguinity or affinity shall be ordered on the application of any interested person or the public prosecutor. Article 33. – Bigamy 1) The dissolution of a bigamous marriage shall be ordered on the application if either of the spouses of bigamous marriage or the public prosecutor. 2) The dissolution mentioned on Sub-Article (1) of this Article may no longer be applied for where the former spouse of the bigamous marriage has died. Article 34 . – Dissolution of Marriage of a Judicially Interdicted person. 1) Where a judicially interdicted person has contracted marriage without prior authorization of the court, the dissolution of such marriage may be requested from the court by the judicially interdicted person himself or by his guardian. 2) The judicially interdicted person may no longer make an application for dissolution six months after the date of termination of his disability. 3) An application for dissolution by the guardian may no longer be made six months after the day on which the guardian came to know the existence of the marriage or in any case, after the disability of the interdicted person has ceased. Article 35. – Act of Violence 1) Whosoever has concluded marriage under the influence of violence may apply to the court to order the dissolution thereof. 2) Such an application may not be made six months after the cessation of such violence and, in any case, two years after the conclusion of the marriage. Article 36. – Error 1) Whosoever has concluded marriage due to fundamental error, may apply to the court to order the dissolution thereof. 2) Such an application may not be made six months after the discovery of such error, and , in any case, two years after the conclusion of the marriage. Article 37. – Period of Widowhood. The dissolution of marriage may not be ordered for the sole reason that the period of widowhood specified under Sub-Article (1) of Article 16 has not been observed. Article 38. – Incompetence of Officer of Civil Status. The dissolution of marriage may not be ordered solely on the ground of incompetence of the officer of civil status who celebrated the marriage. Article 39. – Non-Observance of Formalities. The dissolution of marriage may not be ordered on the sole ground that the formalities of celebration specified under Sub Articles (3) and (6) of Article 25 have not been observed.  

ለጠቅላይ ሚንስትር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ አካላት


ለጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ አካላትን ማቋቋሚያ ህጎች አዋጅ ቁጥር 257/1994 በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል። አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 257/1994” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል። መቋቋም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ከዚህ በኋላ (ምከር ቤቱ) እየተባለ የሚጠራ በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል። ምክር ቤቱ እንዳስፈላጊነቱ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ሊኖሩት ይችላል። የምክር ቤቱ አባላት ምክር ቤቱ የሚከተሉት ቋሚ አባላት ይኖሩታል፣
የምክር ቤቱ ተግባር ምክር ቤቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት የሚመለከቱ የውጭና የመከላከያ ፖሲዎች እንዲጣጣሙ በማድረግና በሚገባ ተግባራዊ መደረጋቸውን በመከ ታተል ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ያማክራል። የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ምክር ቤቱ፣ ሀ/ ለሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት የሥጋት ምንጭ የሆኑ ሁኔታዎችን በመገምገም ሊወሰዱ ስለሚገባቸው እርምጃዎች ሃሣብ ያቀርባል፤ ለ/ የሀገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት ለማስጠበቅ የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚመለከቱ የአፈጻጸም መመሪያዎች ያመነጫል፤ ሐ/ የሀገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት በሚነካ ማናቸውም ጉዳይ ላይ ይመከራል። ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 93 መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሲደነገግም የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ የሚወሰኑ ተግባሮችን ያከናውናል። የምክር ቤቱ ስብሰባዎች ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲጠራ በማናቸውም ጊዜ ሊሰበሰብ ይችላል። በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት አባላት ከተገኙ ምልአተ ጉባዔ ይኖራል። ምክር ቤቱ የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት መመሪያ ሊያወጣ ይችላል። የምክር ቤቱ ኮሚቴዎች በዚህ አዋጅ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ (2) መሠረት የሚቋቋሙ ኮሚቴዎች የሚኖሩዋቸው አባላትና ዝርዝር ተግባራቸው በምክር ቤቱ ይወሰናል።

የአስተዳደር መንግስት እና የአስተዳደር ህግ ውልደት


 የአስተዳደር መንግስት እና የአስተዳደር ህግ ውልደት

19ኛው ክፍለ ዘመን ገኖ የነበረው የነፃ ገበያ (laisse faire) ንድፈ ሀሳብ በዋነኛነት ውስን የመንግስት ጣልቃ ገብነትና ሰፊ የግለሶቦች ነፃነትን ያቀነቅናል፡፡ በዚሁ ንድፈ ሀሳብ መሰረት የመንግስት ሚና ህግና ስርዓት ከማስጠበቅና አገርን ከጠላት ወረራ ከመከላከል የዘለለ መሆን የለበትም፡፡ ምርጥ መንግስት ማለት በስሱ (በትንሹ) የሚገዛ መንግስት ማለት ነው፡፡ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን መምራት፣ መቆጣጠርና መግራት እንደ መንግስት ኃላፊነት አይቆጠርም፡፡ሆኖም ነፃ የሆነው የገበያና የመንግስት ስርዓት እግረ መንገዱን ይዞ የመጣቸው አሉታዊ ውጤቶች በዋነኛነት ያረፉት በደካማውና ደሀው የህብረተሰብ ክፍል ጫንቃ ላይ ነበር፡፡ በሀብታምና ደሀ መካከል የተፈጠረው የሀብት ድልድል ልዩነት በእጅጉ እየሰፋ በመምጣቱ ሀብታም የበለጠ ሲበለፅግ ደሃው ግን ይባስ እየቆረቆዘ መሄድ ጀመረ፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ መካከል የነበረው የመደራደር አቅም ልዩነት ታይቶ ለማይታወቅ የጉልበት ብዝበዛ ምክንያት ሆነ፡፡ እነዚህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠንቆች ለነፃ ገበያ ስርዓትና አስተሳሰብ ፈታኝ ሁኔታዎች ነበሩ፡፡ስለሆነም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠንቆች መፍትሔ መስጠት የመንግስት ግዴታና ኃላፊነት የመሆኑ እውነታ ቀስ በቀስ እየተገለጠ መጣ፡፡b በተለይም የሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ የተከሰቱት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የመንግስት ጣልቃ ገብነት አስፈላጊነትን ከመቼውም ጊዜ በላይ በገሃድ አስረግጠዋል፡፡ መንግስት ኃላፊነቱን መወጣት የሚችለው ደግሞ አወቃቀሩና አደረጃጀቱ ሲገፉት የሚፍረከረክ ዓይነት ‘ልል’ ወይም ውስን መንግስት መሆኑ ቀርቶ ጡንቻው የዳበረና ስልጣኑ የሰፋ ጠንካራ መንግስት ሆኖ ሲገኝ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠንቆች መፍትሔ መስጠት የመንግስት ግዴታ ነው ሲባል ሚናው ከተለመደው ስርዓትና ፀጥታ ማስከበር ባሻገር ሰፊና ውስብስብ አዎንታዊ ተግባራትን ወደ ማከናወን መሸጋገር እንደሆነ ልብ ይሏል፡፡በዚሁ መሰረት የመንግስት ሚና ቀስ በቀስ ከፖሊስነት (Police State) ወደ ማህበራዊ አገልግሎት አቅራቢነት ሊሸጋገር ችሏል፡፡ መንግስት በአገልግሎት አቅራቢነት ሚናው ውሀ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ መንገድ ወዘተ የመሳሰሉ መሰረታዊ ፍላጐቶችን የማሟላት ኃላፊነት ተጥሎበታል፡፡ በተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅጣጫውን ፈር ለማስያዝና ፍትሐዊ የሀብት ድልድል እንዲኖር እንዲሁም ለደካማው የህብረተሰብ ክፍል ጥበቃና ከለላ ለማድረግ በአጠቃላይ የነፃ ገበያን አሉታዊ ውጤቶችን ለመቀነስ ሰፊና ተከታታይ ቁጥጥርና ክትትል (Regulation) ያደርጋል፡፡ አዲሱ የማህበራዊ መንግስት አዲሱን አዎንታዊ ሚናውን በብቃትና ውጤታማ በሆነ መንገድ ይወጣ ዘንድ በዓይነትና በይዘት የጠንካራ ስልጣን ባለቤት ሊሆን የግድ የሚል ሀቅ ነው፡፡cየስልጣን አስፈላጊነቱ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ስልጣን በየጊዜው ወሰኑ፣ መጠኑና ቅርጹ እያደገና እየሰፋ በመጣ ቁጥር ግን የግለሰቦችን መብትና ነፃነት መንካቱ አይቀርም፡፡ የመንግስት ስልጣን እየተለጠጠ መሄድ አቅመቢስ ለሆነው ዜጋ የስጋት ምንጭ ነው፡፡ ፍፁም የሆነና ወደ ፍፁምነት የተጠጋ ስልጣን ወደ ህገ ወጥነትና የበዘፈቀደ ድርጊት የማምራት አደገኛ አዝማሚያ አለው፡:የአስተዳደር ህግ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የመንግስት ‘ጡንቻ መፈርጠም’ በቅጡ ለመቆጣጠር በታሪክ ሂደት በተጓዳኝ የተፈጠረ የህግ መሳሪያ ነው፡፡ መንግስት ተግባራቱን ለማከናወን ፖሊሲ ቀርጾ፣ ህግ አውጥቶ በሚያስፈጽምበት ወቅት በስልጣን እና በፍትህ (የግለሰቦች ነፃነት) መካከል ቅራኔ መከሰቱ የማይቀር እውነታ ነው፡፡ ጥያቄው ቅራኔው እንዴት ይፈታል? ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ የዚህ ቅራኔ የራሱ ውጤት ሲሆን ቅራኔውን በአንፃራዊ መልኩ ለማስማማትና ለማጣጣም በታሪክ ሂደት ብቅ ያለ ተግባራዊ መሳሪያ ነው፡፡d የአስተዳደር ህግ በዕቅድ ታስቦ የተወለደ ሳይሆን በሁኔታዎች አስገዳጅነት የተፈጠረ ክስተት ነው፡፡ ህጉ በሁለት በጉልበት የማይመጣጠኑ ጐራዎች ማለትም በመንግስትና በግለሰብ መካከል ሚዛናዊነትንና ፍትሐዊነትን ለማስፈን ይጥራል፡፡የአስተዳደር ህግ መንግስት በተለይ ስራ አስፈፃሚውና የአስተዳደር አካላት በህግ ከተፈቀደላቸው የስልጣን ክልል አልፈው ህገ ወጥ ድርጊት እንዳይፈጽሙ ቁጥጥር የሚያደርግና ይህንንም የሚያረጋግጥ ህግ ነው፡፡e በዚህም የህግ የበላይነት እንዲሰፍንና የግለሰቦች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዳይሸራረፉና እንዳይጣሱ ከለላ በመስጠትf ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ በተጨማሪም በህግ ማዕቀፍ ውስጥ ያለው ስልጣን በአግባቡና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል መሪ ደንቦችን በማስቀመጥና ስነ ስርዓታዊ ቅድመ ሁኔታዎችን በመዘርጋት የተለያዩ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችን በመጠቀም የግለሰቦችና የዜጐች መብቶችና ነፃነቶች እንዳይገሰሱና እንዳይደፈሩ ከለላ በመስጠት የህገ መንግስት ማስፈፀሚያ ሆኖ ያገለግላል፡፡ የአስተዳደር ህግ ምንነትለአስተዳደር ህግ ብያኔ በማበጀት ረገድ የመስኩ ባለሙያዎች በከፊልም ቢሆን የተለያየ እይታ አላቸው፡፡ በእርግጥ የአስተዳደር ህግ የጥናት ወሰኑን አስመልክቶ የሚከሰት ልዩነት ካልሆነ በቀር በመሰረታዊ እሳቤው ላይ የተራራቀ አቋም የለም፡፡ እንደ ህንዳዊው የአስተዳደር ህግ ምሁር አይ.ፒ. ማሴይ አገላለጽ በአስተዳደር ህግ ትርጓሜ ላይ ያለው ልዩነት ምንጩ በየጊዜው እያደገና እየተወሳሰበ የመጣው አስተዳደራዊ ሂደት ሲሆን ይህም ሂደቱን በሙሉ አጠቃሎ የያዘ ወጥ ትርጉም ለመስጠት አስቸጋሪ አድርጐታል፡፡gያም ሆኖ የአስተዳደር ህግ ትርጓሜ ቢያንስ ሁለት መሰረታዊ አላባውያንን ማካተት ይጠበቅበታል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የአስተዳደር ህግ ከይዘት ይልቅ ስነ ስርዓት ላይ የሚያተኩር ህግ ስለመሆኑ ግልጽ መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም የአስተዳደር ውሳኔው እንዴት ተሰጠ? እንጂ ይዘቱ ትክክል ይሁን አይሁን ፍርድ ቤቶች ሆነ የአስተዳደር ህግ ጣልቃ የሚገባበት ጉዳይ አይደለም፡፡በሁለተኛ ደረጃ ማንኛውም የአስተዳደር ህግ ትርጓሜ የህጉን ዓላማ ግምት ውስጥ ያስገባ ተግባራዊ አቀራረብ እንዲያቅፍ ይጠበቅበታል፡፡ የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ዓላማ ወይም ተግባር ስልጣንን መቆጣጠር ነው፡፡h ያ ሲባል ግን የአስተዳደር አካላት ስራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩና እንዳይላወሱ ማነቆ ሆኖ ያግዳቸዋል ማለት አይደለም፡፡ የስልጣን ቁጥጥር ሲባል ማንኛውም ባለስልጣን ሆነ መስሪያ ቤት በህግ ተለይቶ ከተቀመጠለት የስልጣን ገደብ እንዳያልፍና ስልጣን ቢኖረውም እንኳን ስልጣኑን ፍትሐዊና አግባብ በሆነ መንገድ እንዲወጣ ያደርጋል ለማለት ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ዓላማና ተግባር ስልጣንን በተግባር መቆጣጠር እንደመሆኑ ይህን ባህርዩን ግምት ውስጥ ያላስገባ ብያኔ የተሟላ ተብሎ ሊወሰድ ሆነ ሊወደስ አይችልም፡፡ለንጽጽር እንዲረዳን በመስኩ ባለሙያዎች ለአስተዳደር ህግ የተሰጡ ትርጓሜዎችን እንደሚከተለው እንጠቅሳለን፡፡ቤርናርድ ሺዋሬዝ (Bernard Schwartz) የአስተዳደር ህግን ‘በውክልና ህግ የማውጣትና አስተዳደራዊ ዳኝነት የመስጠት ስልጣን ባላቸው የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ህግ’ በማለት ይገልፀዋል፡፡i ይህ ብያኔ ጠባብ ከመሆኑ በቀር ስለ ህጉ ይዘት ገላጭ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ በውክልና ስልጣን ህግ ከማውጣትና ከአስተዳራዊ የዳኝነት ስልጣን በተጨማሪ ይህ ስልጣን በፍርድ የሚታረምበትን የአጣሪ ዳኝነት (judicial review) ስነ-ስርዓት እንዲሁም በፖርላማና በተለያዩ ተቋማት የሚደረግ ቁጥጥርንም ያካትታል፡፡ጄኒንግስ በበኩሉ የአስተዳደር ህግ ማለት ‘አስተዳደርን የሚመለከት ህግ ነው፡፡ ይህ ህግ የአስተዳደር መስሪያ ቤቶችን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ግዴታ ይወስናል፡፡’ በማለት ይገልጸዋል፡፡j እንደ አይ.ፒ ማሴይ አስተያየት ይህ ትርጓሜ የአስተዳደር ህግን ከህገ መንግስት በግልጽ አይለይም፡፡ አስተዳደር ወይም ማስተዳደር ማለት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስልጣንን በመጠቀም የህብረተሰቡን ጉዳይ መምራት ማለት ነው፡፡k ለዚህም በዋነኛነት አደራ የተጣለባቸው አካላት የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ናቸው፡፡ ምንም እንኳን የእነዚህ ተቋማት ስልጣንና ግዴታ በዝርዝር ህግ ተለይቶ ቢወሰንም የስራ አስፈፃሚው አካል ስልጣን በጠቅላላው የሚቀመጠው በህገ መንግስት ላይ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ሆነ ህገ መንግስት ሁለቱም የመንግስት አስተዳደርን ወይም የግለሰብና የመንግስትን ግንኙነት የሚመሩ ህጐች እንደመሆናቸው በመካከላቸው ያለው መለያ ክር በጄኒንግ ትርጓሜ ላይ በግልጽ ነጥሮ አልወጣም፡፡ታዋቂው የህገ መንግስት ሊቅ ኤ. ቪ. ዲሴይ የአስተዳደር ህግን በሶስት ደረጃዎች ከፋፍሎ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡lየአስተዳደር ህግ የመንግስት ባለስልጣናትን የህግ ስልጣንና ተጠያቂነት የሚወስኑትን የአንድ አገር የህግ ስርዓት የሚመለከት የህግ ክፍል ነው፡፡ግለሰቦች ከመንግስት አካላት ጋር በሚኖራቸው ግንኙነት ያላቸውን መብትና ግዴታ ለይቶ ይወስናል፡፡እነዚህ መብቶችና ግዴታዎች ተፈጻሚ የሚሆኑበትን ስርዓት ይዘረጋል፡፡እንደ ማሴይ ትችት ይህ ትርጓሜ የአስተዳደር ህግ አንድ አካል የሆነውን አጣሪ ዳኝነት (judicial review) ብቻ የሚመለከት እንደመሆኑ በይዘቱ ጠባብ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ከአጣሪ ዳኝነት በተጨማሪ በህግ አውጭውና በተቋማት (ለምሳሌ በእንባ ጠባቂ ተቋምና ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን) አማካይነት የሚደረግ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችንም ያካትታል፡፡ ህጉ ከመንግስት ባለስልጣናትና ከአስተዳደር መስሪያ ቤቶች በተጨማሪ ከፊል የአስተዳደር አካላት ተብለው የሚፈረጁትን መንግስታዊ ኮርፖሬሽኖች፤ ዩኒቨርሲቲዎች እና በከፊል መንግስታዊ ነክ ስልጣን ያላቸውን ማህበራትm በተመለከተም ተፈጻሚነት አለው፡፡በመጨረሻም ታዋቂው የህንድ ምሁር አይ.ፒ. ማሴይ ከላይ ከተሰጡት ሰፋ ያለና የህጉን ባህሪያትና ተግባራት ጠቅልሎ የያዘ ብያኔ እንደሚከተው ያስቀምጣል፡፡የአስተዳደር ህግ የህዝብ አስተዳደር ህግ አካል ሲሆን የአስተዳደርና ከፊል አስተዳደር መስሪያ ቤቶችን አደረጃጀትና ስልጣን የሚደነግግ፣ አስተዳደራዊ ውሳኔ የሚሰጥበትን ደንብና መርህ የሚያስቀምጥ፣ እንዲሁም ከግለሰቦች መብትና ነፃነት ውሳኔው የሚታረምበትን ስርዓት የሚወስን የህግ ክፍል ነው፡፡nይህ ትርጓሜ ከሞላ ጐደል ሁሉንም የአስተዳደር ህግ ባህርያት አጠቃሎ የያዘ በመሆኑ ተመራጭነት አለው፡፡ ከላይ ከቀረቡት የተለያዩ ትርጓሜዎች የሚከተሉት የጋራ ነጥቦች ይመዘዛሉ::አንደኛ፤ የአስተዳደር ህግ የአስተዳደር እና ከፊል የአስተዳደር አካላት ያላቸውን ስልጣን፣ ተግባርና ኃላፊነት ያጠናል፡፡o የማንኛውም የአስተዳደር አካል የስልጣን ምንጭ የሚገኘው ከማቋቋሚያ አዋጁ (Enabling Act) ሲሆን አልፎ አልፎ በሌላ ዝርዝር ህግ ይወሰናል፡፡ በአስተዳደር ህግ የመጀመሪያው ጥያቄ ውሳኔ ወይም እርምጃ የወሰደው አካል በህግ የተሰጠው ስልጣን አለው? የሚል ነው፡፡ ከሌለ ድርጊቱ ከስልጣን በላይ ስለሆነ ዋጋ አልባ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ከድርጊቱ በስተጀርባ የህግ ስልጣን ካለ ውሳኔ ሰጪው ስልጣኑን በአግባቡና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንደተገለገለ ይጣራል፡፡ ካልሆነ ስልጣኑን ያለ አግባብ በሚገለገለው አካል ላይ ህጉ ቁጥጥር ያደርግበታል፡፡ሁለተኛ፤ ህጉ ስልጣንን በመገልገል ሂደት ተፈጻሚ የሚሆኑ መሪ ደንቦችን፤ ስነ ስርዓቶችንና መርሆዎችን ያስቀምጣል፡፡ ህግ አውጭው ለአስተዳደር አካላት ስልጣን ሲሰጥ ስልጣኑ ተግባር ላይ በሚውልበት ጊዜ ህጋዊነቱንና ፍትሐዊነቱን የሚያረጋግጥ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታ አብሮ እንዲደነግግ ይጠበቃል፡፡ ለምሳሌ ያህል ደንብና መመሪያ በማውጣት ረገድ ከሚመለከተው አካል ጋር የመመካከርና የህትመት ቅድመ ሁኔታዎች፣ አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሰጥ የመሰማት መብትና የኢ- አድሎአዊነት መርሆዎችን በአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ወይም በዝርዝር ህግ ማውጣት ይኖርበታል፡፡ እነዚህም በአስተዳደር ሂደቱ ውስጥ ፍትሐዊነትን በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ስፍራ አላቸው፡፡ ስልጣን በዘፈቀደ ሳይሆን በአግባቡ ስራ ላይ ዋለ ለማለት የሚቻለውም ያኔ ነው፡፡ሶስተኛ፤ የአስተዳደር ህግ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችን በተመለከተ የሚያጠና ህግ ነው፡፡p ልጓም የሌለው ስልጣን ለዜጎች መብትና ነፃነት ፀር ነው፡፡ የተጠያቂነት መርሕ እውን እንዲሆን የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችም በግልጽ ተለይተው መቀመጥ ይኖርባቸዋል፡፡ ስለሆነም የአስተዳደር ህግ በፍርድ ቤት፤ በአስተዳደር ፍርድ ቤት፤ በህግ አውጭው እና በተቋማት የሚደረጉ የስልጣን መቆጣጠሪያ መንገዶችን በተግባር እየፈተነ ያጠናል፡፡አራተኛ፤ ህጉ በአስተዳደር አካላት ወይም በመንግስት ባለስልጣናት በተወሰዱ እርምጃዎች መብታቸው ለተጣሰና ነፃነታቸው ለተገፋ ዜጎች መፍትሔ ይሰጣል፡፡q መብት ያለ መፍትሔ ‘ላም አለኝ በሰማይ’ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ መብቱ የተጓደለበት ሰው አቤቱታ አቅርቦ መፍትሔ የሚጠይቅበትና የሚያገኝበት የህግ ክፍል ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ግብና ተግባራትየአስተዳደር ህግ ዋነኛ ዓላማና ተግባር ስልጣንን መቆጣጠር ስለመሆኑ በመስኩ ምሁራን ስምምነት የተደረሰበት ጉዳይ ሆኗል፡፡ ሆኖም በዚህ ብቻ ሳይወሰን ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትንም ያከናውናል፡፡ እንደ ብዙዎች የአስተዳደር ህግ ሊቃውንት የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ግብ አስተዳደራዊ ፍትህን ማስፈን ሲሆን የሚከተሉት ተግባራት ይኖሩታል፡፡ስልጣን መቆጣጠር (Control Function)የአስተዳደር ህግ ስራ አስፈፃሚው የመንግስት አካልና የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች፣ ሚኒስትሮች፣ ባለስልጣናትና ሌሎች ሹመኞች በህግ ተለይቶ የተሰጣቸውን ስልጣን አልፈው እንዳይሄዱና ህጋዊ ስልጣናቸውንም አለአግባብ እንዳይገለገሉበት ለመቆጣጠር የሚያስችለን የህግ ክፍል ነው፡፡ በመሆኑም ስልጣን በህገ ወጥ መንገድ አለአግባብ ጥቅም ላይ እንዳይውል በመከላከል እንደ መገደቢያ መሳሪያነት ያገለግላል፡፡rግዴታ ማስፈፀም (Command Function)በአስተዳደሩ በሚፈፀም ድርጊት የዜጋው መብት ከሚጣስበት ሁኔታ ባልተናነስ ህጋዊ ግዴታን አለመወጣት በግል መብትና ጥቅም ላይ የከፋ ጉዳት ያስከትላል፡፡ የአስተዳደር ህግ ስልጣን በልኩና በአግባቡ ተግባር ላይ እንዲውል ከመቆጣጠር ባሻገር የአስተዳደር አካላት በህግ ተለይቶ የተጣለባቸውን ግዴታ እንዲወጡ አስገዳጅ የስነ ስርዓትና ተቋሟዊ ስልቶችን ይቀይሳል፡፡s አስገዳጅ የህግ ማዕቀፍ ከሌለ ግዴታ በፈቃድ ላይ የተመሰረተ ውዴታ ብቻ ሆኖ ይቀራል፡፡የአስተዳደር ፍትህ ማስፈንበየትኛውም ህግን ለማስፈፀም ስልጣን በተሰጠው የመንግስት አካል የሚወሰዱ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችና እርምጃዎች የህዝብ አመኔታና ተቀባይነት እንዲያገኙ ፍትሐዊነታቸው በተጨባጭ ሊታይ ይገባል፡፡ የአስተዳደር ህግ አይነተኛ ተልዕኮ የአስተዳደር ፍትህን ማስፈን ነው፡፡tግልጽነት ተጠያቂነትና የህዝብ ተሳትፎየአስተዳደር ህግ በመንግስት አስተዳደር ስራ ውስጥ ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና የህዝብ ተሳትፎ እንዲረጋገጥ ተግባራዊ መሳሪያ በመሆን ያገለግላል፡፡ የስልጣን ልኩ ሳይታወቅና ከልክ በላይ የሆነ ስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቱ ሳይቀየስ ስለተጠያቂነት ማውራት የማይመስል ነገር ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ዜጎች መረጃ የማግኘት መብታቸውን በህግ የሚያረጋግጥ ከመሆኑም በላይ በህዝብ አስተዳደር ውስጥ በንቃት እንዲሳተፉ የሚያስችሉ የስነ- ስርዓት ደንቦችን ይዘረጋል፡፡ለተበደለ ወገን መፍትሔ መስጠትየአስተዳደር ህግ ዜጎች ለደረሰባቸው በደል በፍርድ ቤት ወይም ከፍርድ ቤት ውጭ ባሉ መንገዶች አቤቱታ አቅርበው በአነስተኛ ወጪ እና በቀላሉ መፍትሔ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል፡፡ ስለ አስተዳደር ህግ በተደጋጋሚ ቢወራ ‘አንጀት ጠብ’ የሚል፣ የሚጨበጥ፣ የሚዳሰስ፣ መፍትሔ እስከሌለ ድረስ ረብ የለሽነቱን ያጎላው እንደሆነ እንጂ የሚፈይደው ነገር የለም፡፡ የአስተዳደር ህጋቸው በዳበረ አገራት የመንግስት ባለስልጣናት በህዝብ ላይ ለሚፈፅሟቸው አስተዳደራዊ በደሎች በዝርዝር የተቀመጡ የመፍትሔ መንገዶች አሏቸው፡፡በአንድ አገር ውስጥ የአስተዳደር ህግ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራቱን ውጤታማ በሆነ መንገድ ተወጥቷል ለማለት ከአገሪቱ የመንግስት አወቃቀር ስርዓት፤ ህገ መንግስታዊና ዲሞክራሲያዊ ዕድገትና የአስተዳደር ህግ ተቋማት መዳበር ከግምት ውስጥ በማስገባት አንፃራዊ በሆነ መልኩ የሚለካ ጉዳይ ነው፡፡ በአጠቃላይ ግን በአንድ አገር ውስጥ ሁሉን አቀፍ ውጤታማና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰ የአስተዳደር ህግ ስርዓት አለ ለማለት ከሚከተሉት ሶስት ዋነኛ መርሆዎች አንጻር እየተመነዘረ መገምገም አለበት፡፡የአስተዳደር ፍትህየአስተዳደር በደል በፍርድ የሚታረምበትና አስተዳደራዊ ፍትሕ የሚገኝበት የፍርድ ሂደትና መንገድ እንዲሁም ተሞክሮ በአገራችን ውስጥ በግልጽ የሚታወቅ አይደለም፡፡ የአስተዳደር ፍትሕ የአስተዳደር ህግ ‘ልቡ’ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አስተዳደራዊ በደል አለቅጥ በተንሰራፋበት አገር ውስጥ የአስተዳደር ህግ ትንፋሽ ያጠረው ህላዌነቱ የሚያጠራጥር ህግ ነው፡፡ የከለላው መጠን የአስተዳደር ፍትህ ደረጃ አንጻራዊ መለኪያ ነው፡፡የስራ አስፈፃሚው ተጠያቂነትየዚህ መርህ ዋና አላማ ህግ የማስፈፀም ስልጣን ያለው አካል ለሚፈፅመው ድርጊት እና ለሚወስደው እርምጃ በህዝብ ፊት ተጠርቶ እንዲጠየቅና ማብራሪያ እንዲሰጥ ለማስገደድ ነው፡፡ ማንኛውም የመንግስት ባለስልጣንን የተቀበለ አካል ወይም ባለስልጣን የሚፈፅመው ድርጊት የህዝቡን ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆን ይኖርበታል፡፡ ውሳኔ ሰጭው ለድርጊቱ ትክክለኛነትና ፖለቲካዊ ተገቢነት ህግ አውጭው ፊት ተጠርቶ በመቅረብ ለማብራሪያ የሚገደድበት ስርዓት ከሌለ በቀር ተጠያቂነት አለ ማለት አይቻልም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አስተዳደሩ በዜጎች መብት ለሚያደርሰው ጉዳት በፍርድ ሂደት ለድርጊቱ ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፡፡መልካም አስተዳደርበዚህ መርህ መሰረት አስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ሁሉን አቀፍ ተቀባይነት ላገኙ መሪ ደንቦች መገዛት አለበት፡፡ እነዚህም የፍትሀዊነት፣ምክንያታዊነት፣ ሚዛናዊነትና የግልፅነት መርሆዎችን ያጠቃልላሉ፡፡ አስተዳደራዊ ውሳኔ በህጉ መሰረት መወሰዱ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ የውሳኔው መሰረት ከቅን ልቦና የመነጨ፣ለባለጉዳዩ ግልፅ በሆነ አሰራርና መንገድ ያልተወሰደ ካልሆነ በስተቀር የመንግስት አስተዳደር ወደ መልካምነት ደረጃ ለመድረስ ገና ብዙ ይቀረዋል፡፡ የአስተዳደር ህግ እነዚህን መርሆዎች እንዲዳብሩ ከማድረግ አንፃር አይነተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ ስለሆነም የህጉ የእድገት ደረጃ የአንድ አገር የመልካም አስተዳደር ሁኔታ ጠቋሚ መለኪያ ነው ማለት እንችላለን፡

በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ)(ለ) 35:38 እና የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ጥቁር 1176/2012 አንቀጽ 6(2) ን በመተላለፍ ተብለው በፖለቲከኞች ላይ የቀረበው ክስ።


Introduction to Law and Legal Systems


Introduction to Law and Legal Systems LEARNING OBJECTIVES After reading this chapter, you should be able to do the following: Distinguish different philosophies of law—schools of legal thought—and explain their relevance. Identify the various aims that a functioning legal system can serve. Explain how politics and law are related. Identify the sources of law and which laws have priority over other laws. Understand some basic differences between the US legal system and other legal systems. Law has different meanings as well as different functions. Philosophers have considered issues of justice and law for centuries, and several different approaches, or schools of legal thought, have emerged. In this chapter, we will look at those different meanings and approaches and will consider how social and political dynamics interact with the ideas that animate the various schools of legal thought. We will also look at typical sources of “positive law” in the United States and how some of those sources have priority over others, and we will set out some basic differences between the US legal system and other legal systems.

The Revised Family Code Proclamation No-213-2000 The Revised Family Code


The Revised Family Code Proclamation No-213-2000 The Revised Family Code

Proclamation-of-2000- Preamble   WHEREAS, the family, being the natural basis of society, shall be protected by the society and the state, and that one of the means of protection is effected by regulating and governing family relation by law; WHEREAS, it has become essential to make the existing Ethiopian family law in accordance with the socio-economic development of the society and, above all, with the Constitution of the country, and, in particular, realizing that marriage shall be based on the free consent of the spouses, and that it is necessary to provide the legal basis which guarantees the equality of the spouses during the conclusion, duration and dissolution of marriage; WHEREAS, it has become necessary to amend the existing law in such a way that it gives priority to the well-being, upbringing and protection of children in accordance with the Constitution and International Instruments which Ethiopia has ratified; WHEREAS, it is found necessary to settle disputes arising in family by a competent organ in a just and efficient manner; WHEREAS, in order to realize these objectives, it has become essential that a family law be enacted by the House of Peoples’ Representative to be applicable in administration that are directly accountable to the Federal Government; NOW, THERFORE, in accordance with Article 55(1) of the Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia, it is hereby proclaimed as follows: 1. Short Title This proclamation may be cited as the “Revised Family Code Proclamation No. 213/2000.”

Essential Conditions of Marriage


Essential Conditions of Marriage

Article 6. – Consent. A valid marriage shall take place only when the spouses have given their free and full consent. Article 7. – Age 1) Neither a man nor a woman who has not attained the full age of eighteen years shall conclude marriage. 2) Notwithstanding the provisions of Sub-Article (1) of this Article, the Minister of Justice may, on the application of the future spouses, or the parents or guardian of one of them, for serious cause, grant dispensation of not more than two years. Article 8. – Consanguinity. 1) Marriage between persons related by consanguinity in the direct line, between ascendants and descendants, is prohibited. 2) In the collateral line, a man cannot conclude marriage with his sister or aunt; similarly, a woman cannot conclude marriage with her brother or uncle. Article 9. – Affinity 1) Marriage between persons related by affinity in the direct line is prohibited. 2) In the collateral line, marriage between a man and the sister of his wife, and a woman and the brother of her husband is prohibited. Article 10. – Filiations not Established Legally. The existence of a bond of natural filiation which is commonly known to the community is sufficient to render applicable the impediments to marriage referred to in Articles 8 and 9, notwithstanding that the filiation is not legally established. Article 11. – Bigamy. A person shall not conclude marriage as long as he is bound by bonds of a preceding marriage. Article 12. – Representation not Allowed. 1) Each of the future spouses shall personally be present and consent to the marriage at the time and place of its celebration. 2) Notwithstanding the provisions of Sub-Art. (1) of this Article, marriage by representation may be allowed by the Ministry of Justice where it has ascertained that there is a serious cause and the person who intended to do so has fully consented thereto. Article 13. – Fundamental Error. 1) Marriage concluded as a result of error in consent shall not be valid. 2) Consent is deemed to be vitiated as a result of error where such error is a fundamental error. 3) Without prejudice to the provisions of Sub-Article (2) of this Article, the following shall be considered to be fundamental errors: (a) Error on the identity of the spouse, where it is not the person with whom a person intended to conclude marriage; (b) Error on the state of health of the spouse who is affected by a disease that does not heal or that can be genetically transmitted to descendants; (c) Error on the bodily conformation of the spouse who does not have the requisite sexual organs for the consummation of the marriage; (d) Error on the behavior of the spouse who has the habit of performing sexual acts with person of the same sex. Article 14. – Consent Extorted by Violence. 1) Marriage concluded as a result of consent which is extorted by violence shall be valid. 2) Consent is deemed to be extorted by violence where it is given by a spouse to protect himself or one of his ascendants or descendants, or any other close relative from a serious and imminent danger or threat of danger. Article 15. – Judicially Interdicted Persons. 1) Any person who is judicially interdicted shall not be conclude marriage unless authorized, for that purpose, by the court. 2) An application to this effect may be made by the interdicted person himself or by his guardian. Article 16. – Period of widowhood. 1) A woman may not remarry unless one hundred and eight days have elapsed since the dissolution of the previous marriage. 2) The provision of Sub-Article (1) of this Article shall not apply where: (a) The woman gives birth to a child after the dissolution of her marriage; (b) The woman remarries her former husband; (c) It is proved by medical evidence that the woman is not pregnant; (d) The court dispenses the woman from observing the period of widowhood

CONCLUSION OF MARRIAGE


CONCLUSION OF MARRIAGE  

Section 1. General Article 1. – Various Forms of Marriage. 1) Marriage may be concluded before an officer of civil status. 2) Notwithstanding the provision of Sub-Article (1) of this Article, marriage may be concluded in accordance with the religion or custom of the future spouses. Article 2. – Marriage Concluded before an Officer of Civil Status. Marriage shall be deemed to be concluded before an officer of civil status when a man and a woman have appeared before an officer of civil status for the purpose of concluding marriage and the officer of civil status has accepted their respective consent. Article 3. – Religious Marriage. Religious marriage shall take place when a man and a woman have performed such acts or rites as deemed to constitute a valid marriage by their religion or the religion of one of them. Article 4. – Marriage According to Custom. Marriage according to custom shall take place when a man and a woman have performed such rites as deemed to constitute a valid marriage by the custom of the community in which they live or by the custom of the community to which they belong or to which one of them belongs. Article 5. – Marriage Celebrated Abroad. Marriage celebrated abroad in accordance with the law of the place of celebration shall be valid in Ethiopia so long as does not contravene public moral.  

አዋጅ ቁጥር 668/2002 የሙስና ወንጀልን የሚመለከቱ ሕጎች በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 (1)


አዋጅ ቁጥር 668/2002
የሙስና ወንጀልን የሚመለከቱ ሕጎች

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት
አንቀጽ 55 (1)
የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002”

ትርጓሜ

የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ አዋጅ ውስጥ፦
‘‘ሀብት‘‘ ማለት ማንኛውም የማይንቀሳቀስ ወይም የሚንቀሳቀስ ወይም ግዙፍነት ያለው ወይም የሌለው ንብረት ሲሆን የመሬት ይዞታን እና ዕዳን ይጨምራል፤
ኮሚሽን” ማለት የፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ነው፤
‘‘የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል” ማለት በመንግሥት መሥሪያ ቤት ወይም በመንግስት የልማት ድርጅት የስነ-ምግባር ሁኔታን የሚያስተባብርና የሚያማክር አካል ነው፤
‘‘ተሿሚ” ማለት የሚከተሉትን ያጠቃልላል፡-
የሪፐብሊኩን ፕሬዚዳንት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን፣ ሚኒስትሮችን፣ ሚኒስትር ዴኤታዎችን፣ ምክትል ሚኒስትሮችን፣ ኮሚሽነሮችን፣ ምክትል ኮሚሽነሮችን፣ ዋና ዳይሬክተሮችንና ምክትል ዋና ዳይሬክተሮችን፤
የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተሞች አስተዳደሮች ከንቲባዎችንና ሌሎች ተሿሚዎችን፤
የመደበኛና የከተማ ነክ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶችን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶችንና ዳኞችን፤
የመከላከያ ሠራዊትና ፖሊስ ተሿሚዎችን፤
አምባሳደሮችን፣ የቆንስላዎችና የሌሎች የዲፕሎማቲክ ሚሲዮን ኃላፊዎችን፤
ዋና ኦዲተርንና ምክትል ዋና ኦዲተርን፤
የብሔራዊ ባንክ ገዥና ምክትል ገዢን፤
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የሥራ አመራር ቦርድ አባላትን፣ ሥራ አስኪያጆችንና ምክትል ሥራ አስኪያጆችን፤
የመንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞች ፕሬዝዳንቶችንና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን።
‘‘ተመራጭ” ማለት የሚከተሉትን ያጠቃልላል፡-
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሎችን፤
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባሎችን፤ እና
የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተሞች አስተዳደር ምክር ቤቶች አባሎችን።
‘‘የመንግሥት ሠራተኛ” ማለት የሚከተሉትን ያጠቃልላል፡-
በመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የመምሪያ ኃላፊነት፣ የዳይሬክተርነት፣ የአገልግሎት ኃላፊነትና ከነዚህ ተመጣጣኝና በላይ ደረጃ ያላቸው ሠራተኞችን፤
የተሿሚዎች አማካሪዎችን፤
ፈቃድ የመስጠት፣ የመቶጣጠር ወይም ግብር የመሰብሰብ ሥራ የሚያከናውኑ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሠራተኞችን፣ ዐቃቤ ሕጎችን፣ መርማሪዎችን፣ የትራፊክ ፖሊሶችን፣ እና
ኮሚሽኑ በሚያወጣው መመሪያ ተለይተው የሚወስኑ ሌሎች የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሠራተኞችን።
‘‘ቤተሰብ” ማለት የተሿሚ፣ የተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የትዳር ጓደኛ ወይም በሥሩ የሚተዳደር ዕድሜው 18 ዓመት ያልሞላ ልጅ ሲሆን ጋብቻ ሳይፈጽም እንደ ባልና ሚስት አብሮ የሚኖር ሰውን እና የጉዲፈቻ ልጅን ይጨምራል፤
‘‘የቅርብ ዘመድ” ማለት የተሿሚ፣ የተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ወላጆችን፣ ተወላጆችን፣ እህቶችን፣ ወንድሞችን እና ሌሎች እስከ ሦስተኛ ደረጃ የሥጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ያላቸው ሰዎችን ያጠቃልላል፤
‘‘የመንግስት መስርያ ቤት” ማለት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመንግስት በጀት የሚተዳደርና የህግ አውጪነት፣ የዳኝነት እና ወይም አስፈጻሚነት የመንግስት ስራዎች የሚከናወኑበት ማናቸውም መስርያ ቤት ነው፤
‘‘የመንግስት ልማት ድርጅት” ማለት የባለቤትነት ድርሻ በሙሉ ወይም በከፊል ያለበት ማንኛውም የመንግስት የልማት ድርጅት ወይም የአክሲዮን ኩባንያ ነው፤
‘‘ሰው“ ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፤
ማንኛውም በወንድ ዖታ የተገለጸ አነጋገር ሴትንም ይጨምራል፡፡
የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ አዋጅ በፌዴራል መንግሥት እና በአዲስ አበባና በድሬዳዋ ከተሞች አስተዳደሮች ተሿሚዎች፣ ተመራጮችና የመንግስት ሠራተኞች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
ክፍል ሁለት
ሀብትን ስለማሳወቅና ስለማስመዝገብ
የማስመዝገብ ግዴታ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ፡-
በራሱና በቤተሰቡ ባለቤትነት ወይም ይዞታ ሥር የሚገኝ ሀብትን፣ እና
የራሱንና የቤተሰቡን የገቢ ምንጮች፣ የማሳወቅና የማስመዝገብ ግዴታ አለበት፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ መሠረት ሀብቱን የሚያስመዘግብ ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የራሱንና የቤተሰቡን ሀብትና የገቢ ምንጮች ለየብቻ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀ ቅጽ ላይ በመሙላት ትክክለኛነቱን በፊርማው ያረጋግጣል።
በምዝገባ ስለማይካተት ሀብት
የዚህ አዋጅ አንቀጽ 4 ድንጋጌ ቢኖርም የሚከተሉት ሀብቶች አይመዘገቡም፡-
በውርስ ተገኝቶ በጋራ የተያዘና ለወራሾቹ የግል አገልግሎት የሚውል ንብረት፤
የቤት እቃዎችና የግል መገልገያዎች፤
ከጡረታ የሚገኝ ገቢ፡፡
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1//ሀ/ መሠረት በጋራ የተያዘ ንብረት በወራሾች መካከል እንደተከፋፈለ ድርሻውን አሳውቆ ማስመዝገብ አለበት፡፡
ስለመዝጋቢው አካል
የተሿሚዎችን፣ የተመራጮችንና የመንግሥት ሠራተኞችን ሃብት የሚመዘግበው ኮሚሽኑ ይሆናል፡፡
ኮሚሽኑ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የተሿሚዎችን፣ የተመራጮችን ወይም የመንግሥት ሠራተኞችን ሃብት እንዲመዘግብ እንደሁኔታው በሙሉ ወይም በከፊል የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍልን ሊወክል ይችላል፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /2/ መሠረት ውክልና የተሰጠው እያንዳንዱ የሥነ- ምግባር መከታተያ ክፍል በዚህ አዋጅ አንቀጽ 4 ንዑስ አንቀጽ /2/ መሠረት የቀረበለትን የሃብት ማስመዝገቢያ ስነድ ምዝገባው በተደረገ በ30 ቀናት ውስጥ ለኮሚሽኑ ያስተላልፋል።
ኮሚሽኑ በዚህ አንቀጽ መሠረት የተከናወኑ የሀብት ምዝገባ ሰነዶች ጠባቂ ሆኖ ያገለግላል። ሃብታቸውን ላስመዘገቡ ተሿሚዎች፣ ተመራጮችና የመንግሥት ሠራተኞች የምዝገባ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡
ምዝገባ ስለሚካሄድበት ጊዜ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግስት ሠራተኛ ይህ አዋጅ ስራ ላይ ከዋለበት ከስድስት ወር በኋላ ባለው ስድስት ወር ውስጥ ሀብቱን ማሳወቅና ማስመዝገብ አለበት፡፡
ማንኛውም አዲስ ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግስት ሠራተኛ ሀብቱን የሚያሳውቀውና የሚያስመዘግበው ከተሾመበት፣ ከተመረጠረበት ወይም ከተቀጠረበት ቀን ጀምሮ በ45 ውስጥ ነው፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ ወይም /2/ መሠረት ሀብቱን ያስመዘገበ ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ከዚያ በኋላ ሀብቱን የሚያሳውቀውና የሚያስመዘግበው በየሁለት ዓመቱ ሆኖ የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ በ30 ቀናት ውስጥ ይሆናል፡፡
የምዝገባ ጊዜን ስለማራዘም
የምዝገባ ጊዜ እንዲራዘምለት የሚጠይቅ ሰው ምዝገባውን ማራዘም ያስፈለገበትን ምክንያት በጽሑፍ በመግለጽ የምዝገባ ጊዜው በተጠናቀቀ በአምስት ቀናት ውስጥ ለኮሚሽኑ ወይም ለሚመለከተው የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ማመልከት ይችላል።
ኮሚሽኑ ወይም ጉዳዩ የሚመለከተው የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ መሠረት የቀረበለት ጥያቄ በበቂ ምክንያት የተደገፈ ሆኖ ሲያገኘው የምዝገባውን ጊዜ ለአንድ ጊዜ እስከ 30 ቀናት ሊያራዝም ይችላል።
የምዝገባ ጊዜ እንዲራዘምለት ለሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ያቀረበው አቤቱታ ውድቅ የተደረገበት አመልካች ውሳኔው በደረሰው አምስት ቀናት ውስጥ ቅሬታውን ለኮሚሽኑ ሊያቀርብ ይችላል። ኮሚሽኑ የሚሰጠው ውሳኔም የመጨረሻ ይሆናል፡፡
ዘግይቶ ስለማስመዝገብ
በመደበኛው ወይም በተራዘመለት የማስመዝገቢያ ጊዜ ውስጥ ሀብቱን ያላስመዘገበ ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ብር አንድ ሺ መቀጫ ከፍሎ በ30 ቀናት ውስጥ ሊያስመዘግብ ይችላል፡፡
ከስንብት በኋላ ስለሚከተሉ ግዴታዎች
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ በጡረታ ሲገለል ወይም በማንኛውም ምክንያት አገልግሎቱን ሲያቋርጥ ሁበቱን በ30 ቀናት ውስጥ ለኮሚሽኑ ወይም ለሚመለከተው የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል እንዲሁም ከሁለት ዓመት በኋላ ለመጨረሻ ጊዜ ለኮሚሽኑ ማሳወቅ አለበት፡፡
የምዝገባን ትክክለኛነት ስለማረጋገጥ
ኮሚሽኑ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 4 ንዑስ አንቀጽ /2/ መሠረት በተሿሚ፣ በተመራጭ ወይም በመንግሥት ሠራተኛ በተሞላ መረጃ ያልተሟላ፣ ትክክል ያልሆነ ወይም የሀሰት መረጃ የያዘ መሆኑን ለመጠርጠር በቂ ምክንያት ሲኖረው ወይም ሀብቱ በትክክል አልተመዘገበም የሚል ጥቆማ ሲቀርብ ወይም በተፈጸመ ወንጀል ምክንያት ምርመራ ሲጀመር የምዝገባውን ትክክለኛነት የማጣራት ተግባር ያከናውናል።
ኮሚሽኑ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ መሠረት የማጣራት ተግባር ሲያከናውን፡-
ጉዳዩ የሚመለከተው ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ተጨማሪ መረጃ ወይም ማብራሪያ እንዲያቀርብ ሊጠይቀው፣
የተሿሚውን፣ የተመራጩን ወይም የመንግሥት ሠራተኛውን ሀብት የሚመለከት መረጃ ያለው ባንክ፣ የፋይናንስ ተቋም ወይም ማንኛውም ሌላ ሰው መረጃውን እንዲሰጥ ሊያዘው፣ እና
የዋና ኦዲተርን ወይም የሌላ አግባብነት ያለውን አካል ሙያዊ ድጋፍ ሊጠቀም፣
ይችላል።
ኮሚሽኑ ያልተሟላ፣ ትክክል ያልሆነ ወይም የሀሰት መረጃ መቅረቡን በማስረጃ ሲያረጋግጥ ጥፋት በፈጸመው ሰው ላይ በህጉ መሠረት አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድበት ያደርጋል፡፡
የምዝገባ መረጃ ተደራሽነት
በኮሚሽኑ እጅ የሚገኝ ማንኛውም የተሿሚ፣ የተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የሀብት ምዝገባ መረጃ ለህዝብ ክፍት ይሆናል፡፡
ስለሀብት ምዝገባ መረጃ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ጥያቄውን በጽሁፍ ለኮሚሽኑ ወይም ጉዳዩ ለሚመለከተው የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ሊያቀርብ ይችላል።
ኮሚሽኑ ወይም የሚመለከተው የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል የቀረበውን ጥያቄ በመቀበል የምዝገባውን መረጃ ለጠየቀው ሰው መስጠት አለበት፡፡
የዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች ቢኖሩም የቤተሰብ ሀብትን የሚመለከት የምዝገባ መረጃ ለፍትህ ሥራ ወይም ኮሚሽኑ አስፈላጊ ነው ብሎ ለሚወስነው ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በሚስጥር የሚያዝ ይሆናል፡፡
ኮሚሽኑ በዚህ አዋጅ መሠረት በየሁለት ዓመቱ ስላከናወነው የሀብት ምዝገባ አጠቃላይ መረጃ በሪፖርት መልክ ያወጣል።
የሃብት አለመመዝገብ የሚያስከትለው ውጤት
በዚህ አዋጅ መሠረት ያልተመዘገበ ማናቸውም የተሿሚ፣ የተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ሀብት ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ በስተቀር ለወንጀል ሕግ አንቀጽ 419/2/ ድንጋጌ አፈጻጸም ሲባል ምንጩ እንዳልታወቀ ንብረት ይቆጠራል።
ክፍል ሶስት
የጥቅም ግጭትን ስለማሳወቅና ስለማስወገድ
መርህ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የያዘውን መንግሥታዊ የሃላፊነት ቦታ የሕዝብን ጥቅም ለማስጠበቅ ብቻ ማዋል አለበት፡፡ በማንኛውም ምክንያት ቢሆን በሥራው አጋጣሚ ያገኘውንና ሕዝብ እንዲያውቀው ያልተደረገን መረጃ ለግል ጥቅሙ ማዋል የለበትም፡፡
ስጦታ፣ መስተንግዶና የጉዞ ግብዣ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የመወሰን ሥልጣኑን የሚፈታተን ወይም የጥቅም ግጭት የሚፈጥር ስጠታ፣ መስተንግዶ ወይም የጉዞ ግብዣ መቀበል የለበትም፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ የተደነገገው ቢኖርም የቀረበለትን ስጦታ፣ መስተንግዶ ወይም የጉዞ ግብዣ ያለመቀበል በስራ ግንኙነት ላይ ጉዳት የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ ስጦታውን፣ መስተንግዶውን ወይም የጉዞ ግብዣውን ለመቀበል ይችላል፡፡ ሆኖም የተቀበለውን ስጦታ አግባብ ላለው የመንግሥት መሥሪያ ቤት ወይም የልማት ድርጅት ገቢ ማድረግ ወይም መስተንግዶውን ወይም የጉዞ ግብዣውን ለኮሚሽኑ ወይም አግባብ ላለው የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ማሳወቅ አለበት፡፡
የጥቅም ግጭትን ለማስወገድ መወሰድ ስላለበት እርምጃ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ በመንግሥት የሥራ ሃላፊነቱና በራሱ ወይም በቅርብ ዘመዱ የግል ጥቅም መካከል ግጭት ሊያስከትልበት የሚችል ጉዳይ ሲያጋጥመው፡-
በጉዳዩ ላይ ውሳኔ ወይም አስተያየት ከመስጠት እንዲሁም ከኃላፊነቱ ጋር የማይጣጣም ወይም ታማኝነቱን ጥርጣሬ ውስጥ የሚጥል ማንኛውንም ድርጊት ከመፈጸም መቆጠብ፣ እና
ሁኔታውን ለሚመለከተው የበላይ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ መሠረት የጥቅም ግጭት ሊከሰት መቻሉ የተገለጸለት የበላይ ኃላፊ እንደሁኔታው ተሿሚው፣ ተመራጩ ወይም የመንግሥት ሠራተኛው ጉዳዩን ማየቱን እንዲቀጥል መመሪያ ሊሰጠው ወይም ሌላ ሰው ተተክቶ እንዲያየው ሊያደርግ ይችላል።
የጥቅም ግጭት መከሰቱን ተከትሎ ስለሚወሰድ እርምጃ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ በመንግሥት የሥራ ሃላፊነቱና በራሱ ወይም በቅርብ ዘመዱ የግል ጥቅም መካከል ግጭት መከሰቱን ተከትሎ በራሱ ተነሳሽነት ወይም በበላይ ኃላፊው ሲጠየቅ ጥፋተኛ መሆኑን በይፋ አምኖ ይቅርታ የመጠየቅ ወይም ራሱን ከኃላፊነት የማግለል ግዴታ አለበት፡፡
ከሥራ መልቀቅ በኋላ ስለሚኖር ክልከላ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ሥራ በለቀቀ እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ሲቆጣጠራቸው ከነበረው ሰዎች ጋር ጥቅም የሚያስገኙ ሥራዎች መሥራት የለበትም፡፡ ዝርዝሩ በደንብ እና /ወይም/ በመመሪያ ይገለጻል፡ ፡
የጥቅም ግጭትን የማሳወቅ ግዴታን ስላለመወጣት
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የጥቅም ግጭት መኖሩን በዚህ አዋጅ መሠረት የማሳወቅ ግዴታውን ካልተወጣ አግባብ ባለው የሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት ተገቢው አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስድበታል።
ክፍል አራት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
ጥቆማ ስለማቅረብ
ማንኛውም ሰው ይህንን አዋጅ ጥሷል በሚለው ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ላይ ጥቆማ ማቅረብ ይችላል።
ጥቆማው እስከተቻለ ድረስ ከደጋፊ ማስረጃ ጋር በፅሁፍ ለኮሚሽኑ ወይም አግባብ ላለው የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ይቀርባል፡፡
በቀረበው ጥቆማ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የምርመራ ሂደቱና መዛግብቱ በሚስጥር ተይዘው ይቆያሉ።
በዚህ አንቀጽ መሠረት በቀረበ ጥቆማ የተገኘው መረጃ በወንጀል ህግ አንቀጽ 419(2) የሀብት መወረስ ውሳኔ ለማሰጠት ካስቻለ የተወረሰው ሀብት ከሚያስገኘው ገቢ ውስጥ 25 በመቶ ለጠቋሚው ይከፈላል።
የአዋጁን ተፈጻሚነት ስለማረጋገጥ
ማንኛውም የመንግስት መስርያ ቤት ወይም የመንግስት የልማት ድርጅት የዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች በስራ ላይ መዋላቸውን ለማረጋገጥ፡-
ተሿሚዎች፣ ተመራጮችና የመንግስት ሠራተኞች ሀብታቸውን በወቅቱ እንዲያስመዘግቡ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፤
አግባብ ያላቸው የስነ-ምግባር ደንቦችን አውጥቶ ተፈጻሚ ያደርጋል፡፡
ቅጣት
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ፡-
ሀብቱን በዚህ አዋጅ መሠረት ለምዝገባ ሳያሳውቅ ከቀረ ወይም ሆን ብሎ ትክክል ያልሆነ የምዝገባ መረጃ ከሰጠ፣ ወይም
የዚህን አዋጅ ድንጋጌዎች በመተላለፍ ስጦታ፣ መስተንግዶ ወይም የጉዞ ግብዣ ከተቀበለ ወይም የተቀበለውን ስጦታ፣ መስተንግዶ ወይም የጉዞ ግብዣ ሳያሳውቅ ከቀረ፣
በወንጀል ሕግ አንቀጽ 417 መሠረት ይቀጣል።
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ ማንኛውም ሰው በዚህ አዋጅ አንቀጽ 20 መሠረት ለኮሚሸኑ ወይም ለሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ጥቆማ አቅርቧል ወይም ምስክርነት ሰጥቷል ወይም ጥቆማ ለማቅረብ ወይም ምስክርነት ለመስጠት ተዘጋጅቷል በሚል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የበቀል እርምጃ የወሰደ እንደሆነ በወንጀል ህግ አንቀጽ 444 መሠረት ይቀጣል።
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ የጥቅም ግጭት መኖሩን ሳያሣውቅም ሆነ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 16 ንዑስ አንቀጽ /2/ መሠረት ተፈቅዶለት ሲሠራ የመንግሥት ኃላፊነቱን ተጠቅሞ የራሱን ወይም የቅርብ ዘመዱን የግል ጥቅም ያራመደ እንደሆነ አግባብ ባለው የወንጀል ህግ ድንጋጌ መሠረት ይቀጣል።
ማንኛውም ሰው በክፉ ልቦና በመነሳሳት ምንም ዓይነት መሠረት የሌለው ጥቆማ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 20 መሠረት ካቀረበ እስከ ሦስት ዓመት ሊደርስ በሚችል እሥራት ወይም እስከ ብር 2,000 ( ሁለት ሺ) በሚደርስ መቀጮ ወይም በሁለቱም ይቀጣል።
ተፈጻሚነት ስለማይኖራቸው ሕጐች
ከዚህ አዋጅ ጋር የሚቃረን ህግ ወይም ማንኛውም ልማዳዊ አሰራር በዚህ አዋጅ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት አይኖረውም።
ደንብና መመሪያ የማውጣት ሥልጣን
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህን አዋጅ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ ደንቦችን ሊያወጣ ይችላል።
ኮሚሽኑ ይህንን አዋጅና በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ መሠረት የወጡ ደንቦችን ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን ሊያወጣ ይችላል።