የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርህ እና ስርዓትአስተዳደራዊ ውሳኔ ምንድነው?


የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርህ እና ስርዓት
አስተዳደራዊ ውሳኔ ምንድነው?

‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ በአስተዳር ህግ ውስጥ ከቃል አጠቃቀም፣ ከይዘትና ከወሰን አንጻር ቁርጥ ያለ መደብ ከሌላቸው ፅንሰ ሀሳቦች መካከል ጎልቶ ይወጣል። ውስብስብነቱ ከፅንሰ ሀሳቡ ወካይ ስያሜ ይጀምራል። ‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ በሚል እዚህ ላይ መጠቀሱም በአገራችን የአስተዳደር ህግ ውስጥ መደበኛ መጠሪያው ቢሆን ይበጃል በሚል ብቻ ነው። ጀርመኖች እንኳን የራሳቸውን ወካይ ቃል መፍጠር ተስኗቸው አሁን ላይ በአስተዳደር ህጋቸው ዐቢይ ስፍራ ይዞ የሚገኘውን ‘Administrative act’ (Verwaltungsakt) በሚል የሚጠሩትን ፅንሰ ሀሳብ ለማዳበር ከፈረንሳዮች acte administrative ለመዋስ ተገደዋል።
‘Administrative act’ (Verwaltungsakt) is a core concept of the German administrative law. It covers most of the actions of the administrative authorities through which they affect the legal interests of an individual. The origin of this concept is traced from the French concept of acte administratif from which it was borrowed by the German jurists and developed into a German concept since 1826 onwards.a
በእንግሊዝኛው ፍቺ ከወሰድነው Administrative Decision በይዘቱ Administrative Act ውስጥ የሚጠቃለል ሲሆን ዘርፈ ብዙ መልክ ካላቸው አስተዳደራዊ ተግባራት መካከል አንድ ነጠላ ተግባርን ብቻ ይወክላል። ሆኖም ለአገራችን የአስተዳደር ህግ ‘አስተዳደራዊ ተግባር’ ወይም ‘አስተዳደራዊ ድርጊት’ የሚለውን ቃል ብንጠቀም ገላጭነቱ አይጎላም። ከዚህ በተጨማሪ አስተዳደራዊ ድንጋጌ ማውጣት እንዲሁም ምርመራ፣ ቁጥጥርና ክትትል ሁሉም የአስተዳደር ተግባራት እንደመሆናቸው ዳኝነታዊ ባህርይ ያላቸውን ተግባራት ለይቶ ለማመልከት ውስን ይዘት ያለውን ቃል መጠቀም ያስፈልጋል።

ከዚህ አንጻር በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ‘የአስተዳደር ውሳኔ’ ወይም ‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ የሚለው ቃል ዳኝነታዊ ባህርይ ያላቸውን ተግባራት ለመግለጽ ጥቅም ላይ ውሏል። ሆኖም በመደበኛ ትርጓሜው አደናጋሪ መልዕክት ስለሚፈጥር ይዘቱንና ፍቺውን በቅድሚያ መወሰን ያስፈልጋል።
እ.ኤ.አ. በ1976 ዓ.ም. በወጣው የጀርመን የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ የአስተዳደር ተግባር (Administrative act) የሚከተለው ፍቺ ተሰጥቶታል።
Administrative act is every order, decision or other sovereign measure taken by an authority for the regulation of a particular case in the sphere of public law and directed at immediate external legal consequences.b
ወደ አማርኛ ስንመልሰው፤
የአስተዳደር ተግባር ማለት ቅርብና ውጫዊ የህግ ውጤት የሚያስከትል በህዝብ አስተዳደር ህግ ማዕቀፍ ውስጥ አንድን ልዩ ሁኔታ ለመቆጣጠር ሲባል ስልጣን ያለው አካል የሚሰጠው ትዕዛዝ፣ ውሳኔ ወይም ሌላ ማናቸውም ሌላ ሉዓላዊ እርምጃ ነው።
በትርጓሜው ውስጥ ተጨማሪ ሰፊ ማብራሪያ የሚሹ ንዑስ ሀሳቦች ታጭቀዋል። ሆኖም በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል በጀርመን የአስተዳደር ህግ የአስተዳደር ተግባር ማለት ህግ ለማስፈጸምና የአስተዳደር ስራ ለማከናወን ስልጣን የተሰጣቸው ተቋማት ይህን ህዝባዊ ስልጣናቸውን (public functions) በመገልገል የሚሰጡትን ትዕዛዝ፣ ውሳኔ ወይም ማናቸውም በማድረግ፣ ባለማድረግ የሚገለጽ እርምጃ ሁሉ ያጠቃልላል። ይህም ማለት በውል ወይም ከውል ውጪ ኃላፊነት ህጎች ስር የሚሸፈኑ ግላዊ ድርጊቶች፣ ውሳኔዎች፣ እርምጃዎች ወዘተ…በአስተዳደር ተግባር ስር አይሸፈኑም።
በትርጓሜው ላይ ‘ልዩ ሁኔታ ለመቆጣጠር’ ሲባል ተግባሩ ህጋዊ ውጤት እንደሚያስከትል ወሰኑም በአንድ ልዩ ሁኔታ ላይ ያነጣጠረ እንጂ ጠቅላላ ተፈጻሚነት እንደሌለው ያመለክታል። ስለሆነም የበታች ሠራተኛ ለበላይ ኃላፊ የሚያቀርበው የውሳኔ ሀሳብ፣ ሪፖርት ወይም የምርመራ ውጤት ራሱን ችሎ ህጋዊ ውጤት የማይከተለው በመሆኑ እንደ አስተዳደራዊ ተግባር አይቆጠርም። በአንድ ዘርፍ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ የተወሰደ እርምጃ (ለምሳሌ ስጋ ሻጮች ማሟላት ያለባቸው የጥራት ደረጃ) ከላይ በተቀመጠው ትርጓሜ ውስጥ አይወድቅም። ምክንያቱም ተፈጻሚነቱ ሁሉንም የዘርፍ ነጋዴዎች ስለሚያቅፍ ጠቅላላነት ይታይበታል። በመጨረሻም ህጋዊ ውጤቱ በአስተዳደሩ ውስጣዊ መዋቅር ተወስኖ የሚቀር (ለምሳሌ በአንድ ነጋዴ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የበላይ ኃላፊው ለበታች ሠራተኛ የሚያስተላልፈው ማሳሰቢያ) ከሆነ በአስተዳደራዊ ተግባር ውስጥ አይመደብም።
የአሜሪካው የፌደራል አስተዳር ስነ ስርዓት ህግ ተፈጻሚነቱ አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (rule making) እና አስተዳደራዊ ዳኝነት (adjudication) የመስጠት ሂደቶች ላይ ነው። በህጉ ላይ በተሰጠው ፍቺ አስተዳደራዊ ዳኝነት ማለት በውጤቱ ‘ትዕዛዝ’ የሚያቋቁም የአስተዳደር ሂደት (agency process for the formulation of an order) ነው። ትዕዛዝ የሚለው ቃል በአስተዳደር ስነ ስርዓት ህጉ ላይ ፍቺ የተሰጠው ሲሆን ይዘቱ እንደሚከተለው ይነበባል።
order means the whole or a part of a final disposition, whether affirmative, negative, injunctive, or declaratory in form, of an agency in a matter other than rule making but including licensing.c
‘ትዕዛዝ’ ከጀርመኑ ‘የአስተዳደር ተግባር’ ጋር ሲነጻጸር መሰረታዊ ልዩነት አይታይበትም። ጉዳዩን የሚቋጭ የመጨረሻ መሆኑ ህጋዊ ውጤት እንደሚከተለው ይጠቁመናል። በይዘቱ አንድ ድርጊት እንዳይፈጸም፣ እንዲፈጸም ወይም የአንድ ሁኔታ (መብት) መኖር/አለመኖር የሚያረጋግጥ መግለጫ ወይም ከአስተዳደራዊ ድንጋጌ ማውጣት ውጪ ያለ ማንኛውም የመጨረሻ እልባት የሚሰጥ ነው።
በመቀጠል የአገራችን የፌደራል ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ (1993) የተጠቀመውን ቃል እና አፈታቱን እናያለን። በረቂቅ አዋጁ የትርጓሜ ክፍል አንቀጽ 2 /2/ እንደተመለከተው አስተዳደራዊ ውሳኔ ማለት፤
ማናቸውም አስተዳደራዊ ባህርይ ያለውን ተግባር ወይም ነገር ከመፈጸም ጋር የተያያዘ ውሳኔ ወይም ውሳኔ አለመስጠትን ጨምሮ ቅጣትን ለመጣል፣ ወይም መፍትሔ ለመስጠት ወይም የመከላከል ዓላማ ወይም ውጤት ያለው በአስተዳደር ተቋማት የሚሰጥ ማናቸውም ውሳኔ፣ ትዕዛዝ ወይም ብይን [ነው።]
የትርጓሜውን ይዘት ይበልጥ ለመረዳት የእንግሊዝኛውን ቅጂ መመልከቱ ጠቃሚ ነው።
Administrative Decision means any decision, order or award of an agency having as its object or effect the imposition of a sanction or the grant or refusal of relief, including a decision relating to doing or refusing to do any other act or thing of an administrative nature, or failure to take a decision
በቀጣይ በ2001 ዓ.ም. በተዘጋጀው ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ አዋጅ አርቃቂዎቹ የተለየ አገላለጽ መጠቀም መርጠዋል። በረቂቁ አንቀጽ 2/2/ ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንደሚከተለው ተተርጉሟል።
አስተዳደራዊ ውሳኔ ማለት ተጨባጭ ሕጋዊ ግንኙነቶችን ለመመስረት፣ ለማሻሻል፣ በምርመራ ለማረጋገጥ ወይም የተሟላ ለማድረግ ለአንድ ጉዳይ የተወሰነ መፍትሔ የመስጠት ዓላማ ያለውና በግለሰብ ወይም በተወሰኑ ሰዎች ላይ ተፈጻሚነት ያለው በተቋሙ የሚሰጥ ሕጋዊ ውሳኔ ሲሆን፣ አስተዳደራዊ ባህርይ ባለው ተግባር ወይም ጉዳይ ላይ ውሳኔ አለመስጠትንም ይጨምራል።
በሁለቱም ረቂቆች ላይ የሚታየው ገላጭነት የጎደለው የቋንቋ አጠቃቀም አብዛኛው ሰው በቀላሉ አይረዳውም። ከዚህም አልፎ የህግ ባለሞያዎች፣ ዳኞች እና አስተዳዳሪዎች በጋራ የሚያግባባ አገላለጽ አልያዘም። ለምሳሌ በተለምዶ ሰርኩላር በሚል ስያሜ ጠቅላላ ተፈጻሚነት ኖሯቸው የሚተላፉ ትዕዛዞች የአስተዳደራዊ ውሳኔና የአስተዳደራዊ ድንጋጌ ከፊል ባህርያት ይጋራሉ። ሆኖም በአንደኛው ስር ለመፈረጅ ሁለቱም ትርጓሜዎች ግልጽ መለያ መስፈርት አላካተቱም። ለአስተዳደራዊ ውሳኔ ትርጓሜ ለማበጀት ጥሩ መነሻ የሚሆነው የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው። ሁለቱን የሚያመሳስላቸው ብዙ ነጥቦች አሉ። አስተዳደራዊ ሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሁለቱም ምንጫቸው ዳኝነታዊ ስልጣን ነው። በዳኝነት ፍሬ ነገሩን የማረጋገጥና በተረጋገጠው ፍሬ ነገር ላይ ህጉን ተፈጻሚ የማድረግ ተግባራት ይከናወናሉ። ዓላማው አከራካሪ የሆነ አንድ ተለይቶ የታወቀ ጉዳይ (particular case) መቋጨት ነው። ጉዳዩን በመቋጨት የሚነገረው ትዕዛዝ፣ ብይን ወይም ውሳኔ በባለጉዳዮች ወይም ሶስተኛ ወገኖች ላይ ህጋዊ ውጤት ያስከትላል። እነዚህ ወሳኝ ባህርያት በጀርመኑ እና የአሜሪካው የአስተዳደር ህጎች ላይ በግልጽ ተለይተዋል።
የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ ቁ. 1183/2012 ለአስተዳደር ውሳኔ ፍቺ የሰጠበት መንገድ የቀድሞዎቹን ረቂቆች ችግር ከማስተካከል ይልቅ የባሰ ተጨማሪ ችግሮች ይዞ መጥቷል። በአንቀጽ 2/3/ ላይ ትርጓሜው እንደሚከተለው ይነበባብል።
የአስተዳደር ውሳኔ ማለት መመሪያ ማውጣትን ሳይጨምር የአስተዳደር ተቋም በዕለት ተዕለት ተግባሩ በሰዎች መብት ወይም ጥቅም ላይ የሚሰጠው የአስተዳደር ውሳኔ ነው።
የትርጓሜ አለአግባብ መለጠጥ ከሞላ ጎደል ሁሉንም ከመመሪያ ማውጣት ያሉ የአስተዳደር ተግባራት በትርጓሜው ስር እንዲወድቁ አድርጓቸዋል። ምንም እንኳን በአቀራረቡ የአሜሪካውን የአስተዳደር ስነ-ስርዓት የተከተለ ቢመስልም በአዋጁ ውሳኔዎች አዎንታዊ መልክ ብቻ እንዲኖራቸው ነው የተደረገው። ለምሳሌ ተቋሙ ‘የማይሰጠውን ውሳኔ’ ማለትም ግዴታን አለመወጣት በትርጓሜው ላይ አይነበብም።
በአንድ የአስተዳደር መ/ቤት የተፈጸመ ተግባር የአስተዳደር ውሳኔ ነው ወይስ አይደለም? የሚለው ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ውስጥ መሰረታዊ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ነው። ጥያቄው ተቋሙ ካሉት ጠቅላላ የማስተዳደር (ህግ ማስፈጸም)፣ ከፊል የህግ አውጭነት እና ከፊል የዳኝነት ስልጣናት መካከል የትኛውን እየተገለገለ እንደሆነ የሚለይበት ነው። የጥያቄው ሌላ መልክ ሲታይ ተቋሙ የፈጸመው ተግባር በባህርዩ ዳኝነታዊ ነው ወይስ አይደለም? የሚለውን ጥያቄ ይመልሳል። የውሳኔ ሰጭውን የስልጣን እና የተግባር ዓይነት መለየት በህጉ የአፈጻጸም ወሰን ላይ የራሱ ጉልህ እንደምታዎች አሉት። ጠቅለል ባለ አነጋገር የአስተዳደር መ/ቤቶች ዳኝነታዊ ወይም የህግ አውጭነት ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ጊዜ ካልሆነ በስተቀር ሙሉ በሙሉ በአስተዳደር ስልጣን ውስጥ የሚወድቁት ድርጊቶች በመደበኛ ፍ/ቤቶች ቁጥጥር ሊደረግባቸው አይችልም። በሌላ አነጋገር አስተዳደራዊ ውሳኔ ወይም ድንጋጌ ባልሆነ ጉዳይ ላይ የአጣሪ ዳኝነት ስልጣን አይኖራቸውም። የአስተዳደር መ/ቤቶች ዳኝነታዊ ስልጣናቸውን ተጠቅመው አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሰጡ መሰረታዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎች ተፈጻሚ መሆን ይጀምራሉ።
የፍትሐዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎች
ከስነ-ስርዓት አካሄድ አንጻር ውሳኔ ሰጪ የሆነ የመንግስት አካል በቅን ልቦና ተመርቶ አድሎአዊ ያልሆነ ውሳኔ መስጠትና ከሁሉም በላይ በውሳኔው መብቱ ወይም ጥቅሙ ሊነካ ለሚችል ለማንኛውም ግለሰብ ከውሳኔው በፊት የመሰማት መብቱን ሊጠብቅለት ይገባል።
የአስተዳደር ውሳኔ ፍትሐዊነት በዋነኛነት ሁለት መሰረታዊ መርሆዎችን ያቅፋል። አንደኛው የመሰማት መብት ሲሆን (The right to fair hearing) በላቲን audi alteram partem ተብሎ ሲጠራ አንዳንዴ ‘ተቃራኒውን ወገን ሰማው’ ወይም ‘ማንም ሰው መከላከያው ሳይሰማ እርምጃ ሊወሰድበት አይገባም’ (no one should be condemned unheard) በሚል ይገለጻል።d
ሁለተኛው የኢ-አድሎአዊነት መርህ (The rale against bias) ነው። በላቲን nemo judex in causa sua የሚለውን የህግ አባባል / legal maxim/ ይወክላል። ወደ አማርኛው ስንመልሰው ‘አንድ ሰው በራሱ ጉዳይ ራሱ ዳኛ ሊሆን አይገባም’ የሚል መልዕክት አለው።e በእንግሊዝ እነዚህ ሁለት መርሆዎች ‘የተፈጥሮ ፍትሕ’ የሚባለውን በዳኞች የዳበረ ፅንሰ ሀሳብ የሚወክሉ ሲሆን የህጉ የመሰረት ድንጋይ ተደርገው ይቆጠራሉ።
የመሰማት መብት
በተከሰሰበት ጉዳይ መልስ ሳይሰጥ እንዲሁም ማስረጃውን ሳያሰማ የንግድ ፍቃዱ የተሰረዘበት ነጋዴ፣ የቤት ካርታው የመነከበት ግለሰብ፣ ከዩኒቨርሲቲ የተባረረ ተማሪ… ሁሉም የአስተዳደር በደል ሰለባዎች ናቸው። የአንድን ግለሰብ መብትና ጥቅም ሊጐዳ የሚችል ማንኛውም አስተዳደራዊ እርምጃ ከመወሰዱ በፊት ግለሰቡ የመሰማት ዕድል ሊያገኝ ይገባል። የመሰማት መብት በዘፈቀደ በሚወሰድ አስተዳደራዊ እርምጃ የተነሳ ዜጎች ህይወታቸውና ንብረታቸው ለአደጋ እንዳይጋለጥ ይከላከላል።
መሰማት ሲባል ከክስ እስከ ውሳኔ ድረስ ያሉ ዝርዝር የክርክር ሂደቶችን ያቅፋል። እያንዳንዱ ሂደት በራሱ ካልተሟላ በቂ የመሰማት ዕድል እንዳልተሰጠ ይቆጠራል። በአስተዳደር ዳኝነት ውስጥ የዚህ መብት ዝርዝር ሂደቶችና አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች በዋነኛነት የሚከተሉትን ያካትታል።

ቅድመ-ክስ ማስታወቂያ

የክስ መሰማት ውሳኔ ሰጭው ባለስልጣን ለባለጉዳዩ /ለተከሳሹ/ በሚሰጠው የክስ ማስታወቂያ ይጀመራል። ማስታወቂያ ተከራካሪው እንዲቀርብ የሚሰጥ መጥሪያ ነው። በይዘቱ ባለጉዳዩ የቀረበበትን ክስ በሚገባ ተረድቶ መልሱን አዘጋጅቶ እንዲያቀርብ የሚያስችለው በቂ ማስታወቂያ መሆን አለበት። ተከራካሪው ራሱን ለመከላከል የሚችለው የተከሰሰበትን ጉዳይ በማያሻማ ሁኔታ የተገለጸለት እንደሆነ ነው።f ከዚህ አንጻር የክሱ ዓይነትና ምክንያት ቀጥተኛና ግልጽ በሆነ መንገድ በማስታወቂያው ላይ መስፈር ይኖርበታል። ለምሳሌ እንዲቀርብ የተጠራው ባለጉዳይ የመንግስት ሰራተኛ ወይም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆነ በደፈናው ‘የዲሲፕሊን ክስ ስለቀረበብህ እንድትቀርብ!’ የሚል መጥሪያ ግልጽነት ይጐድለዋል። በተጨማሪም ከአንድ በላይ ክስ በቀረበ ጊዜ እያንዳንዱ ክስ በዝርዝር ሊገለጽ ይገባል። በሌላ መልኩ በክስ ማስታወቂያው ላይ የቀረበው የክስ አይነት ክሱ በሚሰማበት ቀን የተቀየረ እንደሆነ ክሱ እንዳልተገለጸ ወይም በቂ ማስታወቂያ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል። በስርቆት ተከሶ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ፊት እንዲቀርብ የተጠራ ተማሪ ክሱ በሚሰማበት ቀን የመጀመሪያው ክስ ተቀይሮ ‘በፈተና ማጭበርበር’ ተከሶ ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ ተማሪው የተቀጣው በቂ ማስታወቂያ ሳይሰጠው እንደመሆኑ ቅጣቱ መሰረታዊ የሆነውን የመሰማት መብት ይጻረራል።
ክሱ የሚሰማበት ጊዜና ቦታ
‘በቂ’ ሊባል የሚችል የክስ ማስታወቂያ መለኪያ ባለጉዳዩ ራሱን በሚገባ እንዲከላከል በሚያስችል መልኩ በቂ መረጃና ጊዜ የሰጠ እንደሆነ ነው። ክርክሩን ለማካሄድ ስልጣን የተሰጠው አካል ተከራካሪዎች የሚመቻቸውን ጊዜ በመወሰን ክሱ ስለሚሰማበት ቦታ ትክክለኛ መረጃ እንዲኖራቸው በሚያስችል መልኩ መጥሪያውን መላክ ይጠበቅበታል። ጊዜው ሲገለጽ ትክክለኛው ሰዓት ጭምር መገለጽ አለበት። ቦታውም እንዲሁ ትክክለኛ መለያ አድራሻውን በመጥቀስ ለባለጉዳዩ/ለተከሳሹ በግልጽ ማሳወቅ ያስፈልጋል።
ከጊዜ ጋር በተያያዘ መልስ ለማቅረብ የሚሰጠው የዝግጅት ጊዜ እንደክሱ ክብደትና ውስብስብነት ሚዛናዊ የጊዜ መጠን መሆን ይኖርበታል። ዛሬ ክሱ ተሰጥቶት ለነገ መልስ መጠበቅ በተዘዋዋሪ የመሰማት መብትን እንደመንፈግ ይቆጠራል። በመጨረሻም ክሱን የሚሰማው አካል ትክክለኛ ማንነት በማስታወቂያው ላይ መመልከት ይኖርበታል።
የክስ ማስታወቂያ በአካል ስለመስጠት
የጥሪ ማስታወቂያው በይዘቱ በቂ ሊባል የሚችል ቢሆንም ለባለጉዳዩ በአግባቡ እስካልዳረሰው ድረስ የመሰማት መብቱ ተጓድሏል። ባለጉዳዩ በቅርብ የሚገኝ ከሆነ በተቻለ መጠን መጥሪያው ለራሱ በአካል ሊሰጠው ይገባል። ከተገቢ ጥረት በኋላ ለማግኘት የማይቻል ከሆነ ማስታወቂያውን ቅርብ በሆነ ቦታ ላይ መለጠፍና ለተወሰነ ጊዜ በተለጠፈበት ቦታ እንዲቆይ ማድረግ ያስፈልጋል። ጉዳዩ በሚሰማበት ቀን አለመቅረብ ክርክሩ በሌለበት እንዲቀጥል የሚያደረግ በመሆኑ የመጥሪያ በአግባቡ መድረስ የመስማት መብት አካል ተደርጐ መቆጠር ይኖርበታል።ክርክርና ማስረጃ የማቅረብ መብት
ክስ የቀረበበት (ባለጉዳይ) ጉዳዩ በተቀጠረበት ቀን በአካል ወይም በወኪሉ ተገኝቶ ክርክሩን የመከታተል፤ መልስ፣ ክርክርና ማስረጃ የማቅረብ ዕድል ሊያገኝ ይገባል። ይህ መፈጸሙን ማረጋገጥ ክርክሩን የሚሰማው አካል ግዴታ ነው። መልሱ የሚቀርብበት መንገድ እንደየሁኔታው በቃል ወይም በጽሑፍ ሊሆን ይችላል። የሚቀርበው የማስረጃ ዓይነት የቃል (የሰው ምስክር) ወይም የጽሑፍ ማስረጃ ሊሆን ይችላል። ማስረጃው በ3ኛ ወገን እጅ የሚገኝ ከሆነ ባለጉዳዩ እንዲቀርቡለት በጠየቀ ጊዜ ክርክሩን የሚሰማው አካል እንዲቀርቡ ማድረግ አለበት።
መስቀለኛ ጥያቄ የማቅረብ መብት
ባለጉዳዩ የተቃራኒ ወገን ክስና ማስረጃ በአግባብ ሊደርሰውና ሊመለከተው እንደሚችል ከዚህ በፊት ተገልጿል። የዚህ ዓላማ በአንድ በኩል ባለጉዳዩ የራሱን መከራከሪያና ማስረጃ በማቅረብ ክሱን በቀጥታ እንዲከላከል ሲሆን በሌላ በኩል የተቆጠረበትን ማስረጃ ማስተባበል እንዲያስችለው ጭምር ነው።
በፍርድ ቤት በሚካሄድ መደበኛ ክርክር መስቀለኛ ጥያቄ የምስክሮችን ተዓማኒነት ለማሳጣትና በአጠቃላይ እውነትን ለማውጣት ውጤታማ መሳሪያ ነው። ተከሳሹ መስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብ ዕድሉ ተነፍጐት የተሰጠ የምስክርነት ቃል ህጋዊ ብቃቱም አጠያያቂ ነው። ያም ሆኖ ግን የአስተዳደር ክርክር በዓይነቱና በይዘቱ የፍርድ ቤት ክርክር መልክ ከያዘ ውጤታማ አስተዳደርን ወደ ኋላ መጎተቱ አይቀርም። ስለሆነም የመስቀለኛ ጥያቄ መቅረት ባለጉዳዩ ውጤታማ መከላከያ እንዳያቀርብ የሚያግደው ካልሆነ በስተቀር ውሳኔ ሰጭው አካል በመብቱ ላይ ገደብ ሊያደርግ ይችላል።g ይሁን እንጂ ምስክርነቱ በቃለ መሀላ ስር የተሰጠ ከሆነ መስቀለኛ ጥያቄ መከልከል አይገባም። በዚህ ረገድ የ1967ቱ ረቂቅ አዋጅ መስቀለኛ ጥያቄ የማቅርብ መብት ለባለጉዳዩ የሚፈቅድ ግልጽ ድንጋጌ የለውም። በተቃራኒው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ (1993) በአንቀጽ 6 (3)(ሐ) ላይ ይህን መብት በግልፅ አካቷል።
የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁ. 1183/2012 በደፈናው ‘ማስረጃ ስለመመርመር’ ቢናገርም በግልጽ ባለጉዳዩ መስቀለኛ ጥያቄ የመጠቅ መብት ያለው ስለመሆኑ አያመለክትም። ባለጉዳዩ ለተቋሙ የቀረቡ ማስረጃዎችን የመስማትና የመመርመር መብት የአንቀጽ 37/1/ ሐ አነጋገር መብቱ ከጽሑፍ ማስረጃ ጋር ብቻ የተቆራኘ የሚመስል ይዘት አለው። በተጨማሪ ‘ለተቋሙ የቀረቡ’ የሚለው አገላለጽ አደናጋሪ ነው።
በአስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ መስቀለኛ ጥያቄ የማቅረብ መብት ከሞላ ጎደል በሁሉም ህጎችቻን ላይ አልተካተተም። ልዩ ሁኔታ የሚገኘው በፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ 847/2006 ላይ ነው። በአንቀጽ 39/2/ እንደተመለከተው የዲሲፕሊን ክስ የቀረበበት ሰው የከሳሽን ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ መብት ይኖረዋል። የመንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን ክስ በሚሰማበት ወቅት እንዲሁ ግራ ቀኙ መስቀለኛ ጥያቄ ማቅረብ ተፈቅዶላቸዋል። በፌደራል መንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ ስርዓት ደንብ ቁ. 77/1994 አንቀጽ 17/5/ እንደሰፈረው የከሳሽ ምስክሮችን ተከሳሹ፤ የተከሳሽ መከላከያ ምስክሮችን የመንግስት መስሪያ ቤቱ ተወካይ፤ የዲሲፕሊን ኮሚቴው የጠራቸውን ተጨማሪ ምስክሮች ደግሞ ሁለቱም ተከራካሪ ወገኖች መስቀለኛ ጥያቄ መጠየቅ ይችላሉ።
በጠበቃ ተወክሎ የመከራከር መብት
የባለጋራን ክስና ማስረጃ ለማስተባበል የህግ ባለሙያ እገዛ አስፈላጊነቱ አያጠያይቅም። በተለይ ውስብስብ በሆኑ የአስተዳደር ክርክሮች ተካፋይ የሆነ ወገን ካለባለሙያ እገዛ ራሱን በውጤታማ መንገድ ለመከላከል ያለው ዕድል አነስተኛ ነው። ሆኖም በጠበቃ መወከል መሰረታዊ የመሰማት መብት አካል ተደርጐ አይቆጠርም። በመብቱ ላይ የሚጣለው ገደብ የራሱ አሳማኝ ምክንያቶች አሉት።
የአስተዳደራዊ ዳኝነት ክርክር ጥብቅ የሆነ የመደበኛ ፍ/ቤቶች ዓይነት የስነ-ስርዓት አካሄድ ሳይከተል በፍጥነት ጉዳዩን ለመቋጨት ያለመ ነው። የጠበቃ መኖር ክርክሩ የባሰ እንዲወሳሰብና ከተገቢው ጊዜ በላይ እንዲንዛዛ በማድረግ የክርክሩን ኢ-መደበኛ ባህርይ ያጠፋዋል። በአጠቃላይ አነጋገር በጠበቃ ውክልና ከሚታገዝ ይልቅ ባለጉዳዩ ራሱ የሚከራከርበት አስተዳደራዊ ክርክር በአጭር ጊዜ እልባት ያገኛል። ያም ሆኖ ግን ክርክር የሚካሄድበት ጉዳይ በባሉጉዳዩ መብትና ጥቅም ላይ ሊኖረው ከሚችለው አሉታዊ ውጤት አንጻር ማለትም የክርክሩን ክብደትና ውስብስነት መሰረት አድርጐ እንደየሁኔታው በጠበቃ የመወከል ጥያቄን ማስተናገድ ያስፈልጋል።
ምክንያታዊ ውሳኔ
ዜጐች በሰውነታቸውና በንብረታቸው ላይ እርምጃ ሲወሰድ ከመንግስት ምክንያት ይሻሉ። አንዳችም ምክንያት የሌለው ውሳኔ የአስተዳደር በደል መገለጫ ነው። ኢ-ፍትሐዊነት በሁለት መልኩ ይገለጻል፤ የመጀመሪያው ምክንያት ሳይጠቀስ በደፈናው ውሳኔ ሲሰጥ፣ ሁለተኛው ደግሞ ውሳኔው በራሱ ፍርደገምድል፣ ሚዛናዊነት የጐደለውና በአሳማኝ ምክንያት ያልተደገፈ ሲሆን።
ለውሳኔ ምክንያት መስጠት በአስተዳደር ህግ ውስጥ ጉልህ ስፍራ እያያዘና እያደገ የመጣ መሰረተ ሀሳብ ነው። ያም ሆኖ ከአሜሪካው የአስተዳደር ስነስርዓት በስተቀር በእንግሊዝ ሆነ በህንድ ምክንያት እንዲሰጥ የሚያስገድድ በሁሉም የአስተዳደር አካላት ተፈጻሚ የሆነ ጠቅላላ ደንብ የለም። ሆኖም አልፎ አልፎ ማቋቋሚያው አዋጅ ለአስተዳደራዊ ውሳኔ ምክንያት እንዲሰጥ ቅድመ ሁኔታ ያስቀምጣል።
አስተዳደራዊ ውሳኔ ሊኖረው የሚገባውን ይዘትና ቅርጽ በተመለከተ በ1967 ረቂቅ አዋጅ አንቀጽ 13 እንዲሁም በፌደራሉ ረቂቅ አዋጅ (1993 ዓ.ም.) አንቀጽ 32 ላይ ቅድመ ሁኔታዎቹ ተዘርዝረዋል። በዚሁ መሰረት አስተዳደራዊ ውሳኔ በጽሑፍ መሰጠት ያለበት ሲሆን ውሳኔውም የክርክሩን ፍሬ ነገር፣ የማስረጃዎች ፍሬ ጉዳይና ምንጭ፣ የነገሩን ጭብጥ አወሳሰን እንዲሁም በውሳኔው መሰረት ተመስርቶ ሊወሰድ ስለሚገባው እርምጃ የሚያመለክት መሆን ይኖርበታል። ምንም እንኳን በረቂቆቹ ላይ ‘ምክንያት’ የሚለው ቃል በግልጽ ባይጠቀስም የውሳኔ ምክንያትን የሚያያቋቁሙ ሁኔታዎች የተካተቱ እንደመሆኑ ምክንያት መስጠት እንደአስገዳጅ ሁኔታ ተቀምጧል ማለት እንችላለን።
ከረቂቆቹ ጋር ሲነጻጸር የአስተዳደር ስነ- ስርዓት አዋጁ የአስተዳደር ውሳኔ መያዝ ያለበትን ፍሬነግሮች የዘረዘረ ሲሆን ለውሳኔ በቂ ምክንያት መስጠትም እንደ አንድ መሰረታዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርህ አካቶታል። በመሆኑም የአስተዳደር ውሳኔ ሲሰጥ አብሮት በቂ ምክንያት ሊሰጥ ይገባል።h የአስተዳደር ውሳኔ ይዘት በተመለከተ በጽሑፍ ሆነ የሚከተሉትን መያዝ ይኖርበታል።
1-የውሳኔ ቀንና ቁጥር ፤
2-የተቋሙን ስም ፤
3-በክርክሩ ተካፋይ የሆኑ ወገኖችን አድራሻ፤
4-አከራካሪ ፍሬ ነገር፤
5-የማስረጃዎች ትንተና፤
6-የፍሬ ነገር እና የሕግ ትንታኔ፤
7-ውሳኔ
በአንዳንድ አዋጆች ላይ ውሳኔን በምክንያት ማስደገፍ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ ነው። ለአብነት የሚከተሉት ይጠቀሳሉ።
በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁ. 980/2008 አንቀጽ 6/2/ የንግድ ምዝገባ ማመልከቻ ውድቅ ከተደረገ መዝጋቢው አካል ምክንያቱን ገልጾ ለአመልካቹ ወዲያውኑ ማሳወቅ አለበት።
ከቀረጥ ዋጋ አወሳሰን ጋር በተያያዘ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ተጨማሪ መግለጫ ወይም ሰነድ ከዲክላራሲዮን አቅራቢው ከተቀበለ በኋላ ስለግብይት ዋጋው ትክክለኛነት ያለውን ጥርጣሬ ማስወገድ ካልቻለ ወይም ዲክላራሲዮን አቅራቢው ምላሽ ካልሰጠ በጉምሩክ አዋጅ ቁ. 859/2006 አንቀጽ 90 መሰረት ዋጋውን መወሰን እንዳልተቻለ ይቆጠራል። በዚሁ መሰረት የቀረበው የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ ተቀባይነት ያላገኘበት ምክንያት በጽሑፍ ለአስመጭው ወይም ለወኪሉ ይገለጽለታል።i
በነዳጅ አቅርቦት ስራ ለመሰማራት የተጠየቀ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ተቀባይነት ካላገኘ ምክንያቱ ለአመልካቹ ይገለጽለታል።j
የስደተኝነት ዕውቅና እንዲሰጥ የሚቀርብ አቤቱታ ተቀባይነት ቢያገኝም ባያገኝም ውሳኔው ለአቅራቢው በጽሑፍ መገለጽ አለበት።k
የኢ-አድሎአዊነት መርህ
ከአድልኦ የፀዳ ፍርድ (The rule against bias) የሚለው መርህ በኮመን ሎው አገራት በስፋት የዳበረ መሰረተ ሀሳብ ሲሆን በአጭሩ ሲገለጽ አንድ ሰው በራሱ ጉዳይ ራሱ ከሳሽ ራሱ ዳኛ መሆን የለበትም እንደማለት ነው። ኢ-አድሎአዊነት አብዛኛውን ጊዜ ራሱን የቻለ የተፈጥሮ ፍትህ መርህ ተደርጐ ቢጠቀስም በተግባር ሲታይ ግን በመሰማት መብት ውስጥ የሚጠቃለል የፍትሐዊ ስነ-ስርዓት አንድ አካል ነው። አንድ ሰው በአስተዳደር ጉባዔ (Administrative Tribunal) ፊት ቀርቦ የመሰማት እድል ሊሰጠው ይገባል ሲባል በውስጠ ታዋቂነት ፍ/ቤቱ ከአድልኦ የፀዳ እንደሆነ ግምት በመውሰድ ነው።
ፍርደ ገምድል ያልሆነ፤ ያልተዛባ ውሳኔ መኖር ህዝቡ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ያለውን አመኔታ የሚያንፀባርቅ እንደመሆኑ ተፈፃሚነቱም /በተለይ በኮመን ሎው አገራት/ እጅግ ጥብቅ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ የታወቁት የእንግሊዝ ዳኛ ሎርድ ሄዋርት እንዲህ ብለው ነበር።
ፍትህ መሰራቱ ብቻ በቂ አይደለም። ፍትህ ሲሰራ ጭምር በማያጠራጥርና ግልጽ በሆነ አኳኋን መታየት መቻል አለበት።
የዳኛው ልጅ ‘ቀማኛ’ ተብሎ በአባቱ ፊት ችሎት ሲቀርብ በእርግጥም በህጉ መሰረት ጥፋተኛ ላይሆን ይችላል። ጥፋተኛ ካልሆነ መለቀቁ ፍትህ ነው። ግን ለማንም አይመስልም። ፍትህ ሲሰራ አይታይምና። ዋናው ቁም ነገር ዝምድና፤ የገንዘብ ጥቅም ወይም ሌላ ምክንያት በዳኛው ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተጽእኖ አለማድረጉ አይደለም። እነዚህ ሁኔታዎች እስካሉ ድረስ ዳኛው ምንም ያህል ንፁህና ጻድቅ ሰው ቢሆን እንኳን በችሎት ላይ ተቀምጦ ሲያስችል አመኔታ ያጣል። የኢ-አድሎአዊነት መርህ ዋና አላማ ውሳኔ ሰጭው አካል የተዛባ ፍርድ እንዳይሰጥ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም ራሱም ሳያውቀው እንኳን በንፁህ ህሊናው ላይ ተፅእኖ ሊያደርሱ ከሚችሉ ሁኔታዎች ነጻ ሆኖ ዳኝነት እንዲሰጥ ለማስቻል ነው።
ይህ የኢ-አድሎአዊነት መርህ በተለይ በመደበኛ ፍ/ቤት፣ በአስተዳደር ጉባኤ እና ዳኝነታዊ ውሳኔ በሚሰጡ የአስተዳደር መ/ቤቶች ጥብቅ ተፈጻሚነት አለው። ውሳኔ ሰጪው አካል በያዘው ጉዳይ በህሊናው ላይ ተፅእኖ ሊያመጣ የሚችል ሁኔታ መኖሩን በተረዳ ጊዜ ራሱን ከውሳኔ ሰጪነት ማግለል አለበት። ይህ ባልሆነበት ጊዜ በቂ ጥርጣሬ ያደረበት ወገን አቤቱታ አቅርቦ ዳኛው እንዲቀየርለት ማመልከት ይችላል። ሁኔታው መኖሩ የታወቀው ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ ከሆነ የዛ ውሳኔ እጣ ፈንታ ዋጋ አልባ መሆን ነው።
አድሎአዊ ውሳኔ ተሰጥቷል የሚባለው የውሳኔ ሰጭው ህሊና የተዛባ እንደሆነ ነው፡ ለመሆኑ የሕሊና መዛባት ምን ማለት ነው?
በጥሬ ትርጉሙ ሲታይ ማንኛውም ነገር በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ውሳኔ ሰጭው በነጻ ህሊናው ተመርቶ ሊሰጥ ይችል ከነበረው ውሳኔ በተቃራኒ የተለየ ውሳኔ ላይ ያደረሰ ከሆነ ህሊናው ተዛብቷል ብለን መናገር እንችላለን። ህሊና ከተዛባ የክርክሩ ውጤት (ማለትም ውሳኔው) ጉዳዩ ከመመርመሩ በፊት ድምዳሜ ተደርሶበታል። ዳኛው ከከሳሽ ወይም ተከሳሽ ጉቦ ከተቀበለ ፍርዱ ለማን እንደሚሰጥ አስቀድሞ ታውቋል። በዚህ መልኩ የሚሰጥ ፍርድ በተዛባ ህሊና የተሰጠ አድሎአዊ ፍርድ ነው።
የተዛባ ህሊና ከምንጩ አንፃር በተለያየ መንገድ ይገለጻል። በዋነኛነት ከሚጠቀሱት መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።
ዝምድና
ዝምድና ሲባል የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም በግል ግንኙነት፣ በሙያ ትስስር እንዲሁም በጓደኝነትና በትውውቅ ላይ የተመሰረተና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተፅእኖ ሊያመጣ የሚችል ዝምድና ወይም ጥላቻ ሁሉ ያጠቃልላል።
ውሳኔ ሲጪው ከአንደኛው ተከራካሪ ወገን ጋር ዝምድና ወይም ጥላቻ ያለው ከሆነ አሉታዊ ወይም አዎንታዊ በሆነ መልኩ አድሎአዊ ወይም የተዛባ ፍርድ የመስጠት እድሉ ከፍተኛ ነው። የፌደራሉ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ (1993 ዓ.ም.) በአንቀጽ 29/2/ ላይ የዝምድናን ጽንሰ ሀሳብ በጣም አጥብቦታል። ድንጋጌው የግል ጥላቻ እንዳለበት የሚገምት ውሳኔ ሰጪ ራሱን በክርክሩ ሂደት ከመሳተፍ እንዲያገል ግዴታ ይጥልበታል። ከግል ጥላቻ ባልተናነሰ ትውውቅ፣ ቅርበት፣ ጓደኝነት በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድራሉ። ይህ መሰረታዊ ቁም ነገር በረቂቅ አዋጁ ላይ ተረስቷል።
ከዚህ በተቃራኒ የ1967ቱ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ከዝምድና የሚመነጭ የተዛባ አመለካከት ከቀጥተኛ የግል ጥቅም እንዲሁም ከስጋ ወይም ከጋብቻ የሚመነጭ ዝምድና በሙሉ እንደሚያጠቃልል በግልፅ ያመለክታል። የአስተዳደር ስነ-ስር ዓት አዋጅ ቁ. 1183/2012 ከ 1967 ቱ ረቂቅ ጋር ተቀራራቢ ይዘት አለው። ውሳኔው ሰጭው ከጉዳዩ ላይ ቀጥተኛ ወይም ቀጥተኛ ያልሆነ ጥቅም ካለው ወይም ባለጉዳዩ የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ወይም በቅርብ የሚታወቅ ወዳጁ ሲሆን ወይም የእነዚህ ሰዎች የጥቅም ግጭት ያለበት ጉዳይ ከሆነ ራሱን ማግለል እንዳለበት አንቀጽ 38/1/ በፊደል ሀ እና ለ በውሳኔ ሰጭው ላይ ግዴታ ይጥላል።
በአስተዳደር ህግ ውስጥ ‘ዝምድና’ የሚለው ቃል ከስጋ ወይም ጋብቻ ዝምድና የዘለለ በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ የሚችል ማንኛውንም አሉታዊና አዎንታዊ ግንኙነት ያቅፋል። ነገሩን ለማብራራት ያህል በአይ.ፒ. ማሴይ ‘የአስተዳደር ህግ’ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሰ አንድ ጉዳይ እንደ መላምታዊ ምሳሌ አገራዊ መልክ በማስያዝ ማየቱ ጠቃሚ ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ አንድ ማዕድን የመፈለግና የማውጣት ስራ ላይ የተሰማራ ድርጅት ከተሰጠው ፍቃድ ውጪ ህገ ወጥ ድርጊት ፈጽሟል ተብሎ በመከሰሱ ፈቃዱ የማይሰረዝበት አጥጋቢ ምክንያት ካለ መከላከያውን ይዞ እንዲቀርብ በማዕድን፣ ነዳጅና ተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር መጥሪያ ተላከለት። ሆኖም የዚህ ድርጅት ባለቤት በአንድ ወቅት ሚኒስትሩ ለምርጫ በተወዳደሩበት ወቅት የተቃዋሚ ፖርቲ አባል ሆኖ ሚኒስትሩ እንዳይመረጡ በመጣር ከፍተኛ ተቃውሞና ቅስቀሳ አድርጓል። በሌላ ጊዜም የሚኒስትሩን ስም በማጥፋት ወንጀል ተከሶ በመጨረሻ ነጻ ወጥቷል። እንግዲህ ሚኒስትሩ የንግድ ፍቃዱን ቢሰርዝ ውሳኔው በግል ግንኙነት /ጥላቻ/ ላይ የተመሰረተና የተዛባ ነው ማለት ይቻላል?
ከህንድና ከሌሎች አገሮች ልምድ ለመረዳት እንደሚቻለው የግል ግንኙነትን ጨምሮ በሌሎች ሁኔታዎች ውሳኔ የተዛባ ነው ለማለት ተገቢ የሆነ ጥርጣሬ መኖር አለበት። የመጀሪያው መለኪያ ውጫዊ መልክ ወይም ገጽታ መሰረት ያደርጋል። ይህም ማለት የግል ግንኙነቱ ደረጃ በአንድ አስተዋይ ሰው እይታ አድሎአዊነትነት የሚፈጥር አይነት ከመሰለና ይህም ተገቢ የሆነ ጥርጣሬን የሚያሳድር ከሆነ ውሳኔው የተዛባ ስለመሆኑ መደምደም ይቻላል። ሁለተኛውና ‘ቅርብ የሆነ አጋጣሚ’ የሚባለው መለኪያ ደግሞ ትኩረት የሚያደርገው አድልኦ የሚፈጠር መሆኑ አይደለም። ከዚያ ይልቅ እያንዳንዱን ጉዳይ በነጠላ በማየት ግንኙነቱ ውሳኔው ላይ ተጽእኖ ለማሳደር ያለውን አጋጣሚ (ደረጃ) ይመረምራል።
ስለሆነም በውሳኔ ሰጪውና በባለጉዳዩ መካከል የስጋ ወይም ጋብቻ ዝምድና ቢኖርም እንኳን ሁለቱ ካላቸው ቅርርብ ወይም ርቀት እንዲሁም ትክክለኛ የግንኙነት ደረጃ አንጻር የተጽእኖው ደረጃ ኢሚንት የሚባል አይነት ከሆነ ውሳኔው አልተዛባም። በተቃራኒው የዝምድናው ደረጃ ሩቅ ቢሆንም እንኳን ውሳኔ ሰጪውና ባለጉዳዩ በማህበራዊ ግንኙነታቸው የጠበቀና ቅርብ ትስስር ያላቸው (ለምሳሌ ለብዙ ጊዜያት አብረው በአንድ ቦታ የኖሩና ሌላም መሰል ትስስር ያላቸው) ከሆኑ አድሎአዊ ውሳኔ የመስጠት አጋጣሚው በጣም የሰፋ መሆኑን ስለሚያሳይ የውሳኔው የመዛባት አጋጣሚ ከፍተኛ ነው።
ተገቢ የሆነ ጥርጣሬ ወይም ቅርብ የሆነ አጋጣሚ እንደ የተዛባ ውሳኔ /አድልዎ/ መለኪያነት እርስ በርስ በጣም የተለያዩ ቢመስሉም በተግባር ሲታዩ ዞሮ ዞሮ መድረሻቸው አንድ ነው። መሰረታዊው ጥያቄ ውሳኔ ሰጪው ህሊናው ተዛብቷል? የሚል አይደለም። የአንድን ሰው የህሊና ሁኔታ ማረጋገጥ ይከብዳል። መታየት ያለበት ውሳኔው የተዛባ ሊሆን የሚችልበት እድል ሰፊ ወይም ቅርብ ነው ብሎ ለማመን የሚቻልበት ተገቢ ጥርጣሬ ማሳደሩ ነው።
ተገቢ ጥርጣሬ ማንኛውም ተራ ስሜትና ሀሜት የሚጨምር ሳይሆን በአስተዋይ ሰው እይታ በቂ መረጃ ላይ ተመስርቶ ያሉትን አጋጣሚዎችና ሁኔታዎች በመመርመር ተገቢ ወይም ሚዛናዊ ሊባል የሚችል የጥርጣሬ ሁኔታ መፈጠሩና ይህም በ3ኛ ወገን ላይ የሚያሳድረው ምክንያታዊ ስሜት ነው።
የገንዘብ ጥቅም
ቀጥተኛ የሆነ የገንዘብ ጥቅም እንደ አድሎዎ መገለጫነቱ ሲታይ ሊገኝ የሚችለው የገንዘብ መጠን አነስተኛ ቢሆንም እንኳን ውሳኔውን ለመሻር አሳማኝ ምክንያት ነው። ሰዎች ከገንዘብ ጥቅማቸው በተጻራሪ ውሳኔ እንደማይሰጡ ከሰው ልጅ ባህርይና ከተፈጥሮ እውቀት መገንዘብ አያዳግትም። ጉቦ መቀበል ግልጽና ዓይን ያወጣ የገንዘብ ጥቅም መገለጫ እንደመሆኑ ከተከራካሪ ወገኖች ከአንዱ የገንዘብ ስጦታ የተቀበለ የአስተዳደር መ/ቤት ሹመኛ ወይም ሰራተኛ እንዲሁም የአስተዳደር ጉባዔ ዳኛ የሚሰጠው ውሳኔ ወዲያውኑ ሊሻር ይገባዋል። ሆኖም የገንዘብ ጥቅም የሚገለጽባቸው መንገዶች የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ ያህል አንድ የአስተዳደር ጉባዔ ዳኛ ከሳሽ ወይም ተከሳሽ ሆኖ በቀረበው ድርጅት ውስጥ የአክሲዮን ባለቤት ከሆነ ተገቢ በሆነ ጥርጣሬ ብሎም ቅርብ በሆነ አጋጣሚ መለኪያ የሚሰጠው ውሳኔ የተዛባ ነው ብሎ መደምደም ተገቢ ይሆናል።
በፌደራሉ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ (1993 ዓ.ም.) መሰረት የአስተዳደር ውሳኔ ለመስጠት ስልጣን ያለው ሰው በጉዳዩ የመጨረሻ ውጤት ላይ የገንዘብ ጥቅም እንዳለው ከተረዳ ወዲያውኑ ራሱን ከውሳኔ ሰጪነት እንዲያገል ይጠበቅበታል። ይህ ካልተፈፀመ በክርክሩ ተካፋይ የሆነው ወገን አቤቱታ አቅርቦ ከችሎት እንዲነሳለት መጠየቅ ይችላል።l
ተደራራቢ (ቅይጥ) ሚና
በአንድ ጉዳይ ላይ በአጣሪነት፣ በመርማሪነት፣ በከሳሽነትና መሰል ኃላፊነቶች የተሳተፈ የመንግስት ባለስልጣን እንደገና ተመልሶ በተመሳሳይ ጉዳይ በውሳኔ ሰጭነት ስልጣኑ ከተሳተፈ የውሳኔውን አድሎአዊነት ያንፀባርቃል። አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመስጠት ስልጣን ያለው ተሿሚ ወይም ሠራተኛ ከውሳኔ በፊት አጣሪ፣ መርማሪ፣ ወይም በሌላ ሙያ ተሳታፊ በሆነበት ጉዳይ ተመልሶ በውሳኔ ሰጪነት ስልጣን የሚሳተፍ ከሆነ የተዛባ አድሎአዊ ውሳኔ የመስጠት እድሉ በጣም ከፍተኛ ነው። አንድ ሰው ራሱን የሚቃረን ውሳኔ የማይሰጥ መሆኑ ከሰው ልጅ ባህርይ የምንረዳው እውቀት ነው።
በአንድ ጉዳይ በተደራራቢ ሚና መሳተፍ በአስተዳደር ሂደቱ በውስጡ ያለ መገለጫ ቢሆንም ውጤታማ በሆነ መንገድ ቁጥጥር ካልተደረገበት የፍትሀዊነትንና የርትዐዊነትን ጽንሰ ሀሳብ ድራሹን ያጠፋዋል። የአንድን ድርጅት የንግድ እንቅስቃሴ ህጋዊነት ለማጣራት በመርማሪነት ሚና የተሳተፈ የመንግስት ሰራተኛ የድርጅቱን የንግድ ፈቃድ ለመሰረዝ በተካሄደው የአስተዳደር ክርክር ላይ በውሳኔ ሰጪነት ሚና በድጋሚ የሚሳተፍ ከሆነ ተደራራቢ ሚናው አድሎአዊ ለሆነ ውሳኔ መንስዔ መሆኑ አይቀርም። በተመሳሳይ መንገድ አንድ ሰራተኛ በተከሰሰበት የዲሲፕሊን ጉዳይ ላይ የመ/ቤቱ ኃላፊ የዲሲፕሊን ኮሚቴው አባል ሆኖ ከተሳተፈ በኃላፊነት ስልጣኑ የሚወስደው የዲሲፕሊን እርምጃ ከአድልኦ ያልፀዳ ነው።
ተደራራቢ ሚናን በተመለከተ ሁለቱም ረቂቅ አዋጆች ቁንጽል ድንጋጌ ቢኖራቸውም ከፍሬያማነታቸው ይልቅ ድክመታቸው ጐልቶ ይታያል። የፌደራሉ ረቂቅ አንቀጽ 29 /6/ እንዲህ ይነበባል።
በማናቸውም የአስተዳደር ተቋም ውስጥ በወንጀል ምርመራ ወይም ክስ በመመስረት ተግባር ተሰማርቶ የሚገኝ የመንግስት አስተዳደር ሰራተኛ በማናቸውም ሁኔታ በያዘው ጉዳይ ወይም ከዚሁ ጋር በፍሬ ነገር በተዛመደ ጉዳይ ላይ በሚሰጥ አስተዳደራዊ ውሳኔ በምስክርነት፣ የህግ ምክር በመስጠት መሳተፍ ወይም መምከር አይችልም።
የዚህ አንቀጽ ዋና ግድፈት የሚነጻጸሩት ተደራራቢ ሚናዎች አጣሪነት፣ መርማሪነት፣ ከሳሽነት ወዘተ… ከውሳኔ ሰጪነት ስልጣን ጋር ሳይሆን ከምስክርነት እና የህግ ምክር ሰጪነት ሚና ጋር መሆኑ ነው። የተደራራቢ ሚና ጽንሰ ሀሳብ ዋና አላማው ጉዳዩን ያጣራው ወይም የመረመረው ባለስልጣን ተመልሶ ውሳኔ ሰጪ ከሆነ ውሳኔው አድሎአዊ ሊሆን ስለሚችል ይህንኑ በመከላከል በአስተዳደር ክርክር ውስጥ ፍትህ ወይም ርትዕ ማስፈን ነው። ረቂቁ ይህን አላማ ለማሳካት ተጨባጭ ችግሩ ላይ ከማነጣጠር ይልቅ ለአስተዳደር ፍትህ አግባብነቱ ብዙም ፋይዳ በሌለው የወንጀል መርማሪነትና ከሳሽነት ሚናን ምስክር ከመሆንና የህግ እርዳታ ከመስጠት ሚና ጋር እንዳይደራረብ ገደብ ያስቀምጣል።
በ1967ቱ ረቂቅ አዋጅ መሰረት የመርማሪነት (ይህም በወንጀል መርማሪነት ሳይሆን በአስተዳደራዊ ሂደት ላይ ያሉ ሚናዎችን ያጠቃልላል።) እና የዐቃቤ ህግነት ሚና የነበረው ባለስልጣን ወይም ሰራተኛ በአስተዳደር ክርክሩ ላይ በዋናነት በውሳኔ ሰጪነት እንዳይሳተፍ ይከላከላል። ይሁን እንጂ በምስክርነት ወይም በአማካሪነት ከመሳተፍ እንደማይከለከል በልዩ ሁኔታነት በግልጽ ያስቀምጣል።
በንፅፅር ሲታይ አዋጅ ቁ. 1183/2012 የተሻለ ይዘት ያለው ቢሆንም ሁሉንም መሰረታዊ የተዛባ አመለካከት ምንጮች አልዳሰሰም። በአንቀጽ 38/1/ በፊደል ሐ እና መ ላይ የተጠቀሱት ሁለት ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው።
በመታየት ላይ ላለው ጉዳይ እንደ ባለሙያ፣ ወኪል ወይም የግል ጠበቃ ሆኖ ተሳትፎ ከሆነ፤
በመታየት ላይ ያለው ጉዳይ ሰራተኛው በስር ውሳኔ አይቶት በይግባኝ የቀረበለት ከሆነ
ከሁለቱ ውጭ በመመርማሪነት የተሳተፈ ሰው በውሳኔ ሰጭነት እንዳይሳተፍ በግልጽ የሚከለክል ድንጋጌ የለም።
 
ልዩ ሁኔታዎችና የተፈጻሚነት ወሰን
በፍርድ ቤቶች የዳበሩ መሰረታዊ መርሆዎች እንዲሁም አስገዳጅነት ያላቸው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ህጎች በሁሉም አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ወጥ ተፈጻሚነት የላቸውም። የእያንዳንዱ አስተዳደራዊ ውሳኔ ከግለሰቦች መብትና አንጻር ሲመዘን ከቀላል እስከ ከባድ የሚያስከትለው ውጤት እና ተፅዕኖ ይለያያል። የውሳኔውም ዓይነት እንዲሁ ወጥ መልክ የለውም። የመንግስት ሠራተኛን ከስራ ማባረር፣ አስተዳደራዊ ቅጣት መጣል፣ ለህዝብ ጥቅም ሲባል ከይዞታ ማፈናቀል፣ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት (ካርታ) መሰረዝ፣ የብቃት ማረጋገጫ፣ የሙያ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ፣ የስራ ፈቃድ መሰረዝና ማገድ፣ የሊዝ ውል ማቋረጥ፣ በአንድ የስራ ዘርፍ የተሰጠ ዕውቅና (ለምሳሌ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) መሰረዝ እና ሌሎች መሰል ውሳኔዎች ህገ መንግስታዊ ጥበቃ ያገኙ መብቶችን የመጣስ ከፍተኛ አዝማሚያ ስላላቸው ፍትሐዊ ስርዓት ተከትለው መወሰድ ይኖርባቸዋል። አስተዳራዊ ቅሬታ እና ይግባኝ የሚስተናገድበት መንገድ እንዲሁ ፍትሐዊ ስነ ስርዓት እና አንጻራዊ ገለልተኘነት ካላንፀባረቀ የይስሙላ ሆኖ ነው የሚቀረው።
ስለሆነም በእነዚህ በተጠቀሱት ምሳሌዎች ስር የሚወድቁና ሌሎች ተመሳሳይ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ለመሰማት መብት እና ኢ-አድሎአዊነት መርሆዎች ተገዢ ሊሆኑ ይገባል። እንደዛም ሆኖ ግትር ተፈጻሚነት ሊኖራቸው አይገባም። አስተዳደራዊ አመቺነትን ያላማከለ የሰነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታ ውጤታማነትን ያኮላሻል። ለምሳሌ በከፊል አስተዳደራዊ ክርክሮች በጠበቃ የመወከል መብት በአስተዳደሩ ላይ ከሚያመጣው ጫና አንጻር እንዲቀር ቢደረግ የመሰማት መብትን አያጣብብም።
ከላይ በምሳሌነት የተጠቀሱት አስተዳደራዊ ውሳኔዎች አንድ የአስተዳደር መ/ቤት በየዕለቱ ይቅርና በየወሩ የሚያከናውናቸው ተግባራት አይደሉም። በቁጥር በእጅጉ በልጠው የሚገኙት ውሳኔዎች ግዙፋዊ የመብት መጓደል አያስከትሉም። ሆኖም በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የግለሰቦችን መብትና ጥቅም የሚነኩ ከሆነ በዘፈቀደ መወሰድ የለባቸውም። ይብዛም ይነስም በተነካው መብት ልክ ፍትሐዊነት በገሀድ እንዲታይ ይጠበቃል።
እስካሁን የቀረበው ዳሰሳ አንድ መሰረታዊ ጥልቅ መልዕክት ያስጨብጠናል። ይኸውም፤ ሁሉንም የአስተዳደራር ውሳኔዎች ለአንድ ወጥ ስነ ስርዓት ተገዢ ማድረግ ሊሞከር ቀርቶ አይታሰብም። ፍርድ ቤት ብቻ ነው አንድ ወጥ ስነ-ስርዓት የሚከተለው። ያላደገ ሆነ የዳበረ የአስተዳደር ህግ ያላቸው አገራት በማንኛውም አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አንድ ወጥ ስነ ስርዓት የላቸውም። አንድ አስተዳደራዊ ውሳኔ ከቀላል እስከ ጥብቅ የትኛውን ስነ ስርዓት መከተል እንዳለበት ለመወሰን ለህግ አውጪው አስቸጋሪ ስራ ነው። ውስብስብ የሆነው የአስተዳደር ስራ ባህርይ በዚህ ረገድ የሚደረገውን ጥረት ፈታኝ ያደርገዋል። ያም ሆኖ ግን ፈተናው በወጉ ካልተመለሰ ፍትሐዊነትና ውጤታማ አስተዳደር ሚዛናቸውን ይስታሉ።
እንደ ፒተር ዎል አገላለጽ በአስተደደራዊ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ተፈጻሚ የሚሆኑት አነስተኛ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች እንደ ጉዳዩ ዓይነትና ውስብስብነት፣ የማስረጃዎችና የሚረጋገጡት ፍሬ ነገሮች ዓይነት፣ የውሳኔ ሰጭው ማንነትና የሚያከናውነው የአስተዳደር ተግባር ባህርይ እንዲሁም ውሳኔው በግለሰቦች ላይ ሊያስከትል ከሚችለው ጉዳት አንጻር ደረጃቸው ይለያያል።
[W]hat constitutes a minimum compliance with due process in the way of administrative hearing…will vary to a considerable extent with the nature of the substantive right, the character and complexity of the issues, the kinds of evidence and factual material, the particular body or official, and the administrative functions involved in the hearing.m
የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ፍትሐዊነት እንዲሰፍን ከዚያም አልፎ በህዝብ አስተዳደር ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነት በአጠቃላይ መልካም አስተዳደር እንዲያብብና እንዲጎለብት የሚያበረክተው አዎንታዊ አስተዋጽኦ በሀሳብ ሆነ በተግባር ደረጃ ተፈትኖ የተረጋገጠ ቢሆንም አፈጻጸሙ በጥንቃቄ ወሰን ካልተበጀለት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። የአስተዳደር ስነ ስርዓት ፍርድ ቤቶች እንደሚከተሉት የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት ጥብቅ እና መደበኛ በሆነ ቁጥር አስተዳደራዊው ሂደት እጅና እግሩ ይታሰራል። በዚህ የተነሳ ዜጎች ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ያጣሉ። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ደግሞ የዜጎችን ብሶት ‘ከፍትሕ ጥማት’ ወደ ‘አገልግሎት ረሀብ’ ቢቀይረው እንጂ ፍሬ አያስገኝም።
እ.ኤ.አ በ1946 በወጣው የአሜሪካው የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ (Administrative Procedure Act) የአስተዳደር ዳኝነት መደበኛ እና ኢ-መደበኛ በሚል ለሁለት ተከፍሏል። መደበኛው የአስተዳደር ዳኝነት ከክስ መስማት እስከ ውሳኔው ይዘት ድረስ በዝርዝር አስገዳጅ ደንቦች የሚገዛ ሲሆን ኢ-መደበኛው ግን በቀላልና ልል ስርዓት ይመራል። አስተዳደራዊ አመቺነትን ያማከለው ይህ አካሄድ በአንድ በኩል በዘፈቀደ በሚወሰድ እርምጃ ፍትሕ እንዳይጓደል በሌላ በኩል ደግሞ በጥብቅ ስነ ስርዓት ሳቢያ ውጤታማ አስተዳደር እንዳይሰናከል ህጉ የተከተለው አስታራቂ መስመር ነው።
በመደበኛው የአስተዳደር ዳኝነት ከክስ መሰማት (hearing) ጀምሮ አጠቃላይ ክርክሩ በመዝገብ (on the record) እንዲካሄድ የሚያስገድድ ሲሆን በይዘቱም ጠበቅ ያለ ስርዓት ነው። ይህ ስርዓት ተፈጻሚ የሚሆነው በልዩ ህግ በግልጽ ተደንግጎ ሲገኝ ብቻ ነው። የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህጉ የመደበኛውን የአስተዳደር ዳኝነት የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች በመደንገግ ተፈጻሚነቱን ግን ህግ አውጪው በዝርዝር ህግ በግልጽ በወሰናቸው ሁኔታዎች ላይ ብቻ ገድቦታል።n በዚህ መልኩ በመደበኛው የዳኝነት ሂደት የሚያልፉ የአስተዳደር ክርክሮች በቁጥር ከአምስት ፐርሰንት አይበልጥም።o የተቀሩት ኢ-መደበኛውን ስርዓት የሚከተሉ ናቸው። በሌላ አነጋገር መደበኛው አስተዳደራዊ ክርክር ተፈጻሚነቱ በልዩ ሁኔታዎች ብቻ ነው።
አሜሪካኖች ከሞላ ጎደል ሁሉም አስተዳደራዊ ክርክሮች ኢመደበኛ አካሄድ እንዲከተሉ የመረጡበት ምክንያት ንድፈ ሀሳባዊ ሳይሆን ተጨባጭና ተግባራዊ ነው። የአስተዳደር መ/ቤቶች እንደ መደበኛ ፍርድ ቤት ክስ እየሰሙ በማከራከር ውሳኔ የሚሰጡ ከሆነ የተቋቋሙለትን ዓላማ መቼም ቢሆን አያሳኩም። መደበኛ የአስተዳደር ክርክር ከሚፈጀው ጊዜ እንዲሁም ከሚያስፈልገው የሰው ሀይልና የገንዘብ ወጪ አንጻር በሁሉም አስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ ተፈጻሚ ቢደረግ ውጤታማ አስተዳደር ይቅርና ‘አስተዳደር’ የሚባል ነገር ራሱ አይኖርም።
በኢትዮጵያ በ1993 ዓ.ም. እና 2001 ዓ.ም. የተዘጋጁት ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጆች ይህን መሰረታዊ ተጨባጭ እውነታ በቅጡ አልተረዱትም። ሁለቱም ረቂቆች አስተዳደራዊ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት መደበኛው የክስ መሰማት ስርዓት እንዲከናወን በአስተዳደር መ/ቤቶች ላይ ግዴታ ያስቀምጣሉ። ይሄ የገዘፈ ችግር በረቂቆቹ የተገታ ሳይሆን ህግ ሆኖ የፀደቀው የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግም የሚጋራው ችግር ነው።p ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በአሜሪካ በዚህ ዓይነት የክርክር ሂደት የሚያልፉ ጉዳዮች ከአምስት ፐርሰንት አይበልጡም። የተቀረው 95 ፐርሰንት ኢመደበኛ ነው። በረቂቅ ህጎቹ የተመረጠው አቅጣጫ ደግሞ ሁሉም (ማለትም 100 ፐርሰንት) አስተዳደራዊ ክርክሮች መደበኛ ስርዓት እንዲከተሉ ያስገድዳል። በዚህ ሁኔታ አስገዳጅ ህግ ሆነው በተወካዮች ም/ቤት ቢታወጁ ሊከተል የሚችለውን አስተዳደራዊ መንዛዛት ለመገመት ከወደሁ ያስቸግራል።
የመሰማት መብት እና ኢ-አድሎአዊነት መርህ ከአገራችን ህግ አንጻር
ህገ መንግስታዊ የመሰማት መብት?
የተፈጥሮ ፍትሕ በእንግሊዝና ሌሎች ኮመን ሎው አገራት በዳኞች የዳበረ የፍትሐዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርህ ነው። ይህ መርህ በህግ በግልጽ እንደ ቅድመ ሁኔታ ባይቀመጥም ዳኞች ተፈጻሚ እንዳያደርጉት አያግዳቸውም። በአሜሪካ እንዲሁ ህገ መንግስታዊ ዕውቅና ያገኘው ዱ ፕሮሰስ ኦፍ ሎው (Due Process of Law) በመባል የሚታወቀው ህገ መንግስታዊ መርህ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓትን የሚገዛ ልዩ ህግ ባይኖርም እንኳን ፍርድ ቤቶች እንደ አግባብነቱ ተፈጻሚ ያደርጉታል። ሆኖም በእነዚህ ሁለት አገራት ሆነ በሌሎችም ዘንድ አስተዳደር የሚመራበት ስነ ስርዓት ምንጩ በህግ አውጪው የሚወጣ ህግ ነው።
ግልጽ የህግ ድንጋጌ ካለ የስነ-ስርዓት ጉድለት ያለበት ውሳኔ በፍርድ ቤት ሊሻር ወይም ሊሰረዝ እንደሚገባው አያጠራጥርም። አስገዳጅ የህግ ድንጋጌ ከሌለስ? ፍርድ ቤቶቻችን እንደ እንግሊዝና አሜሪካ ፍርድ ቤቶች ፍትሐዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎችን ማዳበርና ተፈጻሚ ማድረግ አለባቸው? ካለባቸውስ አቋማቸው ህገ መንግስታዊ መሰረት አለው? በአስተዳደራዊ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት የመሰማት መብት እንዲሁም ኢ-አድሎአላዊነት መርህ በህግ በግልጽ ባልተደነገገበት ሁኔታ የስነ-ስርዓት ጉድለት ያለበት አስተዳደራዊ ውሳኔ ዕጣ ፋንታ መወሰን በብዙ መልኩ ከባድ ነው።
በአንድ በኩል ፍርድ ቤቶች የዜጎችን ፍትሕ የማግኘት መብት የማረጋገጥ ህገ መንግስታዊ ግዴታ ተጥሎባቸዋል። በሌላ በኩል ህጉን ከማንበብና ከመተርጎም ባለፈ ህግ መጻፍ ህገ መንግስታዊ ሚናቸው አይፈቅድላቸውም። በዚህ መልኩ የሚፈጠረው ‘ህገ መንግስታዊ አጣብቂኝ’ ብርታትና ጥንቃቄ ካልታከለበት በቀላሉ አይፈታም። በተጨማሪም ‘መርህ’ በተጨባጭ ‘መሬት ሲወርድ’ ከልዩ ሁኔዎች ጋር ሊጣጣምና የተፈጻሚነት ወሰኑ በአግባቡ ሊሰመር ይገባል። የመሰማት መብት የግድ የሚልበት ሁኔታ ቢኖርም ከተግባራዊ ፋይዳውና ውጤታማ አስተዳደር አንጻር የሚገደብባቸው ሁኔታዎች አሉ። በተጨማሪም የተፈፃሚነቱ ወሰን የግለሰብ መብት ወይም ጥቅም በሚነካ የዳኝነታዊ ባህርይ ባለው አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ ብቻ ነው። ይህ የሚያሳየን አስቸጋሪው ስራ የፍትሐዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎችን በጠቅላላው መቀበሉ ሳይሆን እንደ ጉዳዩ አይነት ልዩ ሁኔታዎችን ከግምት ባስገባ መልኩ የተፈጻሚነቱን አድማስ መለየቱ ላይ ነው።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 43511q በ2005 ዓ.ም. በሰጠው ፈር ቀዳጅ የህግ ትርጉም መሰረት አስገዳጅ የህግ ድንጋጌ ባይኖርም ከፊል የዳኝነት ስልጣን የተሰጠው አካል የመሰማት መብትን የማክበር ግዴታ አለበት። የችሎቱን አቋም በጥልቀት ለመረዳት በሐተታው ክፍል የሰፈረውን የሚከተለውን አስተያየት ማየቱ ተገቢ ነው።
…የመሰማት መብት በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ሊከበር የሚገባው መብት ነው። የመሰማት መብት ከመጀመሪያው ክርክር ጀምሮ እስከመጨረሻው የዳኝነት ሰጪ አካል መከበር ያለበት ስለመሆኑ በሕገ መንግስቱና ስለ ክርክር አመራር በተደነገጉት እንደፍትሐብሔር ስነ ስርአት አይነት ሕጎች ከተደነገጉት ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው።
የችሎቱ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ዜጎች ሀሳባቸው ሳይደመጥ መብትና ጥቅማቸውን የሚጎዳ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዳይሰጥባቸው ከለላ በማጎናጸፍ ረገድ ህገ መንግስታዊ ፋይዳው ‘ታሪካዊ’ ሊሰኝ የሚችል ነው። ከዚያም አልፎ ለአገራችን የአስተዳደር ህግ ዕድገት ችሎቱ ካደረጋቸው አስተዋጽኦዎች መካከል ቀዳሚውን ቦታ ይይዛል። በእርግጥ የውሳኔው ፋይዳ ብቻውን በቁሙ መለካት በተግባር ያስከተላቸውን ለውጦች በማጋነን ያስተቻል። የሰ/መ/ቁ. 43511 አስተዳደሩ አካሄዱን ከችሎቱ አቋም ጋር እንዲያስተካክል በዚህም የመሰማት መብትን የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ አካል አድርጎ እንዲያቅፍ የፈጠረው ጫና ሆነ በተግባር ያስከተለው ተጨባጭ ለውጥ የለም። አስገዳጁን የህግ ትርጉም መቀበልና መተግበር ያለባቸው የስር ፍርድ ቤቶችም ቢሆኑ በአስተዳደራዊ ክርክሮች የመሰማት መብትን በትጋት እንዲያስከብሩ የለውጥ ምንጭ አልሆነላቸውም። ምናልባትም ውሳኔው ስለመኖሩ ራሱ ገና አልሰሙ ይሆናል። የሰበር ውሳኔዎች የተደራሽነት ችግር እንዲሁም በውሳኔዎቹ ላይ ጠንካራ ምሁራዊ የሀሳብ ልውውጥ ባህል አለመዳበር በርካታ አስገዳጅ የህግ ትርጉሞች በቅጾች መጽሐፍ ውስጥ ተቀብረው እንዲረሱ ያደርጋቸዋል።
የሰ/መ/ቁ. 43511 ከህገ መንግስታዊ ፋይዳው ባሻገር ክርክሩ የተጓዘበት መስመር ትኩረት ይስባል። የክርክሩ መነሻ አመልካቾች ከአዋጅ ውጪ የተወረሰ ቤት እንዲመለስላቸው ለኢትዮጵያ ፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ያቀረቡት አቤቱታ ሲሆን ኤጀንሲውም ተጠሪ ምላሽ እንዲሰጡበት ካደረገ በኋላ ማስረጃና ክርክሩን ሰምቶ ቤቱ እንዲመለስላቸው ወስኗል። በውሳኔው ባለመስማማት ተጠሪ ለኤጀንሲው ቦርድ ይግባኝ በማቅረባቸው ቦርዱ የኤጀንሲውን ውሳኔ ሽሮታል። ከመሻሩ በፊት ግን አመልካቾችን ጠርቶ ክርክራቸውን አልሰማም።
በመቀጠል አመልካቾች የመሰማት መብታቸው አለመጠበቁን በመግለጽ በቀጥታ የሰበር አቤቱታ ለፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/ሰ/ችሎት ያቀረቡ ቢሆንም አጣሪ ችሎቱ የቦርዱን ውሳኔ የማረም ስልጣን እንዳልተሰጠው በመግለጽ ሳይቀበለው ቀርቷል። አመልካቾች ተስፋ ባለመቁረጥ ጉዳዩ ህገ መንግስታዊ ትርጉም እንደሚያስነሳ በመጠቆም ለህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ አመለከቱ። እዛም ተቀባይነት አጡ። አሁንም ሰሚ ፍለጋ ‘አቤት!’ ማለታቸውን ባለማቆም ጉዳያቸውን እንዲያይላቸው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይግባኝ አቀረቡ። በመጨረሻ ጥያቄያቸው ፍሬ አግኝቶ የአጣሪ ችሎቱ ውሳኔ ተሻረ።
አመልካቾች ተስፋ ባለመቁረጥ እስከ ፌዴሬሽን ም/ቤት ድረስ ዘልቀው ድል መጎናጸፋቸው በራሱ የተለየ ስሜት ቢያጭርም በተለየ መልኩ ትኩረት የሚስበው ግን የክርክሩ ሂደት ሳይሆን የም/ቤቱ ውሳኔ ይዘት ነው። የሰበር ችሎት የዳኝነት ስልጣንን በማስፋት አዲስ ህገ መንግስታዊ መልክ ያላበሰው ይኸው ውሳኔ የሰበር ችሎት የቦርዱን መሰረታዊ የህግ ስህተት የማረም ስልጣን እንዳለው አረጋግጧል። የም/ቤቱ ህገ መንግስታዊ ትርጓሜ መነሻ ያደረገው የኤጀንሲው ቦርድ ዳኝነታዊ ስልጣን ነው። ስለሆነም ቦርዱ የዳኝነት መሰል አካል (quasi judicial body) በመሆኑና ይህ አካል የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ በመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር ስልጣኑ ጉዳዩን የማየት ስልጣን አለው።
የስልጣን ጥያቄው እልባት ካገኘ በኋላ መዝገቡ ከፌዴሬሽን ም/ቤት ወደ ሰበር ችሎት ሲመለስ የቦርዱ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት መሰረታዊ ጭብጥ ሆኖ ተነስቷል። ጭብጡን ለመፍታት ችሎቱ የቦርዱን የማቋቋያ አዋጅr የተመለከተ ቢሆንም በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ቦርዱ የተከራካሪዎችን የመሰማት መብት እንዲጠብቅ የሚያስገድድ ድንጋጌ አላገኘም።
በአስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ የመሰማት መብት የሚጠብቅ ህግ በሌለበት ሁኔታ ውሳኔው ሰጭው አካል በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት መብቱን እንዲያከብር ግዴታ መጫን ለችሎቱ ፈታኝ ስራ እንደሆነ አያጠያይቅም። ምክንያቱም ከህግ የመነጨ ግዴታ በሌለበት ቦርዱ የመሰማት መብት መርሆዎችን እንዲከተል ማስገደድ በውጤቱ የችሎቱን ተግባር ከህግ መተርጎም ወደ ‘ህግ መጻፍ’ ያሸጋግረዋል። ስለሆነም ችሎቱ በስልጣን ክፍፍል መርህ የተሰመረውን ድንበር ሳይሻገር በራሱ የዳኝነት ስልጣን ዛቢያ ውስጥ ሆኖ ውሳኔውን በአሳማኝ ምክንያት ማስደገፍ አለበት። ከዚህ አንጻር ለአቋሙ መሰረት ያደረገውን ምክንያት ማየቱ ጠቃሚ ነው። በዚህ ነጥብ ላይ ዋናው የሀተታ ክፍል እንደሚከተለው ይነበባል።
ቦርዱ ከፊል ውሳኔ ሰጪ አካል እንደመሆኑ መጠን የሚሰጠው ውሳኔ የሕጉን ስርዓት ተከትሎ ሊሰጥ ይገባል። ከፊል የዳኝነት ስልጣን የተሰጠው አካል በሕጉ ተለይቶ የተቀመጠለት የክርክር አመራርና አሰጣጥ ስርዓት እስከሌለ ድረስ በኢ.ፌ.ዲ. ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት የተጠበቁትን ፍትህ የማግኘት፣ የመሰማትና በእኩል ሚዛን የመታየት መብት ሊያከብር ይገባል። በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ሊጠበቁ ከሚገባቸው ሕገ መንግስታዊ መብቶች አንዱ ደግሞ ክርክር የማቅረብና ማሰረጃ የማሰማት መብት ነው። ይህ የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት የግድ ከሚላቸው የስነ ስርዓት አካሄዶች አንዱ ነው። ክርክሩን በአግባቡ እንዲያቀርብ እድል ያላገኘ ሰው በኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀፅ 37 የተከበረለት ፍትህ የማግኘት መብቱ ውጤታማ ሊሆን አይችልም።
ህጉን በፍሬ ነገሩ ላይ ተፈጻሚ በማድረግ አሳሪ ውሳኔ የሚያስተላልፍ አካል ተግባሩ ዳኞች በችሎት ተቀምጠው ከሚያከናውኑት የዳኝነት ተግባር አይለይም። ስለሆነም የዳኞችን ዓይነት የፍትሐ ብሔር ስነ-ስርዓት መከተል ባይኖርበትም ቢያንስ ቢያንስ አንደኛውን ወገን ብቻ ሰምቶ መወሰን የለበትም። ችሎቱ ይህን መሰረታዊ የአስተዳደር ህግ መርህ በአግባቡ ተረድቶታል። ‘ታሪካዊ’ መባሉም ለዚህ ነው። ምክንያቱም ይሄን የመሰለ ይቅርና የሚቀራረብ ውሳኔ ከችሎቱ መንጭቶ አያውቅም።
ቀደም ብለው የተሰጡ ተመሳሳይ ውሳኔዎች ባይኖሩም ከአንድ ዓመት በኋላ በታየ መዝገብ የመሰማት መብት ህገ መንግስታዊ ዕወቅና አግኝቷል። በሰ/መ/ቁ. 92546s በዲሲፕሊን ጉዳይ የተከሰሰ ዓቃቤ ህግ በዓቃቤ ህግ አስተዳደር ዋና ጉባዔ ውሳኔ መከላከል ሳያስፈልገው ከክሱ ነጻ ከተደረገ በኋላ በድሮው አጠራር የፍትሕ ሚኒስትር (በአሁኑ ጠቅላይ ዓቃቤ) ዴኤታ ፊርማ መከላከያውን ሳያሰማ በመሰናበቱ የሚኒስትሩን እርምጃ በመቃወም በቀጥታ ለሰበር ችሎት ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት አግኝቷል። ችሎቱ በውሳኔው ሚኒስትሩ ከህግ የመነጨ ከፊል የዳኝነት ሰልጣን እንዳለው በመጠቆም የማሰናበት እርምጃው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ጥበቃና ዋስትና የተሰጠውን የእኩልነትና ፍትሕ የማግኘት መብት እንደሚጻረር በመጠቆም ሽሮታል።
በህግ የተቀመጠ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት
በአገራችን ወጥ የአስተዳደር ህግ ባይኖርም የአስተዳደር መ/ቤቶች በግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ እርምጃ የሚወስዱት ሁልጊዜ በዘፈቀደ አይደለም። ይብዛም ይነስም በተለያዩ ዝርዝር ህጎች ላይ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች ተደንግገዋል። ጠቅለል ተደርጎ ሲታይ ከክስ መሰማት ጀምሮ እስከ መጨረሻው ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ድረስ የአስተዳደር መ/ቤቶች የሚከተሉት ስነ ስርዓት በዚህም ፍትሐዊነት የሚገለጽበት መንገድ ደረጃው ይለያያል። በአንዳንዶቹ ጠበቅ ያለና መደበኛነት የሚታይበት ሲሆን በሌሎቹ ደግሞ ቀላል እና ‘ልል’ ተብሎ ሊገለጽ የሚችል ነው።
ከሞላ ጎደል ሁሉንም የመሰማት መብት እና የኢአድሎአዊነት መርሆዎች ያሟላ በዓይነቱ በአሜሪካው የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ላይ ‘መደበኛ’ ተብሎ የተገለጸውን የአስተዳደር ዳኝነት የሚመስል የክርክር ስርዓት የሚገኘው የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁ. 847/2006 ላይ ነው። ስርዓቱ የተዘረጋው ህግን በመተላለፍ ጥፋት በሚፈጽም ኦዲተር ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ነው። ከክስ አመሰራረት እስከ ውሳኔ አሰጣጥ ድረስ የክርክሩ አመራር ስርዓት በአዋጁ ከአንቀጽ 38-43 ባሉት ድንጋጌዎች የሚመራ ሲሆን ሂደቱ አጠር ተደርጎ ሲጠቃለል የሚከተለውን ይመስላል።
አዋጁ የኢ-አድሎአዊነት መርህን ለማረጋገጥ የሚና መደበላለቅን አስቀርቷል። የመርማሪነት፣ ከሳሽነት እና ውሳኔ ሰጭነት ሚናዎች በኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ሰራተኛ/ተሿሚ ተለይተው ተከፋፍለዋል። በዚሁ መሰረት ‘መርማሪ ሹም’ የሚባል የቦርዱ ተቀጣሪ ሠራተኛ ወይም ከቦርዱ ጋር የቅጥር ግንኙነት ያልመሰረተ ብቃት ያለው ባለሞያ የምርመራ ተግባር ያከናውናል። መርማሪ ሹሙ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ሲያምንበት ክስ እንዲመሰረት ለቦርዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ የውሳኔ ሀሳብ ከማቅረብ ውጪ በራሱ ክስ አያቀርብም። በአዋጁ የከሳሽነት ሚና የተሰጠው ለስራ አስፈፃሚው ነው። ስራ አስፈፃሚው ክስ ለመመስረት ከወሰነ በምርመራ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ ያልነበሩ ከመካከላቸው አንዱ የህግ ባለሞያ የሆነ ሶስት የቦርዱን ሰራተኞች በክስ ሰሚነት ይሰይማል። እነዚህ ክስ ሰሚዎች (hearing examiners) ክርክሩን ሰምተው የመጨረሻ ውሳኔ የማስተላፍ ስልጣን አላቸው።
የዲሲፕሊን ክስ የቀረበበት ሰው ስለቀረበበት ክስ ይዘት የማወቅ እና በራሱ ወይም በጠበቃው አማካኝነት ቀርቦ ማስረጃውን የማቅረብ፣ ምስክሮቹን በመጥራት ቀጥተኛ ጥያቄ መጠየቅና እና ለከሳሽ ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ መብቱ በአዋጁ አንቀጽ 39/2/ ተጠብቆለታል። በግራ ቀኙ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች በተጨማሪ ክስ ሰሚዎች ለጉዳዩ አወሳሰን ጠቃሚ ማስረጃ ይዞ የሚገኝ ማንኛውም ሰው በመጥሪያ በመጥራት በቃለ መሀላ የማረጋገጫ ቃሉን መቀበልና አግባብነት ያላቸውን ሰነዶችና ማስረጃዎች እንዲያቀርብ የማስገደድ ሰፊ ዳኝነታዊ ስልጣን ተጎናጽፈዋል። ክስ ሰሚዎች በክርክሩ ሂደት የቀረቡትን ማስረጃዎችና ክርክሩን ከመረመሩ በኋላ ክስ የቀረበበት ተከሳሽ አዋጁንና በአዋጁ መሰረት የወጣን ደንብና መመሪያ መተላለፍ አለመተላፉን ይወስናሉ። የህግ መተላለፍ ከተፈጸመ ማስጠንቀቂያ ከመስጠት ጀምሮ እስከ ፈቃድ መሰረዝ ብሎም እስከ ብር 25,000 (ሃያ አምስት ሺ ብር) የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እና ሌሎች በአዋጁ ላይ የተዘረዘሩ አስተዳደራዊ ቅጣቶችን ማስተላለፍ ይችላሉ።
ከሞላ ጎደል ተቀራራቢ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በሚወስዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች ላይ ተፈጻሚ ይደረጋል። በሲቪል አቪዬሽን አዋጅ ቁ. 616/2001 አንቀጽ 80/1/ ላይ እንደተደነገገው ባለስልጣኑ አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ሊወስደው ስላሰበው እርምጃ ለሚመለከተው ሰው ማሳወቅና እርምጃው ሊወሰድ አይገባም የሚልበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ዕድል መስጠት አለበት። ማስታወቂያው ጥፋት መፈጸሙን የሚገልጽ ክስ ሳይሆን በምርመራ ግኝት ባለስልጣኑ ድምዳሜ ላይ ከደረሰ በኋላ ድምዳሜውን ለማስተባበል የሚደረግ ጥሪ ነው። ስለሆነም በምርመራ ሂደት ባለስልጣኑ የሚሰማቸውን ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ ዕድል አይኖርም። ሆኖም ቀጣይ የአዋጁ አንቀጽ 80/4/ ድንጋጌ በጠበቃ ወይም ባለጉዳዩ በራሱ ክርክር የማሰማት መብትን የሚፈቅድ እንደመሆኑ ማስረጃ የማቅረብና ምስክር ማሰማት የስነ ስርዓቱ አካል አድርጎ መቁጠር ይቻላል። በተጨማሪም የባለስልጣኑ ሠራተኛ የግል ጥቅሙን በሚነካ ጉዳይ በምርመራ ሂደት እንዳይሳተፍ ገደብ የሚጥለው የአዋጁ አንቀጽ 80/3/ በከፊልም ቢሆን ከአድልኦ የፀዳ ውሳኔ እንዲሰጥ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ህግን በማስከበር ስልጣናቸው በቀጥታ ከሚያስተላልፏቸው ውሳኔዎችና ከሚወስዷቸው እርምጃዎች በተጨማሪ በአማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴ ዳኝነታዊ ተግባራት ሲያከናውኑ ጠበቅ ያለ ስርዓት ይከተላሉ። በኢትዮጵያ የውሀ ሀብት አስተዳደር አዋጅ ቁ. 197/1992 የማዕከል ውሀ ሀብት አስተዳደርን አስመልክቶ የቁጥጥር ተግባራት እንዲያከናውን ስልጣን የተሰጠው ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የውሀ ግልጋሎት ፈቃድ የተሰጣቸው ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ከፈቃዱ ጋር የተያያዙ መብትና ግዴታዎችን አስመልክቶ በመካከላቸው የሚነሱ ክርክሮችን እንዲሁም በባለ ፈቃድ እና በሌላ ሶስተኛ ወገኖች መካከል የሚፈጠሩ ማናቸውንም ክርክሮች ሰምቶ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። አዋጁ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት በውክልና በሰጠው የህግ አውጭነት ስልጣን መሰረት ክርክሮቹ የሚመሩበት ስርዓት በደንብ ቁ. 115/1997t ተደንግጓል።
በተቆጣጣሪው ባለስልጣን ዘንድ በሚካሄደው የክርክር አመራር ስርዓት ላይ መደበኛው የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት ህግ ተፈጻሚነት አለው። በደንቡ ላይ ተለይተው የተቀመጡት ጥቂት የስነ-ስርዓት ድንጋጌዎችም ቢሆኑ ጠበቅ ያሉ ናቸው። በዚህ የተነሳ በተቆጣጣሪው አካል የሚካሄደው ክርክር በይዘቱ ፍርድ ቤቶች ከሚከተሉት የሙግት ስርዓት ጋር ይቀራረባል።
ክርክሩ የሚጀመረው አቤት ባዩ በሚያቀርበው ማመልከቻ ነው። ማመልከቻው የክርክሩን ፍሬ ሀሳብ (በእንግሊዝኛው ቅጂ memorandum summarizing the dispute) እና ማስረጃ እንዲሁም የአቤት ባዩን ቅሬታ እና እንዲሰጥለት የሚፈልገውን ውሳኔ አካቶ መያዝ ይኖርበታል። ስለሆነም በይዘቱ ከመደበኛው የክስ አቤቱታ ብዙም አይለይም። ተቆጣጣሪው አካል ማመልከቻውን እንደተቀበለ ክርክሩ የሚሰማበትን ቦታና ጊዜ የሚገልጽ መጥሪያና የማመልከቻ ቅጂ ለተከሳሹ እንዲደርሰው ያደርጋል። በቀጠሮ ቀን ባለጉዳዮች በቀጠሮ ሰዓትና ቦታ ተገኝተው ጉዳያቸውን ያስረዳሉ። ማስረጃም ያቀርባሉ። በሁለቱም ወገኖች የሚቀርቡ ማስረጃዎች በተቆጣጣሪው አካል ይመዘገባሉ። ተከሰሹ መጥሪያ ደርሶት ካልቀረበ ጉዳዩ በሌለበት ይሰማል። ተቆጣጣሪው ጉዳዩን ሰምቶ የሚሰጠውን ውሳኔ ባለጉዳዮች እንዲያውቁት ማድርግ ያለበት ሲሆን በተጨማሪም የውሳኔውን መዝገብ ግልባጭ የመስጠት ግዴታ አለበት። በደንቡ ላይ ለውሳኔ ምክንያት መስጠት እንደ ቅድመ ሁኔታ አልተቀመጠም። ይሁን እንጂ ተቆጣጣሪው እንደ አግባብነቱ የፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህጉን ተፈጻሚ የማድረግ ግዴታ ያለበት እንደመሆኑ ምክንያት የጎደለው ውሳኔ በፍርድ ቤት መሻሩ አይቀርለትም።
ከላይ ያየነው ዓይነት ከመደበኛ ፍርድ ቤት ጋር የሚቀራረብ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት አፈጻጸሙ በውስን አስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ ብቻ ነው። በጣም በርካታ መ/ቤቶች ለስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች የሚገዙት በጣም በስሱ ነው። አብዛኛው ቀዳሚ ውሳኔ /initial decision/ በአስተዳደራዊ የሙግት ሂደት ስር አያልፍም። ውሳኔ አሰጣጡ በባህርዩ መርማሪ ሲሆን ጉዳዩ የሚመለከተውን አካል አያሳትፍም። ህግ መጣሱ የሚረጋገጠው መ/ቤቱ በሚቀርብለት ጥቆማ ወይም በራሱ አነሳሽነት በሚያካሂደው ምርመራና ማጣራት አማካይነት ነው። በዚህ መልኩ ጥፋት መፈጸሙ አስቀድሞ አቋም ይያዝበታል። ሆኖም መ/ቤቱ የደረሰበት ድምዳሜ አስገዳጅነት ወዳለው የመጨረሻ ውሳኔ ከመሸጋገሩ በፊት የሚመለከተው አካል አስተያየት ወይም ምላሽ እንዲሰጥበት ይደረጋል። መልስ ሰጭው የቀረበበትን ማስረጃ የማስተባበል አሊያም ተቃራኒ ማስረጃ የማቅረብ በህግ የተጠበቀ መብት የለውም።
ልል እና ኢ-መደበኛ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ከሚደነግጉ ህጎች መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በመድን ሰጪ ድርጅት ያካሄደው ምርመራ የመጨረሻ ሪፖርት ከመዘጋጀቱ በፊት ለተመርማሪው መድን ሰጪ ድርጅት እንዲደርሰው ተደርጎ በሪፖርቱ ላይ አስተያየቱን እንዲያቀርብ ዕድል ይሰጠዋል።u
/ንግድና ኢንዱስትሪ/ ሚኒስቴሩ ወይም የእርሱ ተወካይ የአንድ ባለዕቃ ማከማቻ ቤት የግብርና ምርት ውጤቶች ተቆጣጣሪ፣ መዳቢ፣ ደረጃ ሰጪ፣ መዛኝ ወይም ናሙና አውጭ የሥራ ፈቃድ ለዘለቄታው እንዲሰረዝ ከመወሰኑ በፊት አጥፍቷል የተባለው ጥፋት በጽሑፍ እንዲገለጽለትና በቂ ጊዜ ተሰጥቶት በጉዳዩ ላይ ምላሽ እንዲሰጥበት ወይም መቃወሚያ እንዲያቀርብበት ዕድል ሊሰጠው ይገባል።v
የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ በማንኛውም ድርጅት ላይ የትኛውንም ዓይነት አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ድርጅቱ መከራከሪያዎቹንና ማስረጃዎቹን የማቅረብና የመሰማት መብት አለው።w
የጉምሩክ ኮሚሽን ማንኛውም ዕቃ ወይም ማጓጓዣ በዚህ አንቀጽ መሠረት ውርስ ሆኖ ለመንግሥት ገቢ ከመደረጉ በፊት የዕቃው ወይም የማጓጓዣው ባለቤት በአዋጁ አንቀጽ 143(3) ወይም (4) መሠረት የመያዝ እርምጃውን አንዲያውቀው ከተደረገበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ ተቃውሞውን እንዲያቀርብ ዕድል መስጠት አለበት፡፡x
በተጨማሪም ኮሚሽኑ በኤሌክትሮኒክስ መረጃ ልውውጥ ሥርዓት የመጠቀም መብትን ከማገዱ ወይም ምዝገባውን ከመሠረዙ በፊት እርምጃው የሚወሰድበትን ምክንያት ለተጠቃሚው በጽሑፍ በማሳወቅ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ አስተያየቱን እንዲያቀርብ ዕድል መስጠት አለበት፡፡y
የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አንድን ፈቃድ ከማገዱ ወይም ከመሠረዙ በፊት እርምጃውን የሚወስድበትን ምክንያት ለባለፈቃዱ በጽሑፍ በመግለጽ ባለፈቃዱ ጽሁ በደረሰው በሰባት ቀናት ውስጥ የበኩሉን አስተያየት በጽሑፍ እንዲሰጥ ያደርጋል፡z
የመሰማት መብት በህግ ቢፈቀድም በጥቅል አነጋገር በሚገለጽበት ጊዜ የመብቱን ወሰን አፈጻጸም አስቸጋሪ ያደርገዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የክፍያ መፈጸሚያ ተቋምን ወይም የግብይት ፈጻሚዎችን ወይም የማህበራቸውን ዕውቅና ከማገዱ ወይም ከመሰረዙ በፊት መጀመሪያ የተቋሙ ኃላፊዎች በማስታወቂያ እንዲያውቁት ማድረግና ለባለጉዳዩ የመሰማት ዕድል መስጠት ይኖርበታል፡a የድንጋጌው አነጋገር የጠቅላላነት ባህርይ ቢታይበትም የመሰማት መብት መሰረታዊ የአስተዳደር ፍትሕ ጥያቄ እንደመሆኑ ዕውቅና ከመታገዱ ወይም ከመሰረዙ በፊት ቅድመ ክስ ማስታወቂያ፣ ማስረጃ የማቅረብ መብትና ተቃራኒ ማስረጃ የማስተባበል መብት ተሟልተው ሊገኙ ይገባል።
በአንዳንድ ህጎች ላይ ደግሞ የመሰማት መብት ውሳኔውን በማሳወቅ ላይ ብቻ ይገደባል። በእርግጥ ውሳኔው አግባብ እንዳልሆነ በቃል ሆነ በጽሑፍ ማስተባበል ካልተቻለ የመሰማት መብት መነፈጉን እንጂ በከፊል መገደቡን አይደለም የሚያሳየው። የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴሩ የዕፅዋት አዳቃዮችን መብት ለመሰረዝ ውሳኔ ላይ ከደረሰ ለመሰረዝ የበቃበትን ምክንያት በመግለጽ ለባለመብቱ የጽሑፍ ማስታወቂያ መስጠትና መብቱ የተሰረዘ መሆኑን ለሕዝብ ማስታወቅ አለበት።b ማስታወቂያው የመሰረዝ ውሳኔውን ከማሳወቅ የዘለለ ውጤት የለውም። ባለመብቱ የእርምጃውን ህጋዊነት ለመቃወም የሚችልበት ቀዳዳ የለም።
አንዳንድ ጊዜ የመሰማት መብት የሚፈቀደው ከውሳኔ በኋላ ይሆናል። የዘር አስመጪ፣ ላኪ፣ የዘር አምራች፣ አዘጋጅ፣ ጅምላ ሻጭ፣ አከፋፋይ ወይም ቸርቻሪ በዘር አዋጅ ቁ. 782/2005 አንቀጽ 21/1/ እና /2/ መሰረት የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀቱ በእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር ወይም በክልል ባለስልጣን ከመታገዱ ወይም ከመሰረዙ በፊት በድንጋጌው ላይ የተጠቀሱት በቂ ምክንያቶች እውነት ስላለመሆናቸው ለማስረዳትና ተቃራኒ ማስረጃ ለማቅረብ ዕድል አልተሰጠውም። ሆኖም ከውሳኔው በኋላ ውሳኔውን ለሰጠው አካል አስተዳደራዊ ቅሬታ የማቅረብ መብቱ በአንቀጽ 25/1/ ተጠብቆለታል። አመልካቹ በተሰጠው ምላሽ ካልረካ ቅሬታውን ለሚመለከታው የፍትሕ አካል ሊያቀርብ እንደሚችል በድንጋጌው ንዑስ አንቀጽ 2 ተመልክቷል።
የመሰማት መብት በዝምታ የታለፈባቸው ድንጋጌዎች
ምክንያቱ ባይታወቅም በዜጎች መብት ላይ ቀጥተኛ እና አሉታዊ ውጤት የሚያስከትሉ አንዳንድ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ሳይዘረጋላቸው በዝምታ ታልፈዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ስራ ፈቃድ የተሰጠው ኩባንያ አሰራሩ ለአደጋ ያልተጋለጠ፣ አስተማማኝና ጤናማ መሆኑን ለማረጋገጥ የኩባንያውን ዳይሬክተር፣ ዳይሬክተሮች ወይም ዋና ስራ አስፈፃሚ ከስራ ማገድ ወይም ማሰናበት ይችላል።c ባንኩ በምን ዓይነት ሁኔታዎችና በቂ ምክንያቶች እርምጃውን እንደሚወስድ ስልጣን በሰጠው አዋጅ ቁ. 807/2005 ላይ አልተመለከተም። በተጨማሪም እርምጃው የሚወሰድባቸው የኩባንያው ኃላፊዎች የተከሰሱበትን ጉዳይ ባንኩ ፊት ቀርበው ለማስረዳትና ማስተባበያ ማስረጃ ለማቅረብ በአጠቃላይ የመሰማት መብታቸው በአዋጁ አልተጠበቀም።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን በማስታወቂያ አዋጅ ቁ. 759/2004 አንቀጽ 31/3/ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር የውጭ ማስታወቂያን ሳይጨምር የአዋጁን ድንጋጌ በመተላለፍ የተሰራጨን ማንኛውንም ማስታወቂያ ይመረምራል፣ ያግዳል፣ የአፀፋ ማስታወቂያ እንዲወጣ ያዛል። ነገር ግን እርምጃውን ከመውሰዱ በፊት የማስታወቂያውን ባለቤት የመስማት ግዴታ አልተጣለበትም። በእርግጥ ለእርምጃው ምክንያት የሆኑት አብዛኛዎቹ ጉዳዮች ህሊናዊ ፍርድ የሚጠይቁ እንደመሆኑ ማስረጃ-ነክ ክርክሮች አይኖሩም። ሆኖም በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ተቃራኒውን ወገን መስማት የተዛባ አመለካከትን በማጥራት ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል። በተጨማሪም ባለስልጣኑ የማስታወቂያ ባለቤቶችን እይታ በጥልቀት ይረዳል። ለምሳሌ በአዋጁ ክልከላ ከተደረገባቸው ህግን ወይም መልካም ስነ ምግባር እንደሚጻረሩ የሚቆጠሩ ማስታወቂያዎች መካከል በአንቀጽ 7/6/ እና /8/ የሚከተሉት ተጠቅሰዋል፡
የህብረተሰቡን አካላዊና አእምሯዊ ጤንነትና ደህንነት ለጉዳት የሚያጋልጥ ድርጊት እንዲፈጸም የሚያነሳሳ ማስታወቂያ
ለመልካም ፀባይ ተቃራኒ የሆነ የጽሑፍ መልዕክት፣ ምስል፣ ስዕላዊ መግለጫ፣ ፊልም ወይም መሰል አቀራረብን የያዘ ማስታወቂያ
የአንድን ማስታወቂያ ይዘት በተጠቀሱት የተከለከሉ ተግባራት ስር ለመፈረጅ ጥንቃቄ የተሞላበት ህሊናዊ ፍርድ ይጠይቃል። በእንዲህ ዓይነቱ የውሳኔ አሰጣጥ ውጫዊ ሁኔታዎች ለምሳሌ የውሳኔ ሰጭው ግላዊ፣ ባህላዊና ስነልቡናዊ አቋም ይብዛም ይነስም ተጽዕኖ ያሳድራሉ። ስለሆነም ከአድልኦ የፀዳና ያልተዛባ ውሳኔ ለመስጠት የተቃራኒው ወገን አመለካከትና እይታ ማዳመጥ ወደጎን ሊተው አይገባም።
የአስተዳደር ውሳኔ አሰጣጥ በአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ
የአሜሪካው የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ አስተዳደራዊ ክርክር /adjudication/ መደበኛ ወይም ኢመደበኛ በሚል የተከፈለ ሲሆን መደበኛው ስርዓት በጣም ውስን በሆነ ጉዳዮች ላይ የተገደበና ተፈጻሚነቱም ህግ አውጭው ባመለከታቸው ሁኔታዎች ላይ ብቻ ነው።d በጀርመን እንዲሁ አስተዳደራዊ ክርክሮች መደበኛ እና ኢ-መደበኛ በሚል የሚከፈሉ ሲሆን መደበኛው ተፈጻሚ የሚሆነው ህግ አውጭው በግልጽ ካመለከተ ብቻ ነው።e በየትም አገር ቢሆን በቁጥር ከፍተኛውን ቦታ የሚይዘው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ኢ-መደበኛውን ስርዓት ይከተላል። በአሜሪካ 90 ፐርሰንት የሚሆኑት አስተዳደራዊ ጉዳዮች ውሳኔ የሚያገኙት በኢ-መደበኛ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ነው። በእንግሊዝ በዳኞች የዳበረው የመሰማት መብትንና የኢ-አድሎአዊነት መርህ አካቶ የያዘው የተፈጥሮ ህግ መሰረታዊ መርህ በሁሉም ውሳኔ ሰጭ አካላት ላይ ወጥ ተፈጻሚነት የለውም። በህግ ያልተቀመጠ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታ ባለመሆኑም ዳኞች እንደየሁኔታው እያጠበቡና እያሰፉ በትርጉም በአስተዳደር ውስጥ ኢመደበኛነት እንዲሰፍን አድርገዋል። ወጥነት የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ መገለጫ ባህርይ ስላለመሆኑና መደበኛው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት የኢ-መደበኛው ልዩ ሁኔታ እንደሆነ እንዲሁም ህግ አውጭው የአስተዳደር ውሳኔዎችን እንደ ዓይነታቸው፤ ውስብስብነታቸው፤ በመብት እና ጥቅም ላይ የሚያስከትሉት ክብደት እና ሌሎች ተገቢ መመዘኛዎችን በመለየት ከልል እስከ ጥብቅ የትኛውን ስነ-ስር ዓት መከተል እንዳለባቸው ሊወስን እንደሚገባ በዚህ መጽሐፍ (ክፍል 5.3 ልዩ ሁኔታዎችና የተፈጻሚነት ወሰን) በስፋት የተብራራ በመሆኑ መድገሙ አስፈላጊ አይሆንም። እዚህ ላይ የሚዳሰሰው አዲስ የወጣው የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ የኢ-መደበኛነትን ፅንሰ-ሀሳብ በምን መልኩ እንዲሁም እስከምን ደረጃ የህጉ አካል እንዳደረገው ይሆናል።
የአገራችን የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ ለሁሉም ተቋማት በሁሉም ሁኔታዎች ተፈጻሚ የሚሆን ወጥ እና መደበኛ ስርዓት ዘርግቷል። እንዲህ ዓይነቱ አካሄድ የአስተዳደር ተቋማት ሊሸከሙት ከሚችሉት በላይ ጫና መደረብ ነው።
ለመሆኑ መደበኛ ሲባል ምን ለማለት ነው? አንባቢ ግልጽ መረዳት ይኖረው ዘንድ በሚከተሉት ህጎች ላይ ያሉትን መደበኛ የሚባሉ የክርክር ሂደቶች ቀንጨብ አድርገን እናያለን።
የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁጥር 847/2006 ከአንቀጽ 38 እስከ 42
የፌደራል መንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ ስርዓት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 77/1994
የዓቃብያነ ህግ የዲሲፕሊን ክስ አቀራረብ፣ ማጣራትና ውሳኔ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት በተመለከተ የፌደራል የዓቃብያነ ህግ መተዳደሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁ 443/2011 ከአንቀጽ 91 እስከ 94 ድረስ የተዘረጋው ስርዓት
መደበኛው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት በመደበኛ ፍርድ ቤት የሚካሄደው ሙግት አምሳያ ነው። ጉዳዩን ሰምቶ አከራክሮ ፍርድ መስጠት ለፍርድ ቤቶች መደበኛ ስራቸው ነው። ስለሆነም እያንዳንዱ የክርክር ሂደት በዝርዝር በተጻፈ የስነ-ስርዓት ድንጋጌዎች ይመራል። ድንጋጌዎቹ ልዩነት ሳይደረግ በሁሉም ተከራካሪዎች ላይ ተፈጻሚነት አላቸው።
ሆኖም ለአንድ የአስተዳደር ተቋም ማከራከር ተጉዳኝ እንጂ ዋና ተግባሩ አይደለም። ተቋሙ የተቋቋመበት የራሱ የሆነ ዓላማና ተግባር አለው። ተልዕኮው ይህን ዓላማ በብቃት እና ውጤታማ በሆነ መንገድ ማሳካት ነው። ተቋሙ በህግ የተሰጠውን ተግባር ሲያከናውን በግለሰቦች መብትና ጥቅም ላይ አሉታዊ ውጤት ሊያስከትል የሚችል አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ይገደዳል። እንደ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሁሉ የተቋሙ ውሳኔ በማስረጃ የተደገፈ እና ህጉን መሰረት ያደረገ እና ፍትሐዊ ሊሆን ይገባል። ይህ በተግባር የሚረጋገጠው እርምጃ የሚወሰድበት ግለሰብ ወይም ድርጅት ጥፋተኛ እንዳልሆነና ተጠያቂነት እንደሌለበት በማስረጃ አስደግፎ ማስረዳት ሲችል ነው። በአግባቡ ማስረዳት ይችል ዘንድ ፍሬነገሩና ህጉ የሚጣራበት ይብዛም ይነስም የተወሰነ የክርክር ስርዓት መወሰን ያስፈልጋል። ስርዓቱ መደበኛ ከሆነ ፍርድ ቤት የሚከተለውን ስነ-ስርዓት ይመስላል። ይመስላል እንጂ ግን ግልባጭ አይደለም። የአስተዳደር ተቋም በውሳኔ አሰጣጥ ረገድ መደበኛውን የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት የሚከተል ከሆነ ሙሉ ጊዜና ሀብቱን የሚያጠፋው የተቋቋመበትን ዓላማ በማሳካት ሳይሆን በማከራከከር ብቻ ይሆናል። ከዚህ አንጻር መደበኛ በሚባል የአስተዳደር ክርክር ላይ ተፈጻሚነት የሚሆኑት የስነ-ስርዓት ቅደመ ሁኔታዎች ውስንና በይዘታቸውም ጠቅላላነት የሚስተዋልባቸው ናቸው።
በተቃራኒው ሂደቱ ኢ-መደበኛ ከሆነ በጣም ልል ከመሆኑ የተነሳ የክርክር ስርዓት ብሎ ለመጥራት እንኳን ይከብዳል። በዛ ላይ በይዘቱ እና በአፈጻጸሙ ከተቋም ተቋም ከውሳኔ ውሳኔ ሊለያይ ይችላል። ይህን በምሳሌ ለማስረዳት ያክል የግብርና ሚኒስቴር የሰጠውን የዕፅዋት አዳቃይ መብት ለመሠረዝ ሲወስን፦
•ሀ) ለባለመብቱ መብቱ ሊሰረዝ እንደሆነ በጽሑፍ ያሳውቃል፤
•ለ) ባለመብቱ ተቃውሞ ካለው የጽሑፍ ማስታወቂያ እንደደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ማስረጃ እንዲያቀርብ በጽሑፍ ያሳውቃል፤ እና
•ሐ) ተቃውሞ ቀርቦ ከሆነ ክርክሩን ሰምቶ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል
ይህንን እላይ ካየናቸው መደበኛ የክርክር ስርዓት ጋር ስናስተያየው ሚናቸው የተለያየ መርማሪና ከሳሽ እንዲሁም ጥፋትን የሚያስታውቅ የክስ አቤቱታ የለም። ባለመብቱ መብቱ ሊሰረዝ እንደሆነ ሚኒስቴር መ/ቤቱ የራሱን ማጣራት አድርጎ ህጉን አመሳክሮ አስቀድሞ ድምዳሜ ላይ ደርሷል። ለዚህም ነው የመከላከያ መልሱን ሳይሆን ማስረጃውን እንዲያቀርብ የተጠየቀው። ሚኒስቴሩ ውሳኔ የሚሰጠው ክርክሩን ሰምቶ ቢሆንም ተከራካሪ ወገኖች (ከሳሽና ተከሳሽ) የሉም። ስለሆነም ክርክሩን ሰምቶ ሲባል ባለመብቱ የሚያቀርበውን ተቃውሞ ሰምቶ ለማለት ነው። በሚኒስቴሩ ፊት ማስረጃ ከማቅረብና ተቃውሞ ከማሰማት የዘለለ የክርክር ስርዓት የለም።
በመደበኛው የፍርድ ቤት ክርክር ከክስ መሰማት በፊት የተለያዩ ጉዳዮችን የሚወስኑ በርካታ የስነ ስርዓት ድንጋጌዎች አሉ። በፍርድ ቤት ክርክር ተፈጻሚ የሚሆኑት የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች በባህርያቸው የማያወላዱ ግትር እንደመሆናቸው ለአስተዳደር ክርክር አይመቹም። በአንድ አገር ውስጥ የሚወጣ የአስተዳደር ህግ ውጤታማ አስተዳደርን ሳያሰናክል የዜጎችን መሰረታዊ የመሰማት መብት የሚያስጠብቅ ተለማጭ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት ይኖርበታል። ከዚህ አንጻር አዋጁ ሁለት ጉልህ ግድፈቶች ይታዩበታል። በአንድ በኩል የመሰማት መብትን ከክስ መሰማት ጋር አምታቶታል። በዚህ የተነሳ መሰረታዊ የሚባሉትን የመሰማት መብት ድንጋጌዎችን አልያዘም። በሌላ በኩል ተፈጻሚ የሚሆነውን ስርዓት እንደ ጉዳዮች ዓይነት /ማለትም እንደ አስተዳደራዊ ውሳኔው ዓይነት/ መደበኛ እና ኢመደበኛ ስነ ስርዓት መዘርጋት ቢኖርበትም አንድ ወጥ ቅድመ ሁኔታ በመደንገግ ሁሉንም በአንድ ሙቀጫ ወቅጧቸዋል። ይህ ደግሞ በቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥ እና ውጤታማ አስተዳደር ላይ የሚያስከትለው ግዙፍ ተደራራቢ ችግር በቀላሉ የሚገመት አይሆንም።
በአዋጁ የሚታዩ የውሳኔ አሰጣጥ አጀማመር ብዥታዎች
በመጀመሪያ ደረጃ ውሳኔ /initial decision/ ሆነ በቅሬታ ስርዓት /review decision/ የአስተዳደራዊ ክርክር የሚጀመረው ከማስታወቂያ ነው። በመጀመሪያው ውሳኔ ሰጭው ባለስልጣን ለባለጉዳዩ /ለተከሳሹ/ የክስ ማስታወቂያ ይሰጠዋል። በሁለተኛው ደግሞ የባለጉዳዩ የቅሬታ አቤቱታ ለውሳኔ ሰጭው አካል ይደርሰዋል። የክስ ሆነ የቅሬታ አቤቱታ ለሚመለከተው ወገን እንዲደርስ ግልጽ የሆነ የማስታወቂያ አሰጣጥ ስርዓት ሊኖር ይገባል። በዚህ መጽሀፍ በክፍል 5.3 እንደተመለከተው ማስታወቂያ ተከራካሪው እንዲቀርብ የሚሰጥ መጥሪያ ነው። በይዘቱ ባለጉዳዩ የቀረበበትን ክስ በሚገባ ተረድቶ መልሱን አዘጋጅቶ እንዲያቀርብ የሚያስችለው ሊሆን ይገባል።
የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጁ ከክስ መሰማት በፊት ያሉ ወሳኝ ሂደቶችን በዝምታ አልፏቸዋል። ሙሉ ትኩረቱን ያደረገው ባለጉዳዩ የአስተዳደር ጉዳይ በሚሰማበት ጊዜ በክርክ ሂደት ሁሉ ተገኝቶ ስለሚከናወነው የአስተዳደር ክርክር ብቻ ነው። በዚህ የተነሳ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓቱን ጎዶሎ አድርጎታል።
የቅድመ ክስ ማስታወቂያ ስርዓትን አስፈላጊነት በተመለከተ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአንድ ውሳኔ ላይ እንዳለው
The right to a hearing embraces not only the right to present evidence, but also a reasonable opportunity to know the claims of the opposing party and to meet them. The right to submit argument implies that opportunity; otherwise the right may be but a barren one.f
የፌደራል መንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ ስርዓት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 77/1994 በአንቀጽ 11 ላይ ክስን ስለማሳወቅ ከአዋጁ በጣም በተሻለ የሚከተሉትን ድንጋጌዎች ይዟል።
1. የዲስፕሊን ኮሚቴ ክስ የቀረበበት ሠራተኛ መልሱን ይዞ እንዲቀርብ የክሱን ጽሁፍና ማስረጃዎች ቅጅ አያይዞ የክስ ማስታወቂያ ይልክለታል።
2. የክስ ማስታወቂያው ክሱ የሚሰማበትን ቦታ፣ ቀንና ሠዓት የሚገልጽ ሆኖ ክሱ ከሚሰማበት ቀን ቢያንስ ከ 10 ቀናት በፊት ለተከሣሹ መድረስ አለበት።
3. ሠራተኛው ሊገኝ ባለመቻሉ ወይም ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆኑ የክስ ማስታወቂያውን ለመስጠት ያልተቻለ አንደሆነ በመሥሪያ ቤቱ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ተለጥፎ ለ15 ቀናት እንዲቆይ ይደረጋል።
የአዋጁ ችግር የክስ ማስታወቂያን የሚደነግግ ነጠላ ድንጋጌ አለመያዙ ብቻ አይደለም። በአጠቃላይ ከክስ መሰማት በፊት በዝርዝር መካተት የነበረባቸው የአስተዳደር ክርክር መሰረታዊ ድንጋጌዎች በሙሉ ተረስተዋል። የውሳኔ አሰጣጥ አጀማመር በተመለከተ አዋጁ ብዥታ ይነበብበታል። የውሳኔ አሰጣጥ አጀማመር በተመለከተ የሚስተዋለው መሰረታዊ ችግር መንስዔም ይኸው ነው።

Article 9 Rule of the Constitution


Article 9 Rule of the Constitution

አንቀጽ 9፡ የሕገ መንግሥት የበላይነት/Article 9 Rule of the Constitution

1- The constitution is the supreme law of the land. Any law, customary practice, or decision of a government body or authority that is inconsistent with this Constitution shall not apply.

2. Every citizen, government body, political association, other associations and their officials shall have the responsibility to uphold the Constitution and abide by the Constitution.

3. It is prohibited to hold public office in any capacity other than that provided for in this Constitution.

4. The international conventions ratified by Ethiopia are part of the country’s law.

አንቀጽ 9፡ የሕገ መንግሥት የበላይነት

1- ሕገ መንግሥቱ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ ነው። ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣ እንዲ ሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለሥ ልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም።

2- ማንኛወም ዜጋ፣ የመንግሥት አካላት፣ የፖ ለቲካ ድርጅቶች፣ ሌሎች ማኅበራት እን ዲሁም ባለሥልጣኖቻቸው፣ ሕገ መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለባቸው።

3- በዚህ ሕገንግሥት ከተደነገገው ውጭ በማናቸውም አኳኋን የመንግሥት ሥልጣን መያዝ የተከለከለ ነው።

4- ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምም ነቶች የሀገሪቱ ሕግ አካል ናቸው።

According to Article 8 of Article 2 of the Defense Forces Proclamation 1100/2019,


According to Article 8 of Article 2 of the Defense Forces Proclamation 1100/2019, “any recruited soldier shall perform a military oath as soon as he / she has completed his / her basic military training,” and Article 9 (2) states that “any member of the Armed Forces “It is an obligation to respect and uphold the constitution and the constitutional order,” he said.

1) Order:


In addition, Article 2, Article 9, Sub-Article (3) of the Proclamation stipulates that “a member of the Armed Forces shall have the obligation to abide by other laws, military laws, directives and directives of the country.”


(B) Hierarchy of Laws:


1) Constitution:
Article 9 (1) of the FDRE Constitution states: “The Constitution is the supreme law of the land. Any law, customary practice, or decision of a government body or authority which is inconsistent with this Constitution shall not apply.” The government declares that not only the supreme law of the country but also any order, decision, regulation, proclamation, etc. of any government official is unconstitutional.


In any case, it means that a member of the military will only obey decisions, orders, and directives that do not conflict with the Constitution. As stated in Article 9 (1) of the Constitution, the order or directive of any government official, executive body and head shall not be enforced if it violates the basic principles of the Constitution.


2) Subordinate Legislations:


If the lower laws, such as the proclamations of the parliament, the regulations of the Council of Ministers, the directives of the Ministry of Defense, and the orders of the Chief of Staff are unconstitutional, then the constitution should be given priority.


(C) Order Vs. Oath?


Because the constitution is the rule of law and members of the military are sworn in first to uphold the constitution; On the other hand, because proclamations, rules, directives and orders are enforceable under the Constitution, when there is a conflict of law, they are more loyal to the Constitution and its conscience than to any directive, regulation or other law.


(D) International Norms:


When the army is ordered to intervene in countries of instability and violence, the army faces three basic conflicts of conscience:


In The insoluble moral dilemma of harming a civilian who is promised protection




ስጋት Consequences of international military tribunal liability for damages;


● On the other hand, disobedience to the superior order can lead to a reduction in rank, dishonorable discharge and even fear of being tried in a martial court.



5) Fortification: Quartering:


Conflict between government and citizens, civil strife, civil unrest, as the experience of some countries shows, by keeping members of the military in a fort or in a separate area, neutral / passive, avoiding unnecessary bloodshed, peaceful, legal and inclusive lasting One of the ways to build consensus is to sit in a quarter.

የአስተዳደር ጉባዔስያሜና ትርጓሜ


የአስተዳደር ጉባዔ


ስያሜ አስተዳደር ጉባዔ (Administrative Tribunal) ከመደበኛ ፍርድ ቤት ውጭ ያለ ገለልተኛ የዳኝነት አካል ነው። ከተግባራዊ እይታ አንፃር ከመደበኛ ፍርድ ቤትና ከአስተዳደር መስሪያ ቤት ከፊል ባህሪያትን ይጋራል። ሁለት ባህሪያትን በአንድ ጊዜ ቀይጦ በመያዙ ሙሉ በሙሉ ‘እዚህ ወይም እዚያ’ ብሎ መፈረጅ ይከብዳል። ከፊል ጎኑ አስተዳደራዊ ከፊሉ ደግሞ ዳኝነታዊ በመሆኑ ቁርጥ ያለ መደብ የለውም።a
ይህን ድርብ መልኩን የሚያንፀባርቅ ትርጓሜ ከማየታችን በፊት ‘የአስተዳደር ጉባዔ’ የሚለው አገላለጽ ከቋንቋ አጠቃቀም አንጻር በዚህ መጽሐፍና በሌሎች አገራት ግልጋሎት ላይ የዋለበትን መንገድ በጥቂቱ ማውሳት ያስፈልጋል። በአገራችን በተለምዶ ‘የአስተዳደር ፍርድ ቤት’ ስንል በእንግሊዝ፣ በአውስትራሊያና በሌሎች አገራት Administrative Tribunal በመባል የሚታወቀውን ከላይ የተጠቀሰውን ከመደበኛ ፍርድ ቤት ውጭ ያለ አስተዳደራዊ ክርክሮችን ለመዳኘት የተቋቋመ አካል ማለታችን ነው። ሆኖም አማርኛውን ከእንግሊዝኛው ጋር ስናዛምደው የአስተዳደር ፍርድ ቤት እና Administrative Tribunal አቻ መልዕክት አያስተላልፉም። የአስተዳደር ፍርድ ቤትን በትክክል የሚገልጸው እንግሊዝኛ Administrative Court ሲሆን የእንግሊዝኛውን ‘Administrative Tribunal’ የሚወክል የአማርኛ ቃል ደግሞ ‘የአስተዳደር ጉባዔ ነው።
Administrative Court በእንግሊዝ አጣሪ ዳኝነት ስልጣን ያለውን የከፍተኛውን ፍርድ ቤት የሚጠቁም ሲሆን ‘የአስተዳደር’ የሚለው ቅጥያ የተጨመረበት በአጣሪ ዳኝነት (Judicial Review) ስልጣኑ እንጂ ከአስተዳደሩ (ከስራ አስፈፃሚው) የመንግስት አካል ጋር ቅርበት ሆነ ግንኙነት ስላለው አይደለም። ፍርድ ቤቱ ሙሉ በሙሉ መደበኛ ፍርድ ቤት ነው። በጀርመን ‘Administrative Court’ የሚለው መጠሪያ ከታች ወደ ላይ ራሳቸውን ችለው ከተቋቋሙት አምስትb ዓይነት መደበኛ ፍርድ ቤቶች መካከል አንደኛው ነው።c ወደ ፈረንሳይ ስንመጣ Administrative Court በብዙ መልኩ ‘ፀጉረ-ልውጥ’ ፍርድ ቤት ነው። በአወቃቀሩ የሥራ አስፈፃሚው አካል ሲሆን በዳኝነት ተግባሩ ከመደበኛው ፍ/ቤት ጋር የሚስተካከል ነጻነት ያለው ገለልተኛ የዳኝነት ተቋም ነው። በአደረጃጀቱ የወንጀልና የፍትሐብሔር ጉዳዮችን እንደሚያዩት መደበኛ ፍርድ ቤቶች የመጀመሪያ ደረጃ፣ የይግባኝ ሰሚ እና የሰበር ስልጣን ያላቸው የፍርድ ቤት ሰንሰለቶች አሉት።
በዚህ መጽሐፍ ‘የአስተዳደር ጉባዔ’ የሚለው አገላለጽ ጥቅም ላይ የዋለው በእንግሊዝ፣ በጀርመንን አሊያም በፈረንሳይ ያለውን Administrative Court በማመልክት ሳይሆን በተቃራኒው የእንግሊዝኛውን Administrative Tribunal አቻ ትርጉም በመወከል ነው።
ወደ ትርጓሜው ስንመጣ ምሁራን ከተግባራቱ አንጻር በሚከተለው መልኩ ገልጸውታል።
Broadly, a tribunal is an adjudicative body, empowered to hear and decide disputes in particular circumstances. Tribunals are sometimes referred to as court substitutes, in that they have the power to make legally enforceable decisions, but they are regarded as having the advantages over courts of speed, cheapness, informality, and expertise.d
Tribunal ቃሉ ሲተረጎም ‘ችሎት’ ወይም ‘ዳኛው የሚያስችልበት ቦታ’ (seat of the judge)፣ ጉባዔ፣ ሸንጎ ማለት ነው። ስለሆነም የአስተዳደር ጉባዔ (Administrative Tribunal) ማለት በህግ ተለይተው የተደነገጉ የአስተዳደር ክርክሮችን ሰምቶ የመወሰን ስልጣን ያለው የዳኝነት አካል ማለት ነው። በስልጣኑ ስር የሚያያቸው ጉዳዮች በዋነኛነት በግለሰብና በመንግስት መካከል የሚነሱ ክርክሮችን ቢሆንም አልፎ አልፎ በግለሰቦች መካከል የሚፈጠሩ ክርክሮችን (ለምሳሌ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ) ይዳኛል።
አስፈላጊነት እና ጠቀሜታ
እንደ ፕሮፌሰር ዌድና ፎርሲይዝ እይታ አስተዳደራዊ ደንብና መመሪያ የመደንገግ ስልጣን የአስተዳደር ህግ ዋነኛ መገለጫ ነው።e የአስተዳደር ጉባዔዎች ከሚሰጡት ግልጋሎትና እያሳዩት ካለው ፈጣን ዕድገት አንጻር በሁለተኛነት የህጉ መገለጫ አድርገን ብንወስዳቸው አንሳሳትም። እነዚህ የዳኝነት ተቋማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በቁጥርና በዓይነት እየበዙ መምጣታቸውና የዳኝነት ስልጣናቸው ክልል እየሰፋ መሄዱ የአስተዳደር ህግ ትልቁ ስኬት እንደሆነ የመስኩ ምሁራን በአፅንኦት የሚገልፁት ጉዳይ ሆኗል።f ፒተር ኬን ይህን ስኬት እንደሚከተለው ይገልጸዋል።
One of the most significant, large-scale and enduring constitutional developments of the past 150 years has been the creation of a set of governmental institutions known, in major common law jurisdictions outside the United States, as ‘tribunals’.g
የአስተዳደር ጉባዔዎች የመፈጠራቸው ዋነኛ ምክንያት ዜጎች በአነስተኛ ወጪና በአጭር ጊዜ ውስጥ የተፋጠነ ፍትህ እንዲያገኙ ለማስቻል ነው። በብዙ አገራት (ለምሳሌ በእንግሊዝና አውስትራሊያ) እነዚህ የዳኝነት አካላት ከሞላ ጎደል ይህን ዓላማቸውን ከግብ በማድረስ ውጤታማ ሆነዋል። በህግ የሚሰጣቸው የዳኝነት የስልጣን ክልል ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች አንጻር ውስን ቢሆንም በመንግስትና በግለሰብ ብሎም በግለሰቦች መካከል የሚነሱ ጉዳዮችን ለምሳሌ በጤና፣ በትምህርት፣ በጨረታ፣ በፈቃድ አሰጣጥ፣ ስደተኞችና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች በአጭር ጊዜ ውስጥ እልባት በመስጠት እንደ አማራጭ የሙግት መፍቻ መንገድ ውጤታማና ፍሬያማ ለመሆን በቅተዋል።
ስለ አስተዳደር ጉባዔ ስኬትና ውጤታማነት ስንነጋገር ኢትዮጵያ ውስጥ የምናገኘው እውነታ የዚህ ተቃራኒ ነው። ለዚህም ብዙ ምክንያቶች ይጠቀሳሉ። በዋነኛነት ግን ሁለቱን ማንሳቱ አግባብነት አለው። የመጀመሪያው ዋነኛ ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ የአስተዳደር ጉባዔዎች በፍትህ ስርአቱ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መዘንጋታቸውና ህገ መንግስታዊ ቦታቸው ጥርት ብሎ አለመታወቁ በዚህም ምክንያት ወጥ፣ ነፃና ውጤታማ አደረጃጀት የሌላቸው መሆኑ ነው።h
በሁለተኛነት ስለ አስተዳደር ፍርድ ቤት ያለው ግንዛቤና እይታ ራሳቸውን እንደቻሉ የፍትህ ስርዓቱ ተጓዳኝ ተቋማት ሳይሆን በአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ስር ያሉ ቅሬታ ሰሚ አካላት ተደርገው መቆጠራቸው ነው።
ከጠቀሜታቸው አንጻር በአነስተኛ ወጪ፣ ቀላል በሆነ የክርክር ስነ ስርዓት፣ ፈጣን የአስተዳደር ፍትህ በመስጠት ለዜጎች የሚያበረከረቱት አስተዋፅኦ እጅጉን የጎላ ነው።i በተለይ በመንግስትና በግለሰብ መካከል የሚነሱ እጅግ በርካታ አስተዳደራዊ ክርክሮችን በተሻለና ውጤታማ በሆነ መንገድ በመፍታት የፍርድ ቤቶችን ጫና ያቃልላሉ።
በፍርድ ቤት ያለው የክስ ሂደት የተንዛዛ ከመሆኑም ባሻገር ከፍተኛ ወጪ ስለሚጠይቅ በተለይ ለድሃው የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ ፍትህ ማጎናፀፍ ይሳነዋል። ይህም ከአስተዳደሩ ጋር በተያያዘ ለሚነሱ ክርክሮች ሁለት ጉዳቶችን ያስከትላል። በአንድ በኩል በተንዛዛ ክርክር ምክንያት ውጤታማ አስተዳደር አይኖርም። በሌላ በኩል ዜጎች በፍትህ እጦት ይንገላታሉ።
ሌላው ጠቀሜታ ልዩ ዕውቀት ያካበተ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ የሙያ ክህሎትን ማጎልበታቸው ላይ ነው። አብዛኛዎቹ ጉባዔዎች የሚያዩት ጉዳይ ውስን ከመሆኑ አንጻር ተደጋጋሚ ጉዳዮች ቀርበው መወሰናቸው የአስተዳደር ዳኛው በመስኩ ሰፊ ተሞክሮና ዕውቀት እንዲቀስም ያስችለዋል። በተጨማሪ የአስተዳደር ክርክሮችን የሚያየው ዳኛ በቦታው ሲሾም ከህግ ዕውቀት በተጨማሪ ስለሚያየው ጉዳይ ልዩ እውቀት ስለሚኖረው የህግ ዕውቀት ብቻ ኖሮት የተለያዩ ዓይነት ጉዳዮችን ከሚያየው የመደበኛ ፍርድ ቤት ዳኛ በተሻለ መልክ ውጤታማ ውሳኔ ለመስጠት ተመራጭ ያደርገዋል። የአስተዳደር ዳኞች ከህግ ዕውቀት በተጨማሪ ለጉዳዩ የሚያስፈልገውን ሙያ የጨበጡ በመሆኑ በክርክር ወቅት ሊነሱ የሚችሉ ህግ ነክ ያልሆኑ ጭብጦችን በቀላሉ ተረድተው ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያስችላቸዋል።
ለማጠቃለል ያህል የሚከተሉትን ነጥቦች እንደ አስተዳደር ጉባዔ ጠቃሜታዎች መጥቀስ እንችላለን።
ጉዳዩን ሰምቶ ለመወሰን አጭር ጊዜ የሚፈጅ በመሆኑ ያለ ረጅም ቀጠሮ ፈጣን ውሳኔ ይሰጣል።
በአስተዳደር ክርክር አብዛኛውን ጊዜ ጠበቃ ማቆም አስፈላጊ ባለመሆኑና መዝገብ ለማስከፈት መጠነኛ ወይም ከነጭራሹ ክፍያ ስለማይኖር የተከራካሪዎችን ወጪ ይቆጥባል።
በቦታው የሚቀመጠው የአስተዳደር ዳኛ ለጉዳዩ ልዩ እውቀት ያለው በመሆኑ የተሻለ ውሳኔ ይሰጣል።
መደበኛውን ስነ ስርዓትና የማስረጃ ህግ የመከተል ግዴታ ሳይኖርበት እንደየሁኔታው ተፈጻሚ የሚሆኑ ኢ-መደበኛ የስነ ስርዓት ደንቦች ላይ ተመርኩዞ ክርክሩን በመምራት የተንዛዛ የክርክር ስርዓትን ያስቀራል።
አስፈላጊነቱና ጠቀሜታው እንዳለ ሆኖ ደካማ ጎኑንም በጥቂቱ መዳሰሱ ጥቅምና ጉዳቱን ከመመዘን አንጻር ፋይዳው የጎላ ነው። ከደካማ ጎኖች መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው።
በጊዜ ሂደት የተወሰኑ የአስተዳደር ጉባዔዎች መለያቸው የሆነውን ኢ-መደበኛ ስነ ስርዓት በመተው ጥብቅ የስነ ስርዓት ደንቦች የሚከተሉ ፍርድ ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል።
በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በስራ አስፈፃሚው እጅ ስለሚወድቁ ነፃና ገለልተኛ አካላት አይደሉም።
አንዳንዶቹ የሰለጠነ የሰው ኃይል የላቸውም። ለውሳኔያቸው በቂ ምክንያት አይሰጡም።
በአስተዳደር ፍርድ ቤት ተከራካሪ የሆነ ባለ ጉዳይ የህግ እርዳታ አያገኝም።
መለያ ባህሪያት
የአስተዳደር ጉባዔን ከመደበኛው ፍርድ ቤት ጋር የሚያመሳስለው ነጥብ ቢኖርም ከፊል ጎኑ አስተዳደራዊ እንደመሆኑ የራሱ ባህርያት አሉት። በአጠቃላይ መለያ ተደርገው ሊወሰዱ የሚችሉ መሰረታዊ መገለጫዎች የሚከተሉት ናቸው።
በህግ መቋቋም
የአስተዳደር ጉባዔ ሊቋቋም የሚችለው ፓርላማው (የተወካዮች ምክር ቤት) በሚያወጣው አዋጅ ነው። ህግ አውጪው አንድን የአስተዳደር ፍርድ ቤት ሲያቋቁም ፖሊሲን መሰረት ያደረገ ምክንያት ተንተርሶ ሲሆን ይህም የመንግስት አስተዳደርን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ ወይም ዜጎች በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ርትዐዊ ዳኝነትና አስተዳደራዊ ፍትህ እንዲያገኙ አማራጭ የሙግት መፍቻ መንገድ ማቅረብ ሊሆን ይችላል። በዚህ መሰረት በኢትዮጵ ውስጥ የሚገኙ የአስተዳደር ጉባዔዎች ማቋቋሚያ አዋጅ ከፊሎቹ እንደሚከተለው ይዘረዘራሉ።
የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ
ስለ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ የወጣ አዋጅ ቁ. 1156/2011 አንቀጽ 145/1/ እና /2/
የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
የፌደራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁ. 983/2008 አንቀጽ 86/1/
የመንግስት ሰራተኞች አስተዳደር ፍ/ቤት
የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁ.1064/2010 አንቀጽ 79
የማህበራዊ ዋስትና ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ
የመንግስት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁ. 714/2003 አንቀጽ 57
የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ይግባኝ ሰሚ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት
የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁ. 813/2006 አንቀጽ 33
የስደተኞች ጉዳይ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ
የስደተኞች ጉዳይ አዋጅ ቁ. 1110/2011 አንቀጽ 17
የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ቅሬታ ሰሚ ጉባዔ
የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁ. 818/2006
የአእምሯዊ ንብረት ትሪቡናል
የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ (ማሻሻያ) አዋጅ ቁ. 872/2007
የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ
የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁ. 847/2006 አንቀጽ 48
የከተማ ቦታ ማስለቀቅና የካሳ ጉዳዮች ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ
የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የወጣ አዋጅ ቁ. 721/2004 አንቀጽ 30
የፌደራል ዓቃብያነ ሕግ አስተዳደር ጉባኤ
የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 943/2008 አንቀጽ 12/1/
የህንፃ ግንባታ ይግባኝ ሰሚ ቦርድ
ደንብ ቁ. 243/2003 የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህንፃ ደንብ አንቀጽ አንቀጽ 21/1/
የምርት ገበያ ባለስልጣን
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ቁ. 551/1999 አንቀጽ 7
የኢንቨስትመንት ቦርድ
ደንብ ቁ. 313/2006 የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድንና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ
የመንግስት ግዥና አቤቱታ አጣሪና ዉሳኔ ሰጪ ቦርድ
የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 ዓ.ም አንቀጽ 70/1/
የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማኅበር የክርክር አወሳሰን ኮሚቴ
የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማኅበራት አዋጅ ቁጥር 841/2006 አንቀጽ 56
የከተማ መሬት ይዞታ ማረጋገጥ ቅሬታ ሰሚ ጉባዔ
የከተማ መሬት ይዞታ ማረጋገጥ እና ምዝገባ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 324/2006 አንቀጽ 22
የክሪፕቶ መሠረተ ልማት ካውንስል
የኤሌክትሮኒክ ፊርማ አዋጅ ቁ. 1072/2010 አንቀጽ 50
አስገዳጅ ውሳኔ
የአስተዳደር ጉባዔዎች ክርክሩን ሰምተው የሚሰጡት ውሳኔ እንደማንኛውም የመደበኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ተፈፃሚነት ያለው አስገዳጅ ወይም አሳሪ ውሳኔ ነው። ተፈፃሚና አሳሪ የሆነ ውሳኔ የማይሰጥ አካል እንደ አስተዳደር ጉባዔ ለመቁጠር ያስቸግራል። ስለሆነም የዲሲፕሊን ኮሚቴዎችና ሌሎች በህግ ወይም በየመ/ቤቱ የሚቋቋሙ አጣሪና መርማሪ አካላት ከአስተዳር ጉባዔ ማእቀፍ ውጪ ናቸው። የጠበቆች ዲሲፕሊን ጉባዔj ከአገር ማስወጫ ትዕዛዝ ላይ አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴk የይቅርታ ቦርድl የጤና ሙያ ስነ ምግባር ኮሚቴm የቱሪስት አገልግሎት ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴn የአመክሮ ኮሚቴo የደህንነተ ህይወት ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴp ሁሉም የመወሰን ስልጣን ላለው ሚኒስቴር ወይም የበላይ አካል የውሳኔ ሀሳብ ከማቅረብ በስተቀር አስገዳጃ ውሳኔ ማስተላለፍ የማይችሉ በመሆኑ እንደ አስተዳደር ጉባዔ አይፈረጁም።
ስነ-ስርዓት
የአስተዳደር ጉባዔ የመቋቋሙ ዐቢይ ምክንያት በአነስተኛ ወጪና ቀላል የክርክር ስርዓት ቀልጣፋ ፍትህ መስጠት በመሆኑ በመደበኛው ፍ/ቤት የክርክር ሂደት ተፈፃሚ የሚሆኑት ጥብቅና የማያወላዱ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ አይሆኑበትም። ሆኖም ለመሰረታዊ የስነ-ስርዓት ደንቦች ተገዢ መሆን አለበት።
ተፈጻሚ የሚሆኑት የስነ-ስርዓት ድንጋጌዎች አልፎ አልፎ በማቋቋሚያ አዋጁ ላይ የሚዘረዘሩ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ግን ጉባዔው የራሱን ስነ-ስርዓት በውስጠ ደንብ እንዲወስን ስልጣን ይሰጠዋል። ከአነስተኛ መሰረታዊ የስነ-ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች መካከል የተከራካሪ ወገኖች ክርክርና ማስረጃ የማቅረብ፣ (የመሰማት መብት) አድሎአዊ ያልሆነ ውሳኔ ወይም ፍትህዊ ውሳኔ መስጠት እንዲሁም በማስረጃና በምክንያት የተደገፈ ውሳኔ መስጠት በዋናነት ይጠቀሳሉ።
የአስተዳደር ጉባዔን ከመደበኛው ፍ/ቤት በስነ-ስርዓት ረገድ የተለየ የሚያደርገው ለፍትሀዊ ስነ-ስርዓት ህጉ ተገዢ ያለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ባመቸው መንገድ የሚመራበትን ስነ-ስርዓት በራሱ ለመወሰን ስልጣን የተሰጠው መሆኑ ጭምር ነው። ይህም በተለዋዋጭ ሁኔታዎች ውስጥ የተለያየ ስነ-ስርዓት ተፈፃሚ በማድረግ እንደየሁኔታው እንዲለጠጥ ይረዳዋል። ተለጣጭነቱ ግን ወጥ አሰራርን ጨርሶ በማጥፋት ወደ በዘፈቀደ አካሄድ የሚያመራ መሆን የለበትም። ከጉዳይ ጉዳይ ቢለያይም በተለጣጭነት እና ወጥ አሰራር መካከል ሚዛኑን የሚጠብቅ መስመር ሊኖር ይገባል። ጠቅለል ባለ አነጋገር የመደበኛ ፍ/ቤቶች የማያወላዳ ግትር የስነ-ስርዓት አካሄድ በአስተዳደር ፍ/ቤቶች ተፈፃሚ አለመሆኑ በአካሄዳቸው ተለጣጭነት ውጤታማ እንዲሆኑ የተመቻቸ እድል ይሰጣቸዋል።
የዳኞች ሚና
በስነ-ስርዓት ረገድ በኮመን ሎው እና ሲቪል ሎው አገራት መካከል ያለው የመርማሪ (inquistiorial) እና የሙግታዊ (adversarial) አቀራረብ የአስተዳደር ጉባዔና የመደበኛ ፍ/ቤት የልዩነት ነጥብ ተደርጐ ይወሰዳል። በሁለቱ የህግ ስርዓቶች ጉባዔዎች በጉዳዩ ወይም በክርክሩ ላይ ካላቸው ቀጥተኛ ተሳትፎ አንጻር አካሄዳቸው የመርማሪነት እንደሆነ ስምምነት አለ። ከስምምነቱ ባሻገር ብዙዎቹ የመስኩ ባለሙያዎች የአስተዳደር ጉባዔ ይህን መርማሪ አካሄድ መከተል እንዳለበት ጠንካራ መከራከሪያ ያቀርባሉ።
እንደ ፒተር ሌይላንድ እና ቴሪውድስ ገለጻ፤
የአስተዳደር ጉባዔ መርማሪ የስነ-ስርዓት አቀራረብ መከተል ይኖበታል። ይህ ሲሆን ነው በጉዳዩ ላይ በቀጥታ ምርመራ በማድረግ ፍትህ መሰራቱን ማረጋገጥ የሚችለው።
መርማሪ በሆነው አካሄድ እውነትን ፈልፍሎ ማውጣት ለተከራካሪ ወገኖች ብቻ የሚተው ሳይሆን ችሎቱን የሚመራው ዳኛም በንቃት ይሳተፍበታል። ይህ መርማሪ የክርክር አመራር ስርዓት በመደበኛው የፍትሐ ብሔር ሙግት ላይም የሚታይ ቢሆንም በገዘፈ መልኩ በተጨባጭ የሚንፀባረቀው ግን በአስተዳደር ጉባዔ በሚካሄዱ ክርክሮች ላይ ነው።
ቁጥብነት
ቁጥብነት የአስተዳደር ጉባዔ ዋነኛ መገለጫው ነው። የክርክር ሂደቱ እንደ መደበኛው ፍ/ቤት ከፍተኛ ወጪን አይጠይቅም። ተከራካሪ ወገኖች ለሚያቀርቡት አቤቱታ በመደበኛው ታሪፍ መሰረት ዳኝነት አይከፍሉም። አብዛኛውን ጊዜ የጠበቃ ውክልና አስፈላጊ ስለማይሆን ተጨማሪ ወጪ አይኖርም። ውሳኔ ከተሰጠም በኋላ ወጪና ኪሳራ በማቻቻል የሚታለፍ ሲሆን አልፎ አልፎ አነስተኛ ኪሳራ ሊወሰን ይችላል።
ስልጣንና ተግባር
የአስተዳደር ጉባዔዎች የዳኝነት የስልጣን ክልል (Judicial Jurisdiction) ጠባብና በህግ ተለይተው በተጠቀመጡ ውሱን ጉዳዮች ላይ ብቻ የተገደበ ነው። በአንጻሩ መደበኛ ፍ/ቤቶች እርስ በርሳቸው የይዘት ቅርበትና ዝምድና የሌላቸውን የተለያዩ የህግ ክፍሎችን የሚመለከቱ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ስልጣን አላቸው። ጠባብ የሆነው የዳኝነት ስልጣን ልዩ እውቀትን በማጐልበት ረገድ የጐላ አሰተዋጽኦ ያበረክታል። ለምሳሌ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የዳኝነት ስልጣን በአሰሪና ሰራተኛ መካከል በሚነሱ የወል የስራ ክርክሮች ላይ ብቻ ነው።q የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን እንዲሁ የግብር አሰባሰብና ጉምሩክን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ብቻ የሚያይ ሲሆን የማህበራዊ ዋስትና ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ከጡረታ መብትና ጥቅም ጋር በተያያዘ የዳኝነት ስልጣን አለው።
ምንም እንኳን የጉባዔዎች የዳኝነት ስልጣን በጥቅሉ ሲቀመጥ ጠባብ ቢመስልም በስራቸው ከሚወድቁት ጉዳዮች ብዛትና ከሚነሱት ጭብጦች ዓይነት አንጻር ስልጣናቸው ትንሽ የሚባል አይደለም። ለአብነት ያህል የማህበራዊ ዋስትና ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ምንም እንኳን የስልጣኑ ክልል የጡረታ መብትና ጥቅም የሚመለከቱ ጉዳዮች ቢሆንም ጉባዔው በኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ማንኛውም ጡረተኛ የሚያቀርበውን ይግባኝ ስለሚሰማ በአይነት ሆነ በቁጥር በርካታ ጉዳዮችን ያስተናግዳል።
ከዳኝነት ስልጣን በተጨማሪ በክርክሩ ሂደት የሚኖረው ስልጣን ከባህርያቱ አንጻር መጠቀስ ያለበት ጉዳይ ነው። የአስተዳደር ጉባዔ ከፊል የዳኝነት አካል እንደ መሆኑ ከሞላ ጐደል መደበኛ ፍርድ ቤት የሚኖሩትን ስልጣንና ተግባራት ይጋራል። ስለሆነም በማቋቋሚያ አዋጅ ላይ ተለይቶ በግልፅ ቢመለከትም ባይመለከትም እንደ ማንኛውም ፍ/ቤት ተከራካሪ ወገኖችና ምስክሮች እንዲቀርቡ ወይም ቃላቸውን እንዲሰጡ የማድረግ፣ የመሀላ ወይም የማረጋገጫ ቃል የመቀበል፣ ለክርክሩ በማስረጃነት አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች ከሚመለከተው ሰው ወይም ድርጅት እንዲቀርቡ የማድረግ ብሎም በማናቸውም ድርጅት ውስጥ ገብቶ አስፈላጊ መረጃዎችን የመሰብሰብና ምስክሮችን የመስማት የመሳሰሉ ተግባራትን ለማከናወን ስልጣን አለው። በተጨማሪም በክርክሩ ወቅት የሚያስተላልፋቸው ትእዛዞችና ውሳኔዎች አስገዳጅ ተፈጻሚነት አላቸው።
የእነዚህ ባህሪያት መኖር ከመደበኛ ፍ/ቤት ጋር በተያያዘ ለሚነሱ ሁለት ጭብጦች የጠራ መልስ ይሰጠናል። የመጀመሪያው በክርክር ሂደት ፍ/ቤት የመድፈር ውጤትን ይመለከታል። የአስተዳደር ጉባዔ በያዘው ጉዳይ ላይ በክርክር ወቅት የፍ/ቤት መድፈር ወንጀል በተፈጸመ ጊዜ እንደ መደበኛ ፍርድ ቤት ወዲያውኑ ቅጣት ማስተላለፍ ይችላል? ለሚለው ጥያቄ ዳኝነታዊ የሆነው ባህርዩ አዎንታዊ መልስ ይሰጠናል። በወንጀል ህግ አንቀጽ 449 ላይ የተመለከተው ፍ/ቤትን የመድፈር ወንጀል ከሚያቋቁሙት ህጋዊ ክፍሎች መካከል በድንጋጌው ላይ ከተመለከቱት ድርጊቶች መኖር በተጨማሪ ድርጊቱ በፍ/ቤት፣ ምርመራ ወይም የዳኝነት ስራ በሚከናወንበት ወቅት መሆን አለበት። የአስተዳደር ጉባዔ በከፊልም ቢሆን ዳኝነታዊ ስልጣን ያለው የዳኝነት አካል እንደመሆኑ የጉባዔው ዳኛ ላይ ማፌዝ፣ መዛት፣ መሳደብ ወይም በማናቸውም መንገድ ስራውን ማወክ የፍ/ቤት የመድፈር ወንጀል ነው። ስለሆነም ድርጊቱ በተፈፀመ ጊዜ ዳኛው ወዲያውኑ በጥፋተኛው ላይ ቅጣት ሊወስንበት ይችላል።
በሁለተኛነት ተያይዞ የሚነሳው ጭብጥ በጉባዔ ፊት ሀሰተኛ ቃል ወይም ምስክርነት መስጠት በወንጀል የማስቀጣቱ ሁኔታ ነው። በወንጀል ህግ አንቀጽ 425 እና 453 ላይ ተከራካሪ ወገን የሚሰጠው ሀሰተኛ ቃል እና ሀሰተኛ የምስክርነት ቃል፣ አስተያየት ወይም ትርጉም በመደበኛ ፍ/ቤት ፊት ብቻ ሳይሆን የዳኝነት ነክ ስልጣን ባለው አካል ፊት የተፈፀመ ከሆነ በወንጀል ያስቀጣል። ምንም እንኳን የወንጀል ህጉ በግልፅ ስለ አስተዳደር ጉባዔ ባያወራም ‘የዳኝነት ነክ ስልጣን ያለው አካል’ ከፊል የዳኝነት ስልጣን ያለውን የአስተዳደር ጉባዔን እንደሚጨምር ግልፅ ነው።
አመዳደብ
ጉባዔዎች እንደ ቅርጻቸው፣ ስልጣናቸውና አወቃቀራቸው የተለያየ መልክ ይዘው ይቋቋማሉ። አንድ የመስኩ ምሁር ከዳኝነት ስልጣናቸው እና መዋቅራቸው አንጻር በአራት መንገዶች እንደሚከተለው ይከፋፍላቸዋል።r ይኸውም፤
ልዩ (ውስን) እና ሁሉን አቀፍ (ሁለገብ ወይም ዘርፈ ብዙ)
ነጠላ እና ድርብ (አንድ እርከን እና ሁለት እርከን)
የግል እና የአስተዳደር ክርክር ሰሚ
የመጀመሪያ ደረጃ እና አጣሪ
ልዩ እና ሁሉን አቀፍ
ልዩ የአስተዳደር ጉባዔ ስልጣኑ በአንድ ውስን ዘርፍ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። በእኛ አገር የሚገኙት ጉባዔዎች ሁሉም በልዩ የአስተዳደር ጉባዔ ስር ይመደባሉ። ለምሳሌ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የሚያያቸው ጉዳዮች የወል ስራ ክርክሮችን ብቻ ሲሆን የመንግስት ሰራተኞች የአስተዳደር ፍ/ቤት በበኩሉ በመንግስት ሰራተኞች የሚቀርቡ የስራ ክርክር ቅሬታዎችን ተቀብሎ ዳኝነት ይሰጣል።
ሁሉን አቀፍ የሚባለው ደግሞ በአንድ ጉዳይ ላይ ሳይወሰን ተቀራራቢነት የሌላቸው ዘርፈ ብዙ የአስተዳደር ክርክሮችን ለማየትና ለመዳኘነት ሰፊ ስልጣን ተሰጥቶት የሚቋቋም የአስተዳደር ጉባዔ ነው። ስለሆነም ከንግድ ፈቃድ መሰረዝ አንስቶ እስከ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ መባረር፣ የንግድ ድርጅት መዘጋት፣ ከአገር የማስወጣት እርምጃ፣ የጡረታ መብት አወሳሰን ወዘተ…ሁሉንም ጠቅልሎ በመያዝ በተለያዩ የአስተዳደር ክርክሮች ላይ ዳኝነት ይሰጣል። ይህን መሰሉ የአስተዳደር ጉባዔ በመዋቅርና በአደረጃጀት ራሱን የቻለ ህጋዊ ሰውነት ያለው ተቋም ሆኖ የሚቋቋም ሲሆን በስሩም የተለያዩ ጉዳዮችን የሚያዩ ችሎቶች ይኖሩታል፡
አሀዳዊ ቅርጽ ይዞ የሚቋቋም ሁሉን አቀፍ የአስተዳደር ጉባዔ ከውጤታማነት አንጻር ሲታይ በብዙ መልኩ ተመራጭነት አለው። በመጀመሪያ በወጪ እና በሰው ኃይል ረገድ ውጤታማ አጠቃቀም ያዳብራል። ለምሳሌ ያህል ለጉባዔው ስራ የሚያስፈልጉ ሬጅስትራሮች እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ቁጥር ይቀንሳል። ምናልባትም ሁሉንም ስራዎች በአንድ ሬጅስትራር ማከናወን ይቻላል። ለሌሎች ግብዓቶች (ቤተ-መጻህፍት፣ መኪና፣ ኮምፒውተር ወዘተ…) የሚወጣው ወጪም በእጅጉ ይቀንሳል። በተጨማሪም ሁሉም የአስተዳደር ዳኞች በአንድ ተቋም ውስጥ ስለሚታቀፉ በተለያዩ ችሎቶች እያዘዋወወሩ ለማሰራት አመቺ ያደርገዋል። ዳኞች በየችሎቱ እየተዘዋወሩ ሲሰሩ በተለያዩ የአስተዳደር ክርክሮች በሚነሱ የህግ እና ፖሊሲ ጉዳዮች ላይ የሰፋ አመለካከት እንዲኖራቸው ዕድል ይሰጣቸዋል።
ነጠላ እና ድርብ
የአስተዳደር ጉባዔ ውሳኔ በሌላ ይግባኝ ሰሚ የአስተዳደር ጉባዔ በድጋሚ በይግባኝ ሊታይ ይችላል። በዚህ መልኩ በመጀመሪያ ደረጃ እና በይግባኝ የተዋቀረ የአስተዳደር ጉባዔ ድርብ (ባለ ሁለት እርከን) በሚል ይመደባል። በአንጻሩ የስር የአስተዳደር ጉባዔ ውሳኔን በይግባኝ ሰምቶ ዳኝነት የሚሰጥ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ከሌለ ነጠላ (አንድ እርከን) ተብሎ ይጠራል። በአገራችን የሚገኙት የአስተዳደር ጉባዔዎች በሙሉ የተዋቀሩት በአንድ እርከን ነው። ምንም እንኳ የተወሰኑት ‘ይግባኝ ሰሚ’ የሚል ቅጥያ ቢይዙም አንዳቸውም በስራቸው ከሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ካለው ጉባዔ ይግባኝ አይሰሙም። ‘ይግባኝ’ የሚለው አገላለፅ ጉባዔው በአንድ የአስተዳደር መስሪያ ቤት የተሰጠ ውሳኔ እንደገና የማየትና የማጣራት የዳኝነት ስልጣን እንዳለው ለማመልከት ነው። የጉባዔው ውሳኔ በይግባኝ የሚታየው በመደበኛ ፍርድ ቤት እንጂ በሌላ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ አይደለም።
የግል እና የአስተዳደር ክርክር ሰሚ
በግል ክርክር ሰሚ እና የአስተዳደር ክርክር ሰሚ ጉባዔዎች መካከል ያለው ልዩነት ከሚያዩት ጉዳይ ጋር ይያያዛል። በሁለተኛው ረድፍ ውስጥ የሚወድቁት በመንግስትና በግለሰብ መካከል የሚነሱ የአስተዳደር ክርክሮችን ይዳኛሉ። ጉዳዩ በግለሰቦች መካከል የሚነሳ ክርክር በሚሆንበት ጊዜ የግል ክርክር ሰሚ የአስተዳደር ጉባዔ /ወይም ባጭሩ የግል የአስተዳደር ጉባዔ/ በሚል ይመደባል። በአገራችን የግል ተብለው ሊጠሩ ከሚችሉ የአስተዳደር ጉባዔዎች መካከል የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ፤ የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ይግባኝ ሰሚ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት እና በመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማኅበራት አዋጅቁጥር 841/2006 የተቋቋመው የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማኅበር የክርክር አወሳሰን ኮሚቴ ተጠቃሽ ናቸው። የአስተዳደር ተብለው ከሚመደቡት መካከል ደግሞ የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን፣ የመንግስት ሠራተኞች የአስተዳደር ፍ/ቤት እና የማህበራዊ ዋስትና ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ደረጃ እና ይግባኝ ሰሚ
የአስተዳደር ጉባዔ የግራ ቀኙን ክርክር እና ማስረጃ ሰምቶ በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣኑ በቀረበለት ጉዳይ ላይ ቀዳሚ ውሳኔ ሰጪ አካል ሆኖ ሊቋቋም ይችላል። ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ በአንድ አስተዳደር መስሪያ ቤት የተሰጠን ውሳኔ እንደገና የሚመረምርና የሚያጣራ ቅሬታ ወይም ይግባኝ ሰሚ አካል ሆኖ ሊቋቋም ይችላል። የፌደራል ዓቃብያነ ሕግ አስተዳደር ጉባኤ በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣኑ በዓቃቤ ህግ ላይ የሚቀርብን ክስ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል። የውሳኔ ሰጭነት ስልጣን ባይኖረውም የጠበቆች ዲሲፕሊን ጉባዔ የመጀመሪያ ደረጃ ሲሆን የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን፣ ማህበራዊ ዋስትና ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ እና የመንግስት ሠራተኞች የአስተዳደር ፍርድ ቤት ሁሉም አግባብነት ያለው መስሪያ ቤት በሰጠው ውሳኔ ላይ የሚቀርቡ ይግባኞችን የሚያዩ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔዎች ናቸው። የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ እንዲሁ የአሠሪውን ውሳኔ ህጋዊነትና አግባብነት የሚያጣራ ጉባዔ ነው።
መዋቅርና አደረጃጀት፡ ንጽጽራዊ እይታ
የአስተዳደር ጉባዔ አደረጃጀት በተለያዩ አገራት የተለያየ ቅርፅ ይይዛል። ጠቅለል ባለ አነጋገር የፈረንሳይን የአስተዳደር ህግ በሚከተሉት እና በተቃራኒው የእንግሊዝ የህግ ስርዓት በሚከተሉት አገራት መካከል የሰፋ ልዩነት ይታይል።
ለንፅፅር እንዲረዳን የፈረንሳይ፣ የእንግሊዝና አውስትራሊያ የአስተዳደር ጉባዔዎች ያላቸውን አደረጃጀትና መዋቅር በቅደም ተከተል እናያለን። በየአገራቱ ያለው አደረጃጀት የተቃኘው እንደሚከተሉት የህግ ስርዓት በተለይም የአስተዳደር ህግ ስርዓት እንዲሁም ነባራዊና ታሪካዊ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት ቢሆንም ንጽጽሩ በአገራችን ውጤታማ የአስተዳደር ጉባዔ ስርዓት በመዘርጋት ረገድ ጠቃሚ ግብዓት ሊሆን ይችላል።
በፈረንሳይ
በፈረንሳይ የአስተዳደር ፍርድ ቤትs ሲወሳ መነሻችን የፈረንሳይ የአስተዳደር ህግ (droit administratif) ነው። ፈረንሳይ የምትከተለው የአስተዳደር ህግ የታሪካዊ ክስተት ውጤት ሲሆን የራሱ መገለጫ ባህሪያት አሉት። በዋነኛነት ግን ሁለት ራሳቸውን የቻሉ የፍ/ቤት ስርዓት ያላት መሆኑ ለአስተዳደር ህጉ መሰረታዊ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
በአንድ በኩል በግለሰቦች መካከል የሚነሱ የፍትሐብሔር ክርክሮችን የሚያይ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሰበር ሰሚ ድረስ የተዘረጋ መደበኛ የፍርድ ቤት ስርዓት ሲኖር በሌላ በኩል በግለሰብና በአስተዳደሩ የሚነሱ አስተዳደራዊ ክርክሮችን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ ውሳኔ የሚሰጥ ራሱን የቻለ የአስተዳደር ፍርድ ቤት ስርዓት ተዘርግቷል። በዚህ መዋቅር ውስጥ Conseil d’Etat (የመንግስት ምክር ቤት በእንግሊዝኛው Council of State) የበላይ የአስተዳደር ፍ/ቤት ሲሆን አስተዳደራዊ ክርክሮችን በተመለከተ የመጨረሻ የዳኝነት ስልጣን አለው። ይህም ማለት በግለሰብና በመንግስት የሚነሱ የአስተዳደር ክርክሮች በመደበኛ ፍርድ ቤት በይግባኝ ሆነ በሌላ መንገድ የሚስተናገዱበት አጋጣሚ የለም።
የዚህ የድርብ ወይም የሁለትዮሽ የፍርድ ቤት ስርዓት ጠንሳሽና ቀያሽ የ17ኛው ክፍለ ዘመን የፈረንሳይ ንጉስ የነበረው ናፓሊዮን ቦናፓርቴ ነው። ናፓሊዮን በስልጣን በነበረበት ወቅት በፓርላማው ሆነ በመደበኛ ፍ/ቤቶች ላይ እምነት አልነበረውም። ስለሆነም በወቅቱ በፖለቲከኞችና ምሁራን ዘንድ በስፋት የሚቀነቀነውን የስልጣን ክፍፍል መርህ ለጥጦ በመተርጎም አስተዳደሩ በስሩ የሚነሱትን ክርክሮች በራሱ በአስተዳደሩ ማለቅ አለባቸው ወደ ሚል ድምዳሜ አድርሶታል። በዚህ መሰረት በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ለአስተዳደሩ በአማካሪነት ሚና ብቻ ተወስኖ የነበረውን conseil detat የዳኝነት ስልጣን በመስጠት እንደ የበላይ የአስተዳደር ችሎት ማቋቋም ችሏል። ይህ የሆነው እ.ኤ.አ. በ1799 ዓ.ም. ሲሆን conseil detat ከሁለት ክፍለ ዘመናት በላይ ባስቆጠረው እድሜው ውጤታማነቱን በማስመስከር የፈረንሳይ ኩራት ከመሆን አልፎ በብዙ አገራት የሚደነቅና በአምሳያነት በህግ ስርዓታቸው የሚታቀፍ ተቋም ሆኗል።t
በአሁን ወቅት በፈረንሳይ ያለው የአስተዳደር ፍ/ቤት ስርዓት በሶስት ደረጃዎች የተከፋፈለ ነው። በደረጃው መነሻ ላይ የሚገኙት የመጀመሪያ ደረጃ የአስተዳደር ፍርድ ቤቶች (tribunaux administratifs) ሲሆኑ በግለሰብና በአስተዳደሩ መካከል የሚነሱ አስተዳደራዊ ክርክሮችን አይቶ የመወሰን የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣን አላቸው።u በመቀጠልም የመጀመሪያ ደረጃ ውሳኔዎችን በይግባኝ የሚያይ የአስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት (Administratifs d’appeal) ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በመጨረሻ ደረጃ ላይ ከይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በይግባኝ ስልጣኑ ከተሰጠ ውሳኔ ላይ የመጨረሻ የይግባኝ ስልጣን እንዲሁም የሰበር እና የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ያለው Consei detat በመባል የሚጠራው ተቋም በአስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ የመጨረሻና የበላይ የዳኝነት አካል ነው።v
በእንግሊዝ
እ.ኤ.አ ከ1974 ዓ.ም ወዲህ በእንግሊዝ አስተዳደራዊ ክርክሮችን የሚዳኙ የአስተዳደር ጉባዔዎች ቁጥር እያሻቀበ መጥቷል። የመንግስት ሚና ወደ ማህበራዊ አገልግሎት አቅራቢነት እየተለወጠ መምጣቱና በዚህም የመንግስትና የግለሰብ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች እየሰፋ መሄዱ ከግንኙነቱ የሚመነጩ ክርክሮችን በአማራጭ ለመፍታት የተለያዩ የአስተዳደር ጉባዔዎችን (Administrative tribunals) ማቋቋም አስፈልጓል። ይኸው ምክንያት ለቁጥራቸው ማደግ እንደ ዋነኛ ምክንያት ይጠቀሳል። እንደዛም ሆኖ በእንግሊዝ የአስተዳደር ጉባዔዎች ሊከተሉት ስለሚገባ ስርዓት በተመለከተ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ትኩረት ያገኘ ጉዳይ አልነበረም።
በእርግጥ አደረጃጀታቸውን በተመለከተ ያለው ችግር ገንኖ የወጣው ሎርድ ሄዋርድ በ1929 ዓ.ም. ‘አዲሱ አምባገነንነት’ (The New Despotism) በሚለው መጽሐፋቸው መነሻ ነበር። ይህ መጽሐፉ በወቅቱ በጣም እያደገ የመጣውን የአስተዳደር መ/ቤቶች ሰፊ ስልጣን የሚተነትንና ይህም ገደብ ካልተደረገበት ቅልጥ ያለ አምባገነንት እንደሚያስከትል ተጨባጭ ስጋት አንጸባርቋል። በምላሹም የእንግሊዝ ፓርላማ የሚኒስትሮችን ስልጣን የሚመረምር ኮሚቴ በማቋቋም እ.ኤ.አ. በ1932 ዓ.ም. የሚኒስትሮች ስልጣን ኮሚቴ ሪፖርት (Report of the Committee of Ministers Powers) ለህዝብ ይፋ ሆነ።w የሪፖርቱ ይዘት በጠቅላላው እያደገ የመጣውን የስራ አስፈፃሚ ስልጣን የሚመለከት እንጂ ስለ የአስተዳደር ጉባዔዎች ዝርዘር ጥናት አላካተተም።
እ.ኤ.አ. በ1957 ዓ.ም. የተቋቋሙው የፍራንክ ኮሚቴ (Franks Coomittee) የአስተዳደር ጉባዔዎችን የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት፣ አደረጃጀትና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ ዝርዝር ምርመራና ጥናት አድርጐ ሪፖርቱ በዚሁ ዓመት ይፋ ሆኖ ታተመ። የኮሚቴውን ሪፖርት እንደ መነሻ በመውሰድ ከአንድ ዓመት በኋላ እ.ኢ.አ. በ1958 የወጣው የአስተዳደር ጉባዔዎችና መርማሪ አካላት አዋጅ (Tribunals and Inquiries Act 1958) ተብሎ የሚጠራውን ህግ ለአስተዳደር ፍ/ቤቶች ዘላቂ አደረጃጀት መሰረት ሆኗል። በመቀጠልም እ.ኢ.አ. በ1992 አዋጁ የተወሰኑ ማሻሻያ ታክለውበት እንደገና ህግ ሆኖ ወጥቷል።
በዚሁ መሰረት የተሻሻለው አዋጅ በተለያዩ አስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣን ያላቸውን ጉባዔዎች በመዘርዘር አቋቁሟል። ሌሎች በቁጥር አነስተኛ የሆኑ ተመሳሳይ የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው የአስተዳደር ጉባዔዎች ደግሞ በሌላ በልዩ ህግ ተቋቁመዋል። የእነዚህ ጉባዔዎች ባህርያት በጥቅሉ ሲታይ ሁሉም ራሳቸውን ችለው የተቋቋሙ እንጂ የጐንዮሽ እና ቀጥተኛ ግንኙነት የላቸውም። ይህም ማለት ሁሉንም በበላይነት የሚያስተዳድርና የሚመራ ፕሬዝዳንት ሆነ ሊቀመንበር የለም። በውሳኔ አሰጣጥ ረገድ የሚከተሉት ስነ-ስርዓት ወጥነት የለውም። ሁሉም ለጉዳዩ አመቺ የሆነ ዝርዝርና ልዩ ስነ-ስርዓት ተፈፃሚ ያደርጋሉ። የሚከተሉት ስነ-ስርዓት የተለያየ ቢሆንም ባይሆንም ሁሉም በውሳኔ አሰጣጥ ረገድ የተፈጥሮ ፍትህ መሰረት ሀሳቦችን ማለትም የመሰማት መብት እና የኢ አድሎአዊነት መርህ ወጥ በሆነ መልኩ የመከተል ግዴታ አለባቸው።
የእንግሊዝ የአስተዳደር ጉባዔዎች በአንድ ጥላ ስር አለመደራጀታቸው ዝብርቅርቅ ስነ-ስርዓት በመፍጠር ከወጪ አንፃር አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድርና ይህም በውጤታማነታቸው ላይ ክፍተት እንደሚፈጥር እሙን ነው። ይህን ችግር በከፊልም ቢሆን ለማስወገድ እ.ኤ.አ. በ1992 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣው አዋጅ አሰራርና አደረጃጀታቸውን የሚከታተል የአስተዳደር ጉባዔዎች ካውንስል የተባለ ራሱን የቻለ አካል በማቋቋም በተግባርም የተሻለ ውጤት እንዲመጣ አድርጓል።
ይህ ተቋም ምንም አይነት የዳኝነት ስልጣን የለውም። ሆኖም የጉባዔዎችን አሰራር ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዙ እርምጃዎች የመውሰድ ወይም እንዲወሰዱ የማድረግ ስልጣናት ነበሩት። ለምሳሌ ያህል የሚመሩበት ስነ-ስርዓት በየትኛውም አካል ከመውጣቱ በፊት በቅድሚያ ካውንስሉን ማማከር ያስፈልጋል። የዳኞችን ሹመት በተመለከተም ለሚመለከተው አካል ሀሳብ መስጠት ይችላል። በተጨማሪም አጠቃላይ አሰራራቸውን በተመለከተ በየአመቱ ሪፖርት ያቀርባል። በተጨማሪም ስልጠና እና ትምህርት በማዘጋጀት አቅማቸውን በማጐበት ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።
እ.ኤ.አ እስከ 2007 ዓ.ም. ድረስ በእንግሊዝ የመጀመሪያ ደረጃ የአስተዳደር ጉባዔዎች አደረጃጀት ወጥነት እንዳልነበረው ሁሉ የይግባኝ ስርዓቱም ወጥ ስርዓት ሲከተል አልነበረም። አንዳንድ ጉባዔዎች በመጀመሪያና በይግባኝ ቢደራጁም የተቀሩት ግን የይግባኝ ስርዓት አልተዘረጋላቸውም።
እ.ኤ.አ. በ2007 ዓ.ም. የአስተዳደር ጉባዔዎችን በአዲስ መልክ ያቋቋመው Tribunals, Courts and Enforcement Act 2007 (TCE Act) ተሰበጣጥረው የነበሩትን ሁሉንም ጉባዔዎች አንድ ላይ አዋህዷቸዋል። በዚሁ መሰረት ገለልተኛና ነጻ ጉባዔዎች በመጀመሪያ ደረጃ እና በይግባኝ ሰሚ ተዋቅረዋል። የመጀመሪያ ደረጃ ጉባዔዎች በአስተዳደር አካላት የተሰጡ ማናቸውንም ውሳኔዎችና እርምጃዎች በመቃወም የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በህግና በፍሬ ነገር ላይ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ሲሆን በይግባኝ ሰሚነት የተዋቀሩት ደግሞ በህግ ጉዳይ ላይ አከራክሮ የመወሰን ስልጣን አካቸው። በተጨማሪም ውስን በሆኑ ጉዳዮች በቀጥታ የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።x
በአውስትራሊያ
የአውስትራሊያ የአስተዳደር ጉባዔዎች ስርዓት ከሞላ ጐደል በእንግሊዝ ስርዓት መሰረት የተቀረጸ ቢሆንም የራሱ የሆኑ ልዩ ባህርያት አሉት። በአውስትራሊያ የአስተዳደር ጉባዔ ጽንሰ ሀሳብ ከመነሻው ከእንግሊዝ በውሰት የተወሰደ ቢመስልም የራሱን ልዩ መገለጫዎች በመያዝ በየጊዜው በለውጥ ሂደት ውስጥ እያለፈ በተለያየ ቅርጽና አወቃቀር ውስጥ እየተፈተነ አሁን ያለበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
እንደ እንግሊዝ ሁሉ የአውስትራሊያ የአስተዳደር ጉባዔዎች ስርዓት ሊይዝ ስለሚገባው ቅርጽና ገጽታ በተመለከተ በተለያዩ አጥኒ ቡድኖች ስፊ ጥናትና ዳሰሳ ከተሄደበት በኋላ አብዛኛዎቹ ከጥናቱ የተገኙ የመፍትሔ ሀሳቦች በህግ ማእቀፍ ውስጥ ተካትተዋል። የእነዚህ ጥናቶች ዋና አላማ በመንግስት አስተዳደር በደል የደረሰባቸው ዜጐች የአስተዳደር ፍትህ ማጐናጸፍ ነው። ጥናቶቹ ወጥነት በሌለው መልኩ ተሰበጣጥረው የነበሩትን ጉባዔዎች ሁሉን አቀፍ አሀዳዊ ስርዓት እንዲከተሉ የጐላ አስተዋጽኦ አድርጓል።
ወጥነት ያለው ሁሉን አቀፍ የአስተዳደር ጉባዔ አስፈላጊነቱ በየጊዜው እየታመነበት በዚህ አቅጣጫ ሰፊ እንቅስቃሴ የተደረገ ቢኖርም የመጀመሪያ ደረጃ ጉባዔዎችን በአንድ ጥላ ስር የሚያዋቅር ስርዓት አሁንም ድረስ በአውስትራሊያ በፌደራል መንግስቱ ደረጃ አልተዋቀረም። በእርግጥ እ.ኤ.አ. በ2000 ዓ.ም. ረቂቁ ለፓርላማ የቀረበ ቢሆንም ህግ ሆኖ ገና አልፀደቀም።
ከዚህ በተቃራኒ ከእነዚህ የተለያዩ የአስተዳደር ጉባዔዎች የተሰጡ ውሳኔዎች በይግባኝ የሚዳኙት ወጥ በሆነ አንድ የይግባኝ ሰሚ አስተዳደር ጉባዔ ስር ነው። በዳኝነት ስልጣኑ የመጀመሪያ ደረጃ የአስተዳደር ጉባዔዎች በሚያስተላልፏቸው ውሳኔዎች ላይ በፍሬ ነገር እና በህግ ጉዳይ ላይ ይግባኝ ይሰማል።
በአገራችን የአስተዳደር ጉባዔዎች መዋቅርና አደረጃጀት
በአትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የአስተዳደር ጉባዔዎች አደረጃጀት ወጥነት አይታይበትም። ማቋቋሚያ አዋጁ ለአንዳንዶቹ በግልጽ የህግ ሰውነት ሲሰጥ ሌሎቹን ግን ከማቋቋም ባለፈ ከአስተዳደር መ/ቤቱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እና የህግ ሰውነት በግልጽ አይለይም። ሁሉም ጉባዔዎች ራሳቸው ችለው በተናጠል የተቋቋሙ ሲሆን እርስ በርስ የጐንዮሽ ግንኙነት የላቸውም። በተጨማሪም በአሰራር፣ በስነ-ስርዓት፣ የዳኞች ምልመላ፣ ሹመትና ሽረት ከበላይ ሆኖ የሚያስተዳድርና የሚመራና አንድ ወጥ አካል የለም።
የይግባኝ ስርዓቱም እንዲሁ ወጥነት ርቆታል። ሁሉም የአስተዳደር ጉባዔዎች የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ብቻ ያላቸው ሲሆን በአንድ ጉባዔ የተወሰነን ጉዳይ ይግባኝ የሚሰማ ይግባኝ ሰሚ ጉባባዔ የለም። ለምሳሌ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የተወሰነ ጉዳይ ይግባኙ የሚሰማው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤትy ሲሆን በመንግስት ሰራተኞች አስተዳደር ፍ/ቤትz እና በማህበራዊ ዋስትና ይግባኝ ሰሚ ጉባዔa የተወሰነ ጉዳይ ይግባኙ የሚቀርበው ለፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ነው። በታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የሚሰጡ ውሳኔዎች ደግሞ በፌደራል ከፍተኛ እና ጠቅላይ ፍ/ቤት በይግባኝ ይታያሉ።b
የአስተዳደር ጉባዔዎች ሁሉን አቀፍ መልክ ይዘው በአንድ ጥላ ስር አለመደራጀታቸው ለአላስፈላጊ ወጪ የሚዳረግ ከመሆኑም በላይ በተሰበጣጠረ ቦታ መገኘታቸውና ወጥ ስነ-ስርዓት አለመከተላቸው ተደራሽነታቸውን ሩቅ አድርጐታል። አብዛኛዎቹ በአስተዳደር መ/ቤቱ ህንፃ ውስጥ የሚገኙ ሲሆን ከጸሐፊ ጀምሮ ለስራ አስፈላጊ ቁሳቁሶች በመ/ቤቱ በጀት ይመደብላቸዋል። ይህም ገለልተኛነታቸውን ጥያቄ ውስጥ ከቶታል። በተግባር እንደሚታየው ስለ አስተዳደር ጉባዔዎች ያለው እይታ በመ/ቤቱ ውስጥ እንደተቋቋሙ ቅሬታ ሰሚ አካላት እንጂ ራሳቸውን እንደቻሉ ፍትህ ሰጪ ተቋማት አይደለም። ይህም በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ያላቸውን ቦታ እና ተቀባይነታቸውን አውርዶታል ማለት ይቻላል።
የ1967ቱ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ወጥ የአደረጃጀት ስርዓት ለመዘርጋት በመሞከር የመጀመሪያው ነው። ረቂቁ በአንቀጽ 23 ላይ የጠቅላይ ፍ/ቤት (Imperial supreme court) አካል (Division) የሆነ ጠቅላይ የአስተዳደር ፍ/ቤት ያቋቁማል። ይህ ፍ/ቤት በአስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ይግባኝ የመስማት ብቸኛ የዳኝነት ስልጣን (exclusive jurisdiction) አለው። ይህ ስርዓት የፈረንሳይ የአስተዳደር ፍ/ቤትን አደረጃጀት የሚከተል ይመስላል። ይሁን እንጂ ይህን ድምዳሜ ሙሉ በሙሉ መቀበል ያስቸግራል።
ጠቅላይ የአስተዳደር ፍ/ቤቱ የጠቅላይ ፍ/ቤት አንድ ክፍል ተደርጐ መቆጠሩ ራሱን የቻለ የህግ ሰውነት ያለው የአስተዳደር ፍ/ቤት አለመኖሩንና የሁለትዮሽ ስርዓት ተፈፃሚ አለመሆኑ ያሳየናል። በአቋሙ ሲታይ እንደፈረንሳይ ኮንሲል ዴታ (Conseil d’Etat) በአስተዳደራዊ ጉዳዮች የመጨረሻ ስልጣን ያለው ፍ/ቤት ይመስላል። ይሁን እንጂ ከዚህ ጠቅላይ የአስተዳደር ፍ/ቤት ስር አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣንና በይግባኝ የሚያዩ የአስተዳደር ጉባዔዎች አልተቋቋሙም። ስለዚህ ምንም እንኳን ‘ይግባኝ’ የሚለው ቃል በአንቀጽ 25 ላይ ቢጠቀስም ጠቅላይ የአስተዳደር ፍ/ቤቱ አስተዳደራዊ ክርከሮችን በቀጥታ የሚያይ የመጀመሪያ ደረጃ የአስተዳደር ፍ/ቤት ነው። ከአስተዳደራዊ ፍትህ አንፃር ሲታይ በዚህ ፍ/ቤት የሚታይ ጉዳይ ለበላይ አስተዳደር ፍ/ቤት ሆነ ለመደበኛ ፍ/ቤት በይግባኝ ስለማይቀርብ የዜጐችን አስተዳደራዊ ፍትህ የማግኘት መብት በእጅጉ ያጣብባል።
በ2001 ዓ.ም. የተዘጋጀው ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ በ1967ቱ ላይ የሚንጸባረቀውን የተምታታ አደረጃጀት በማስወገድ ከሞላ ጐደል የእንግሊዝ የአስተዳደር ጉባዔ ስርዓት የመሰለ አደረጃጀት ተፈፃሚ ያደርጋል። በረቂቁ አንቀጽ 17 ላይ እንደተመለከተው ከመደበኛ ፍ/ቤት ውጪ የሆነ ራሱን የቻለ የፌደራል የአስተዳደር ቅሬታዎች ይግባኝ ፍ/ቤት የተባለ አካል ይቋቋማል። ፍ/ቤቱ የእለት ተእለት እንቅስቃሴውን የሚመራ የራሱ ፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚደንት የሚኖሩት ሲሆን የሚሾሙትም በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በተወካዮች ም/ቤት ይሆናል። ረቂቅ አዋጁ ሁሉንም የአስተዳደር ችሎቶች በአንድ ጥላ ስር በማደራጅት ሁሉን አቀፍ የአስተዳደር ጉባዔ ስርዓት (generalized tribunal) መከተሉ ከስነ-ስርዓት ወጥነት፣ ተደራሽነትና ወጪ ቆጣቢነት አንጻር ተመራጭነት አለው።
ረቂቁ በተጨማሪ ከእንግሊዙ የአስተዳደር ጉባዔ ም/ቤት (Council on Tribunals) ጋር ተመሳሳይነት ያለው ምክር ቤት ያቋቁማል። ሆኖም በይዘትና በስልጣን ረገድ የተከተለው አካሄድ የተለየ ያደርገዋል። የዚህ ም/ቤት ስልጣን ለአስተዳደር ፍ/ቤት ዳኞች ስልጠና በማዘጋጀት፣ በማመቻቸት እንዲሁም በቀጥታ በመስጠትና ሪፖርት በማቅረብ ላይ የተገደበ ሳይሆን በፕሬዝዳንቱ የሚቀርቡትን እጩ ዳኞች መርጦ የመሾም፣ የዲሲፕሊን እርምጃ የመውሰድ፣ ስነ-ስርዓትን ጨምሮ ፍ/ቤቱ ተግባሩን በአግባቡ እንዲወጣ የሚረዳ መመሪያ የማውጣት እንዲሁም አስተዳደራዊ ፍትህን ለማስፈን የሚረዱ አጠቃላይ የፖሊሲ አቅጣጫዎች ላይ የመወሰን ስፊ ተግባራዊ ስልጣን ተሰጥቶታል። ምክር ቤቱ ስፊ ስልጣን ማግኘቱ የአስተዳደር ፍ/ቤቱ በየጊዜው የሚያጥሙትን ችግሮች በቅርበት እየተከታተለ ለመፍታት ያስችለዋል።
ከይዘቱ አንፃር ግን የተለያዩ አስተዳደር ፍ/ቤቶች ሆነ የሌሎች ሶስተኛ ወገኖች ውክልና አለማግኘቱ የችሎቶቹን ሚዛናዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት ከመሆኑም በላይ የአስተዳደር ፍ/ቤቱን ኢ-መደበኛ ባህርይ ያጠፋዋል።
በረቂቁ አንቀጽ 19 መሰረት ም/ቤቱ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል።
የተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ……………ሊቀመንበር
የፌደሬሽን ም/ቤት አፈ- ጉባኤ…………………አባል
የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት…………አባል
ዋና እንባ ጠባቂ………………………………አባል
የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ዋና ኮሚሽነር………አባል
የፍትህ ሚኒስትር (በአሁኑ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ)………አባል
የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት………………………አባል
የፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት………………. አባል
በዚህ መልኩ የሚዋቀረው ም/ቤት በአስተዳደር ፍ/ቤቱ ዳኞች ሹመት ላይ የመወሰን ስልጣን አለው። በተጨማሪም ችሎቶቹን ያደራጃል። ይመድባል።
ከፌደራል የአስተዳደር ቅሬታዎች ይግባኝ ፍ/ቤት በሚሰጥ ውሳኔ ላይ ስለሚኖረው የይግባኝ ስርዓት እንደበፊቱ ረቂቅ ሁሉ በፌደራሉ ረቂቅ ላይም በዝምታ ታልፏል። ምንም እንኳን ይህ ፍርድ ቤት ‘የይግባኝ ፍ/ቤት’ የሚል ስያሜ ቢሰጠውም በተግባር ግን በአሰተዳደር መ/ቤቱ በሚሰጡ የመጨረሻ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ በፍሬ ነገርና በህግ ጉዳይ ላይ አከራክሮ ውሳኔውን የመለወጥ፣ የማጽደቅ ወይም ቅጣቱን የመቀነስ የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ያለው የአስተዳደር ፍ/ቤት ነው።
በረቂቁ መሰረት ስራ ላይ ያሉት ጥቂት የአስተዳደር ጉባዔዎች እጣ ፋንታ አልለየለትም። እነዚህ ጉባዔዎች ታጥፈው በረቂቁ መሰረት በሚቋቋሙት ችሎቶች የሚተኩ ከሆነ ረቂቁ ይህንን የሚያጣጥም ድንጋጌ ሊኖረው ይገባል።
የዳኞች ሹመት እና ሽረት
በአስተዳደር ጉባዔ የሚያስችሉ ዳኞች የሹመት ስርዓትና የብቃት መመዘኛ እንደ ክርክሩ አይነት ይለያያል። ልዩ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በብዙ አገራት ተቀባይነት ያገኘው ስርዓት ‘ሚዛናዊ የአስተዳደር ጉባዔ’ (balanced tribunal) ተብሎ የሚጠራው ሲሆን በገለልተኛ አካል የሚሾም አንድ ሊቀመንበርና የተለያዩ ጐራዎችን ጥቅም የሚወክሉ ሁለት አባላት ይኖሩታል። የዚህ ስርዓት ዋና ዓላማ በክርክሩ ተካፋይ የሆነ ወገን የእርሱን ጉዳይ በወጉ የሚረዳ ቢያንስ አንድ አባል እንዲኖረው በማድረግ ፍትሐዊነቱን ማረጋገጥ ነው።
በአገራችን የአስተዳደር ጉባዔዎች ከሞላ ጐደል ይህንኑ ስርዓት ይከተላሉ። የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ቦርድ በችሎት የሚሰየም አንድ ሰብሳቢ እና ከአሰሪ ማህበራት የሚወክሉ ሁለት አባላት እንዲሁም ከሰራተኞች ማህበራት የሚወክሉ ሁለት አባላት ይኖሩታል። የቦርዱ ተተኪ አባላትም ከሰራተኛና አሰሪ ማህበራት የሚወከሉ አንድ አንድ አባላት ይሆናሉ።
በሁሉም የአስተዳደር ጉባዔዎች ሰብሳቢው ወይም ሊቀመንበሩ በስራ አስፈፃሚው ይሾማል። የችሎቱ አባላት ከችሎት የሚነሱትም ሹመቱን ባጸደቀው ሚኒስትር ወይም ባለስልጣን ሲሆን በተለይ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን በተመለከተ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ከሰራተኛ ወይም አሰሪ ማህበራት የተወከሉ አባላትን ሳይቀር የመሻርና በሌላ የመተካት ስልጣን አለው። ሹመትና ሽረት የሚፈጸመው በአንድ ሰው መሆኑ ሳያንስ ሚኒስቴሩ ያልሾመውን አባል ጭምር የመሻር ስልጣን ማግኘቱ የቦርዱንን ነፃነትና ገለልተኝነት በእጅጉ ይጋፋል።
በአስተዳደር ጉባዔ የሚሰየሙ ዳኞች በሚያዩት ጉዳይ ላይ የተካነ እውቀት እንዲኖራቸው እንጂ የግድ የህግ እውቀት አያስፈልጋቸውም። ሆኖም አንዳንድ የተወሳሰቡ የአስተዳደር ክርክሮች የህግ ባለሙያ እገዛ ስለሚጠይቁ ቢያንስ የተወሰኑ አባላት የህግ እውቀት ቢኖራቸው ይመረጣል። በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ከሚሾሙት ዳኞች መካከል ሁለቱ ስለአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ብቃትና ልምድ ሊኖራቸው ይገባል። ሁሉም የቦርዱ አባላትና ተተኪ አባላት የአገልግሎት ዘመናቸው ሶስት ዓመት ሲሆን የስራ ጊዜያቸውም ‘የትርፍ ጊዜ’ (part-time) ሆኖ በቦርድ ስብሰባ ለተገኘ አባል በሚኒስትሩ ከሚወሰን አበል በስተቀር ቋሚ ደመወዝ አይከፈላቸውም።
በፌደራሉ ረቂቅ አዋጅ (2001 ዓ.ም.) መሰረት በችሎቱ የሚሰየሙ አባላት ሹመትና ሽረት በረቂቁ በሚቋቋመው ም/ቤት አማካይነት የሚከናወን ሲሆን ይህም የፍ/ቤቱን ገልተኛነት በሚገባ ያረጋግጣል። የችሎቱ አባላት የስራ ዘመን ለአምስት ዓመት ሆኖ በድጋሚ ከመሾም ገደብ አይደረግባቸውም። የስራ ጊዜያቸው ሙሉ ወይም ከፊል የስራ ሰዓት ስለመሆኑ ባይመለከትም ፍ/ቤቱ ራሱን ችሎ እንደ ተቋም የተደራጀ ከመሆኑ አንጻር የሙሉ ሰዓት ዳኞች እንደሆኑ መገመት ይቻላል። ለዳኞች የሚከፈለው ክፍያ መጠን በምክር ቤቱ በሚወሰነው መሰረት ይሆናል።
የዳኞች ብቃት መለኪያ እንደሚቋቋሙት ችሎቶቸ የሚቀያየር ሳይሆን ወጥነት ባለው መልኩ የተቀመጠ ነው። እያንዳንዱ ችሎት ሶስት አባላት ሲኖሩት ሰብሳቢው በህግ ትምህርት ስልጠና ያለው ወይም በህግ መስክ በቂ ልምድ ያለው ሰው መሆን ይኖርበታል። በዚህ መመዘኛ መሰረት ከስልጠና ወይም ልምድ በስተቀር በመደበኛ የህግ ትምህርት ዲፕሎማ ወይም ዲግሪ መያዝን አይጠይቅም። የተቀሩት ሁለት አባላት ‘መልካም ስምና ክብር ከበቂ የአስተዳደር ተግባራት እውቀትና ልምድ’ ጋር ሊኖራቸው እንደሚገባ በረቂቁ አንቀጽ 46/2/ ተመልክቷል። ይህ መለኪያ ግልጽነት የሚጎድለው እንደመሆኑ ‘የአስተዳደር ተግባራት’ የሚለው ‘በህዝብ አስተዳደር’ በሚል ቢተካ የተሻለ ነው። ይህም ቢሆን ጥቅል ሀሳብ ያዘለ እንደመሆኑ መጠን የአስተዳደር ዳኞች እንደ ክርክሩ አይነት ልምድና እውቀታቸው እየተመዘነ በዳኝነት ቢሾሙ ሊቋቋም የታሰበው የአስተዳደር ፍ/ቤት እንደሌሎች አገራት ሁሉ ውጤታማነቱን በማስመስከር በአስተዳደር በደል ለተጠቃው ዜጋ የአስተዳደር ፍትህ ለማስፈን ብቃት ይኖረዋል።

Accusations Against God And A Demon


Accusations against God and A Demon.

Man is a plaintiff.

It would not be an exaggeration to say that the main difference between humans and animals is their guilt.

(Probably.) Not only the size of the case and the plaintiff but also the nature and content of the case can be taken as evidence of a strong connection between people and the dispute.

There are so many ridiculous accusations in the world today, but the accusations against God and A Demon can be categorized.

It may seem ridiculous, but the accusers are not.

For example, Antu, a U.S. senator in the United States, filed a lawsuit against God.

His name is Ernie Chambers. He filed a lawsuit against the Douglas County Court of Appeals in the United States, alleging that he had been sentenced to life in prison.

Among them is the widespread suffering of mankind in our world; Hunger: Natural Disasters: War: It means that he has not been able to stop the abuse.

The judge, after examining the case carefully, dismissed the case on the grounds that it was impossible to find God at his address. Satan was charged in 1971. The plaintiff is called Gerald Mayo.

Plaintiff also pleaded guilty to one count of felony criminal mischief and one count of felony criminal mischief with intent to defraud. The trial judge dismissed the case in the first instance, but he did not want to close the case. Each point is examined from left to right, and the record is thoroughly examined.

To summarize, the court rejected Satan’s accusation, citing the following main reasons. Cause of accusation Even if the plaintiff’s rights are upheld, there is no solution that the court can give. What can a court do for Satan?

Defendant’s address How would he respond to Satan’s call, even if he were to be prosecuted? Group accusation It is difficult to stand firm in this way without being convinced that Satan can protect the interests of his troops. There is no evidence that he has a certified representative.

Fairness If the defendants come to court, the first thing they see is a large sign that reads “In God We Trust”.

In this case, the defendants are not expected to receive a fair trial. “We therefore dismiss the charge. The registry is closed. Return to registry. The right to appeal is reserved. ”

የክልል አስተዳደር ህግ


ፌደራላዊ የመንግስት አወቃቀር የመንግስትንና

የግለሰብን ግንኙነት ሁለትዮሽ ገፅታ ያላብሰዋል፡፡ በፌደራል ደረጃ በፌደራሉ መንግስትና በግለሰቡ መካከል የሚፈጠር ግንኙት ሲኖር ይኸው ተመሳሳይ ግንኙነት በክልል ደረጃ በክልሉ መንግስትና በግለሰቡ መካከል ይፈጠራል፡፡ የኢትዮጵያ የአስተዳደር ህግ ይዘት፣ ወሰንና መገለጫ ባህሪያት ከዚህ ሀሳብ ይነሳል፡፡ መንግስትና የህዝብ የአስተዳደር በፌዴራልና በክልል ደረጃ የተዋቀረ እንደመሆኑ የአገራችን የአስተዳደር ህግ የፌደራል እና የክልል አስተዳደር ህግ ድምር ውጤት ነው፡፡
ከድምሩና ከውጤቱ በፊት ግን በፌደራላዊ የመንግስት ስርዓት ውስጥ ሁለት ዓይነት የአስተዳደር ህግ የመኖሩ ጉዳይ ግልጽ መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም ክልሎች የራሳቸውን የአስተዳደር ህግ ማውጣት ይችላሉ? የሚል የስልጣን ክፍፍል ጥያቄ ሊነሳ አይገባም፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በፌደራል እና በክልል የተዋቀረ ሲሆን ሁለቱም በተመሳሳይ መልኩ ህግ አውጪ፤ አስፈፃሚና ህግ ተርጓሚ የሚባሉ የመንግስት አካላት አቅፈዋል፡፡a እነዚህ ሶስት የመንግስት አካላት በህገ-መንግስቱ ለፌደራል እና ለክልሎች በተሰጡት ስልጣናት ስር ህግ የማውጣት፤ የመተግበር እና የመተርጐም ተግባራትን ያከናውናሉ፡፡ በክልል ደረጃ ህግ አስፈፃሚው አካል የክልሉ መስተዳድር ሲሆን የክልሉ ምክር ቤት ያወጣቸውን ህጐች ይተገብራል፡፡b
ስልጣንን በመገልገል የሚፈጸሙ ተግባራት አስተዳደራዊ (ለምሳሌ የምርመራ፤ የክትትል፤ ቁጥጥርና ምክር መስጠት)፣ ህጉን ለመተግበር የሚረዱ መመሪያዎችን የማውጣት እንዲሁም የአስተዳደር ውሳኔዎችንና እርምጃዎችን የመውሰድ (ለምሳሌ የንግድ ድርጅት የመዝጋት፤ የንግድ ፍቃድ የመስጠት፤ የማገድ፤ የመሰረዝ) ተግባራትን ያጠቃልላል፡፡ የክልል አስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ህጋዊነትና ፍትሐዊነት በተመለከተ የክልል ምክር ቤት እና የክልል ፍ/ቤቶች የየራሳቸውን ሚና ይጫወታሉ፡፡ ለምሳሌ የክልሉ ምክር ቤት አነስተኛ የውሳኔ እና የመመሪያ አወጣጥ ስነ-ስርዓቶችን ሊደነግግ ይችላል፡፡ ፍ/ቤቶች ደግሞ የአስተዳደራዊ ውሳኔዎችና መመሪያዎች ህጋዊነት በመመርመር መስተዳደሩ ለህግ ተገዢ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ በዚህ መልኩ የአስተዳደር ህግ በእያንዳንዱ ክልል የግድ ይፈጠራል፡፡ በአሁኑ ወቅት ያለው የፌደራል የአስተዳደር ህግ ገና በቅጡ ያልዳበረና ጥልቀት ያለው ጥናትና ምርምር ተደርጐበት ትክክለኛ ይዘቱ፤ ቅርፁ፤ መገለጫውና ወሰኑ ተለይቶ የሚታወቅ አይደለም፡፡ ከዚህ በባሰ ደግሞ በክልሎች ያለው የአስተዳደር ህግ በአግባቡ ሊጠናና ሊታወቅ ቀርቶ እስከ መኖሩ ሳይቀር ተዘንግቷል ማለት ይቻላል፡፡ በዚህ የተነሳ በፌደራሉ የአስተዳደር ህግ እና በክልል የአስተዳደር ህግ መካከል ያለው ዝምድና እና መወራረስ ራሱን የቻለ ጥናትና ምርምር ይፈልጋል፡፡ በየክልሉ ያሉትን አዋጆች፤ ደንቦች፤ መመሪያዎችና የፍ/ቤት ውሳኔዎች ብሎም የየአስተዳደር መስሪያ ቤቱ ውሳኔዎችና ሌሎች የህጉን ምንጮች ለማግኘት ካለው አዳጋችነት የተነሳ የዚህ መጽሀፍ ዋነኛ ትኩረትም የፌደራል የአስተዳደር ህግ ብቻ ነው፡፡

አንታራም ህጎች ከአገራችን


በአገራችን ከላይ እንዳየናቸው ዓይነት ፈገግታን የሚያጭሩ አንታራም ህጎች እስካሁን አልገጠመኝም፡፡ ሆኖም ከህገ-መንግስታዊነት መለኪያ አንጻር አንታራምነታቸው ጎልተው የወጡ የህግ ድንጋጌዎች አሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ እኔ የሚከተሉትን መርጫለው፡፡ ማብራሪያ አልተጨመረም፡፡
(የትራንፖርት አዋጅ ቁጥር 468/1997 አንቀጽ 27(2)
ክልሎች የራሳቸውን ህግ እስኪያወጡ ድረስ የዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች ትራንስፖርት ነክ በሆኑት ጉዳዮች ላይ በክልሎች ውስጥ ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል፡፡
(የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩል ባለስልጣን ሰራተኞች አስተዳደር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 155/2000 አንቀጽ 37)
በልዩ ሁኔታ ሰራተኞችን ስለማሰናበት
1) በዚህ ደንብ በሌላ ሁኔታ የተደነገገው ቢኖርም ዋና ዳይሬክተሩ በሙስና የተጠረጠረንና እምነት ያጣበትን ሰራተኛ መደበኛውን የዲስፕሊን አፈፃፀም ስርዓት ሳይከተል ከስራ ማሰናበት ይችላል
2) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት ከስራ የተሰናበተ ሰራተኛ በየትኛውም የፍርድ አካል ውሳኔ ወደ ስራ የመመለስ መብት አይኖረውም፡፡
(የፍትሐ ብሔር ህግ እንደተሻሻለ አዋጅ ቁጥር 639/201)
ለባንክ ወይም ለአነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ብድር መያዣነት የተሰጠ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሚመለከት የተደረገ ውል በፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 1723 መሰረት በፍርድ ቤት መዝገብ ወይም ስልጣን በተሰጠው አዋዋይ ፊት አልተደረገም በሚል ተፈጻሚነት እንዳይኖረው ይህ አዋጅ ከመጽናቱ በፊት በማናቸውም ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ አይጸናም፡፡ (ሰረዝ የተጨመረ)
(የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ አዋጅ ቁ. 691/2003)
የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ደንብ በማውጣት፣ ማንኛውም አስፈጻሚ አካል እንዲታጠፍ፣ ከሌላ አስፈጻሚ አካል ጋር እንዲዋሃድ ወይም እንዲከፋፈል በማድረግ፣ ተጠሪነቱ ወይም ሥልጣንና ተግባሩ እንዲለወጥ በማድረግ ወይም አዲስ አስፈጻሚ አካል እንዲቋቋም በማድረግ የፌዴራል መንግሥት አስፈጻሚ አካላትን እንደገና የማደራጀት ሥልጣን በዚህ አዋጅ ተሰጥቶታል፡፡
(የደን ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ማፅደቂያ አዋጅ ቁ. 542/1999 አንቀጽ 20) ንዑስ አንቀጽ 6ን ይመልከቱ

ቅጣት

የተፈጸመው ጥፋት በወንጀል የበለጠ የሚያስቀጣ ካልሆነ በስተቀር፤
፩/ በዚህ አዋጅና አዋጁን ለማስፈጸም በሚወጡ መመሪያዎች ካልሆነ በስተቀር ከመንግሥት ደኖች ዛፎችን የቆረጠ ወይም የደን ውጤቶችን የወሰደ፤ ያዘጋጀ ወይም በማንኛውም መንገድ የተጠቀመ ከ፩ ዓመት በማያንስና ከ፭ ዓመት በማይበልጥ እሥራት እና በብር ፲ሺ ይቀጣል፣
፪/ የደን የወሰን ምልክቶችን ያጠፋ፤ ያበላሸ ወይም ያዛባ ከ፩ ዓመት በማያንስና ከ፭ ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል፣
፫/ እሳት በመለኮስ ወይም በማናቸውም ሌላ ሁኔታ በደን ላይ ጉዳት ያደረሰ ከ፲ ዓመት በማያንስና ከ፲፭ ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል፣
፬/ በደን ክልል ውስጥ ያለፈቃድ የሰፈረ ወይም የእርሻ ቦታ ያስፋፋ ወይንም ማንኛውም የመሠረተ ልማት ግንባታ ያለፈቃድ በደን ቦታ የተጠቀመ ከ፪ ዓመት በማያንስ እስራት እና በብር ፳ሺ ይቀጣል፣
፭/ ለህገወጥ ደን ጨፍጫፊዎች ወይም የደን ውጤት አዘዋዋሪዎች በማንኛውም መልኩ ምርቱን እንዲደብቁ ወይም እንዲያሸሹ እገዛ ያደረገ በ፭ ዓመት እስራት እና በብር ፭ሺ መቀጫ ይቀጣል፣
፮/ ከላይ ከተራ ቁጥር ፩ እስከ ፭ ባሉት ውስጥ ያልተጠቀሱና ቅጣት ያልተቀመጠባቸውን ጥፋቶች ያደረሰ ከ፮ ወር በማያንስና እስከ ፭ ዓመት በሚደርስ እስራትና እስከ ፴ሺ በሚደርስ መቀጮ ይቀጣል፣ (ሰረዝ የተጨመረ)
(የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ቻርተር አዋጅ ቁ. 87/1989 አንቀጽ 3 ንዑስ አንቀጽ 3)
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ደንቦች፤ መመሪያዎችና ውሳኔዎች አገራዊ ጥቅምን ይጎዳሉ ተብሎ ሲታመን በፌደራሉ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስቴር ሊታገዱና ሊሻሩ ይችላሉ፡፡

የአስተዳደር መንግስት እና የአስተዳደር ህግ ውልደት 


የአስተዳደር መንግስት እና የአስተዳደር ህግ ውልደት 

የአስተዳደር ህግ ግብና ተግባራት//የህጉ ምንጮች፣ /የተፈጻሚነቱ ወሰን

በ19ኛው ክፍለ ዘመን ገኖ የነበረው የነፃ ገበያ (laisse faire) ንድፈ ሀሳብ በዋነኛነት ውስን የመንግስት ጣልቃ ገብነትና ሰፊ የግለሶቦች ነፃነትን ያቀነቅናል፡፡a በዚሁ ንድፈ ሀሳብ መሰረት የመንግስት ሚና ህግና ስርዓት ከማስጠበቅና አገርን ከጠላት ወረራ ከመከላከል የዘለለ መሆን የለበትም፡፡ ምርጥ መንግስት ማለት በስሱ (በትንሹ) የሚገዛ መንግስት ማለት ነው፡ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን መምራት፣ መቆጣጠርና መግራት እንደ መንግስት ኃላፊነት አይቆጠርም፡ሆኖም ነፃ የሆነው የገበያና የመንግስት ስርዓት እግረ መንገዱን ይዞ የመጣቸው አሉታዊ ውጤቶች በዋነኛነት ያረፉት በደካማውና ደሀው የህብረተሰብ ክፍል ጫንቃ ላይ ነበር፡፡ በሀብታምና ደሀ መካከል የተፈጠረው የሀብት ድልድል ልዩነት በእጅጉ እየሰፋ በመምጣቱ ሀብታም የበለጠ ሲበለፅግ ደሃው ግን ይባስ እየቆረቆዘ መሄድ ጀመረ፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ መካከል የነበረው የመደራደር አቅም ልዩነት ታይቶ ለማይታወቅ የጉልበት ብዝበዛ ምክንያት ሆነ፡፡ እነዚህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠንቆች ለነፃ ገበያ ስርዓትና አስተሳሰብ ፈታኝ ሁኔታዎች ነበሩ፡ስለሆነም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠንቆች መፍትሔ መስጠት የመንግስት ግዴታና ኃላፊነት የመሆኑ እውነታ ቀስ በቀስ እየተገለጠ መጣ፡፡b በተለይም የሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ የተከሰቱት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የመንግስት ጣልቃ ገብነት አስፈላጊነትን ከመቼውም ጊዜ በላይ በገሃድ አስረግጠዋል፡፡ መንግስት ኃላፊነቱን መወጣት የሚችለው ደግሞ አወቃቀሩና አደረጃጀቱ ሲገፉት የሚፍረከረክ ዓይነት ‘ልል’ ወይም ውስን መንግስት መሆኑ ቀርቶ ጡንቻው የዳበረና ስልጣኑ የሰፋ ጠንካራ መንግስት ሆኖ ሲገኝ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠንቆች መፍትሔ መስጠት የመንግስት ግዴታ ነው ሲባል ሚናው ከተለመደው ስርዓትና ፀጥታ ማስከበር ባሻገር ሰፊና ውስብስብ አዎንታዊ ተግባራትን ወደ ማከናወን መሸጋገር እንደሆነ ልብ ይሏል፡፡በዚሁ መሰረት የመንግስት ሚና ቀስ በቀስ ከፖሊስነት (Police State) ወደ ማህበራዊ አገልግሎት አቅራቢነት ሊሸጋገር ችሏል፡፡ መንግስት በአገልግሎት አቅራቢነት ሚናው ውሀ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ መንገድ ወዘተ የመሳሰሉ መሰረታዊ ፍላጐቶችን የማሟላት ኃላፊነት ተጥሎበታል፡፡ በተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅጣጫውን ፈር ለማስያዝና ፍትሐዊ የሀብት ድልድል እንዲኖር እንዲሁም ለደካማው የህብረተሰብ ክፍል ጥበቃና ከለላ ለማድረግ በአጠቃላይ የነፃ ገበያን አሉታዊ ውጤቶችን ለመቀነስ ሰፊና ተከታታይ ቁጥጥርና ክትትል (Regulation) ያደርጋል፡፡ አዲሱ የማህበራዊ መንግስት አዲሱን አዎንታዊ ሚናውን በብቃትና ውጤታማ በሆነ መንገድ ይወጣ ዘንድ በዓይነትና በይዘት የጠንካራ ስልጣን ባለቤት ሊሆን የግድ የሚል ሀቅ ነው፡፡የስልጣን አስፈላጊነቱ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ስልጣን በየጊዜው ወሰኑ፣ መጠኑና ቅርጹ እያደገና እየሰፋ በመጣ ቁጥር ግን የግለሰቦችን መብትና ነፃነት መንካቱ አይቀርም፡፡ የመንግስት ስልጣን እየተለጠጠ መሄድ አቅመቢስ ለሆነው ዜጋ የስጋት ምንጭ ነው፡፡ ፍፁም የሆነና ወደ ፍፁምነት የተጠጋ ስልጣን ወደ ህገ ወጥነትና የበዘፈቀደ ድርጊት የማምራት አደገኛ አዝማሚያ አለው፡:የአስተዳደር ህግ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የመንግስት ‘ጡንቻ መፈርጠም’ በቅጡ ለመቆጣጠር በታሪክ ሂደት በተጓዳኝ የተፈጠረ የህግ መሳሪያ ነው፡፡ መንግስት ተግባራቱን ለማከናወን ፖሊሲ ቀርጾ፣ ህግ አውጥቶ በሚያስፈጽምበት ወቅት በስልጣን እና በፍትህ (የግለሰቦች ነፃነት) መካከል ቅራኔ መከሰቱ የማይቀር እውነታ ነው፡፡ ጥያቄው ቅራኔው እንዴት ይፈታል? ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ የዚህ ቅራኔ የራሱ ውጤት ሲሆን ቅራኔውን በአንፃራዊ መልኩ ለማስማማትና ለማጣጣም በታሪክ ሂደት ብቅ ያለ ተግባራዊ መሳሪያ ነው፡፡d የአስተዳደር ህግ በዕቅድ ታስቦ የተወለደ ሳይሆን በሁኔታዎች አስገዳጅነት የተፈጠረ ክስተት ነው፡፡ ህጉ በሁለት በጉልበት የማይመጣጠኑ ጐራዎች ማለትም በመንግስትና በግለሰብ መካከል ሚዛናዊነትንና ፍትሐዊነትን ለማስፈን ይጥራል፡፡የአስተዳደር ህግ መንግስት በተለይ ስራ አስፈፃሚውና የአስተዳደር አካላት በህግ ከተፈቀደላቸው የስልጣን ክልል አልፈው ህገ ወጥ ድርጊት እንዳይፈጽሙ ቁጥጥር የሚያደርግና ይህንንም የሚያረጋግጥ ህግ ነው፡፡e በዚህም የህግ የበላይነት እንዲሰፍንና የግለሰቦች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዳይሸራረፉና እንዳይጣሱ ከለላ በመስጠትf ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ በተጨማሪም በህግ ማዕቀፍ ውስጥ ያለው ስልጣን በአግባቡና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል መሪ ደንቦችን በማስቀመጥና ስነ ስርዓታዊ ቅድመ ሁኔታዎችን በመዘርጋት የተለያዩ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችን በመጠቀም የግለሰቦችና የዜጐች መብቶችና ነፃነቶች እንዳይገሰሱና እንዳይደፈሩ ከለላ በመስጠት የህገ መንግስት ማስፈፀሚያ ሆኖ ያገለግላል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት በሀገሪቱ በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን በስልፍ ስለጠየቁ ብቻ በህዝቡ ላይ ሃገሪቱን የሚመራው መንግሥት የፈጸመው ግፍ ግድያና ጭፍጨፋ የዘር ማጥፋት የመንግስት ድርጊት ነው። እና ዜጎችን በጭቆና በሀይል በመግደል ሃገሪቱን እየመራ ይገኛል። በህገመንግስት መሰረት ዜጎች በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን የማሰማት መብት እንዳላቸው በህገመንግስቱ ተደንግጓል። ይህም፦በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 9/1 “ሕገ መንግሥቱ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ ነው፡፡ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግሥት አካል ወይንም ባለሥልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም” ተብሎ ተደንግጓልና፡፡


Doesn’t the government have a duty to uphold the rule of law and uphold the rule of law? Because the government that is running the country itself is not subject to law and constitutional order! The whole Ethiopian people are witnessing that he has not even complied with the court order to prove it! So how can I be a citizen safeguard if the government does not violate the law and the constitution? By what legal means?

አስተዳደራዊ ስልጣን


አስተዳደራዊ ስልጣን

ደንብና መመሪያ ማውጣት እንዲሁም የአስተዳደር ውሳኔ እና እርምጃ መውሰድ ህግ አስፈፃሚ አካላት ህግና ፖሊሲን ለመተግበር የሚያከናውኗቸው ተግባራት ናቸው

አስተዳደራዊ ስልጣን

ደንብና መመሪያ ማውጣት እንዲሁም የአስተዳደር ውሳኔ እና እርምጃ መውሰድ ህግ አስፈፃሚ አካላት ህግና ፖሊሲን ለመተግበር የሚያከናውኗቸው ተግባራት ናቸው፡፡ የእነዚህ አካላት ዋነኛ ስልጣንና ተግባር ህግ ማውጣት አሊያም ዳኝነት መስጠት ሳይሆን ማስተዳደር ነው፡፡ አስተዳደራዊ ስልጣን ከህግ ማውጣት እና ዳኝነት መስጠት ውጪ ያሉትን ተግባራት በሙሉ ያጠቃልላል፡፡ የአስተዳደር /ቤቶች አብዛኛውን ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ይህን የእለት ተእለት የአስተዳደር ስራ በማከናወን ነው፡፡
በዚህ ስልጣን ስር ከሚወድቁ በርካታ ምሳሌዎችን መካከል ሪፖርት ማቅረብ፣ ፓስፖርት መስጠት፣ ፍቃድ መስጠት፣ ማደስ፣ ፀጥታ ማስከበር፣ ክስ መመስረት፣ እድገትና ሹመት መስጠት፣ ምርመራ፤ ቁጥጥርና ክትትል ማካሄድ የምክር ሀሳብ መስጠት ወዘተ ሁሉም የአስተዳደር /ቤቶች አስተዳደራዊ ስልጣናቸውን በመጠቀም የሚያከናውኗቸው ስራዎች ናቸው፡፡
እነዚህ ተግባራት የህግ መጣስ መኖርን አለመኖሩን ለማረጋገጥ መረጃ በመሰብሰብና በማጠናቀር ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ የመረጃ አሰባሰብና ጥንቅር ስርዓት የንግድ ድርጅቶች በየጊዜው በሚያቀርቡት ሪፖርት ላይ ሊመሰረት ይችላል፡፡ ሆኖም አብዛኛውን ጊዜ የመረጃ አሰባሰብ ስርዓቱ በአካል ተገኝቶ ቀጥተኛ እና የአካባቢ ማስረጃዎችን በመሰብሰብ እና የማጣራት ስራዎችን በማከናወን ላይ መሰረት ያደረገ ነው፡፡
የመርማሪነት ስራ ህጉ ልዩ ስልጣን በሰጣቸው መርማሪዎች የሚከናወን ሲሆን የምርመራ ሂደቱም በህግ ማእቀፍ ውስጥ ይመራል፡፡ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን የፖሊስ የምርመራ ተግባር ነው፡፡ ፖሊስ ወንጀል ሲፈጸም ወይም ተፈጽሟል የሚል መረጃ ከደረሰው አሊያም ተገቢ ጥርጣሬ ካደረበት የወንጀል ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ በአካል በመገኘት ተጨባጭ ማስረጃዎችን የመሰብሰብ እና ተጠርጣሪውን የመመርመር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ ረገድ ሰፊ ስልጣናት አሉት፡፡ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአስተዳደር /ቤቶች የመርማሪነት፣ የቁጥጥርና ክትትል ስልጣን በወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ህጉ ለፖሊስ ከተሰጠው ስልጣን ቢበልጥ እንጂ አያንስም፡፡
በአስረጂነት በተወሰኑ ህጎች ለተቆጣጠሪዎች የተሰጣቸው መጠነ ሰፊ ስልጣን በማጣቀሻነት እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡
የአካባቢ ተቆጣጣሪዎች ስልጣንa
ሳያሳውቁ ወይም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሳይዙ በማንኛውም ተገቢ መስሎ በሚታያቸው ጊዜ ወደ ማንኛውም ቦታ ወይም ቅጥር ግቢ መግባት
ማንኛውንም ሰው ብቻውን ወይም በምስክር ፊት የመጠየቅ
ከብክለት ጋር ግንኙነት ያለውን ማንኛውንም ወረቀት፣ ማህደር ወይም ሌላ ሰነድ መፈተሽ፣ መገልበጥ ወይም ለይቶ መቅዳት
የማንኛውንም ቁስ ናሙናዎች እንደአስፈላጊነቱ ያለክፍያ መውሰድና በአካባቢ ወይም በህይወት ላይ ጉዳት የሚያደርስ መሆኑ አለመሆኑን ለመወሰን መመርመር ወይም ማስመርመር
የአካባቢ ብክለት ቁጥጥር አዋጅ ቁ. 300/1995 ወይም ሌላ ህግ መከበሩን ለማረጋገጥ ሸቀጥን፣ የአመራረት ሂደትን ወይም መገልገያን በፍቶግራፍ ማንሳት፣ መለካት፣ መሳል ወይም መፈተሽ
አዋጁን ወይም አግባብ ያለውን ሌላ ህግ በመተላለፍ ጥፋት ተፈጽሞበታል የተባለ መሳሪያን ወይም ሌላ ነገርን መያዝ
የዱር እንስሳት ቁጥጥር ሠራተኛ
ሕግን በመተላለፍ በይዞታ ስር የተደረጉ የዱር እንስሳት ወይም የዱር እንስሳት ውጤቶች ተደብቀዋል ብሎ ለማመን በቂ ምክንያት ሲኖር ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ ወደ ማንኛውም ሰው መሬት፣ ህንጻ፣ ድንኳን፣ ተሸከርካሪ፣ የአየር መንኮራኩር ወይም ጀልባ ውስጥ የመግባትና የመፈተሸ እንዲሁም ሻንጣ ወይም እሽግ የመፈተሸ
ሕግን በመተላለፍ በይዞታ ስር የተደረጉ የዱር እንስሳት ወይም የዱር እንስሳት ውጤቶችን እንዲሁም ጥፋቱ የተፈጸመባቸውን መሳሪያዎች እንዲወረሱ ለማድረግ እንዲቻል በቁጥጥር ስር የማድረግና የሚመለከተው አካል ባወጣው የመመዝገቢያ ቅፅ መሰረት ተገቢውን ደረሰኝ ሰጥቶ የመረከብ
የዱር እንስሳት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ማፅደቂያ አዋጅ ቁ. 541/1999 አንቀጽ 16 ድንጋጌዎች በመተላለፍ ጥፋት ሲፈጽም የተገኘን ሰው ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይዞ ለሚመለከተው ህግ አስከባሪ አካል ማስረከብ
የደን ውጤት ተቆጣጣሪ
የደን ውጤቶችን የጫነ ወይም ለመጫኑ የሚጠረጠርን ማናቸውንም ማጓጓዣ በደን መግቢያና መውጫዎች እንደአስፈላጊነቱ በሚመረጡ የሀገር ውስጥ እና የድንበር መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ላይ አስቁሞ መፈተሸ
የደን ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም አዋጅ ቁ. 542/1999 በመተላለፍ ተዘጋጅተው ሲጓጓዙ ወይም ተከማችተው የተገኙ የደን ውጤቶችን ከድርጊቱ ተጠያቂዎች ጋር የመያዝ
የቡና ጥራት ቁጥጥርና ግብይት አዋጅ ቁ. 602/2000 ለማስፈጸም የሚወጡ ደንብና መመሪያዎች መከበራቸውን ለማረጋገጥ ቡና ሊገኝበት ይችላል ተብሎ የሚገመትን መጋዘን፣ መኖሪያ ቤት፣ የመንግስት ድርጅት፣ ማጓጓዣ ወይም ማናቸውም ሌላ ቦታ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወይም አስቸኳይ ሁኔታ ሲኖር ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ የመፈተሽ፣ህገ ወጥ ቡና ሲያዝ የማሸግ፣ ምርቱን የማገድ፣ የመያዝ፣ ህገ ወጥነታቸው የማያጠራጥር ሲሆን የቡናው ባለቤት ለፍርድ ቤት ቅሬታ የማቅረብ መብቱ እንደተጠበቀ ሆኖ የመውረስና የመሸጥ.

የአስተዳደር ህግ እና ህገ መንግስታዊ መርሆዎች የአስተዳደር ህግ እና የህገ መንግስት ትስስር እና ተዛምዶ የህግ የበላይነት የስልጣን ክፍፍል


የአስተዳደር ህግ እና ህገ መንግስታዊ መርሆዎች
የአስተዳደር ህግ እና የህገ መንግስት ትስስር እና ተዛምዶ የህግ የበላይነት የስልጣን ክፍፍል

1-⚖️ የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት አፈፃፀም መሰረታዊ የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች ተጠያቂነት ግልፅነት እና የህዝብ ተሳትፎ 2-⚖️ የአስተዳደር ህግ እና ህገ መንግስታዊ መርሆዎች የአስተዳደር ህግ እና የህገ መንግስት ትስስር እና ተዛምዶ የአስተዳደር ህግ ጽንስቱ ሆነ ውልደቱ ከህገ መንግስት እንደመሆኑ ከዚህ የህግ ክፍል ጋር ብዙ ባህርያትን ይጋራል፡፡

ሁለቱም የመንግስትና የግለሰብ ግንኙነትን በሚመራው ‘የህዝብ አስተዳደር ህግ’ ተብሎ በሚጠራው የህግ ክፍል ውስጥ ይመደባሉ፡፡ አብዛኛዎቹ የአስተዳደር ህግ ጥያቄዎች በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የህገ መንግስታዊነት ጥያቄዎችን ያስነሳሉ፡፡ የአስተዳደር ህግን በጥልቀት ለመረዳት ከተፈለገ ሂደቱ መጀመር ያለበት ህገ መንግስትን በማጥናት ነው፡፡ በምሁራኑ አንደበት ይኸው እውነታ እንዲህ ይገለፃል፡፡ የአስተዳደር ህግ ከህገ መንግስታዊ መሰረቱ ተለይቶ በደንብ ሊታወቅ ሆነ ሊጠና አይችልም፡፡ የአስተዳደር ህግ በህገ መንግስት ማስፈጸሚያ መሳሪያነቱ የዝምድናቸውን ገጽታ በሚገባ ለማወቅ ይረዳናል፡፡ በዚህ የተግባሪነት ሚናው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ላይ የተቀመጡትን የህገ መንግስታዊነትና የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች እንዲሁም የግለሰቦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በተጨባጭ እንዲረጋገጡ በማድረግ ህገ መንግስቱን በማስፈጸም ረገድ እንደ አንድ መሳሪያ ያገለግላል፡፡ እ.ኤ.አ በ1959 ዓ.ም. የጀርመን የፌደራል አስተዳደር ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት እንደተናገሩት የአስተዳደር ህግ ‘ተጨባጭ ህገ መንግስት’ ማለትም በተግባር የሚታይ ህገ መንግስት ነው፡፡a የአንድ አገር ህገ መንግስት በዋነኛነት የዜጐችን ሰብአዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፖለቲካዊ መብቶችና ነጻነቶች ይደነግጋል፡፡ የዜጐች መብት በሌላ ግለሰብ፣ ማህበር ወይም የንግድ ድርጅት ሊጣስ ይችላል፡፡ ትልቁ አደጋ ያለው ግን ከመንግስት በተለይም ከስራ አስፈፃሚው አካል በኩል ነው፡፡ መብቶች በሚገባ እንዲጠበቁ የመንግስት አስተዳደር ልኩ ተለይቶ በታወቀ የስልጣን ገደብ ውስጥ ሊከናወን ይገባል፡፡ ሆኖም ስልጣን ሁልጊዜ በህጉ መሰረት ግልጋሎት ላይ ይውላል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ የግድ በአግባቡ ሊገራና ልጓም ሊበጅለት ይገባል፡፡ የአስተዳደር ህግ የስልጣን መቆጣጠሪያ መሳሪያ ነው፡፡ በዚህ ተግባሩ ውጤታማ የስልጣን ቁጥጥር የዜጐች ህገ መንግስታዊ መብትና ነፃነት እንዳይጣስ ዋስትና ይሰጣል፡፡ መንግስቱን በተግባር እንዲተረጐም የሚደርገውም በዚህ መንገድ ነው፤ ስልጣንን በመቆጣጠር የዜጐችን መብት በተጨባጭ ማቀዳጀት፡፡ ይህ ሚናውን በሌሎች ህገ መንግስታዊ መርሆዎች አንጻርም ጎልቶ ይታያል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት በዋነኛነት ከሚደነግጋቸው የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች መካከል ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና የህዝብ ተሳትፎ ይገኙበታል፡፡b ግልጽነት እውን የሚሆነው የመንግስት ባለስልጣናትና የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ለዜጐች መረጃ የመስጠት ግዴታቸው ከነዝርዝር አፈፃፀሙ ጭምር በህግ ተደንግጐ ሲገኝ ነው፡፡ ተጠያቂነት፤ ጠያቂውና ተጠያቂው ተለይቶ የተጠያቂነት ስልቱ በዝርዝር ህግ ካልተቀመጠ በተግባር አይረጋገጥም፡፡ የህዝብ ተሳትፎ እንዲሁ የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች በሚሰጡት ውሳኔ በተለይም ደንብና መመሪያ ሲያወጡ በጉዳዩ ጥቅም ካላቸው ወገኖች ሀሳብና አስተያየት እንዲቀበሉ የሚያስገድድ የህግ ድንጋጌ ከሌለ የህዝብ ተሳትፎ በተጨባጭ አይታይም፡፡ ግልፅነትን፣ ተጠያቂነትንና የህዝብ ተሳትፎን በተግባር ለማረጋገጥ የሚወጡ ህጐች በአስተዳደር ህግ የሚካተቱ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ህጉ እነዚህ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች በተግባር እንዲረጋገጡ በማድረግ ህገ መንግስቱን ያስፈጽማል፡፡ በህገ መንግስትና በአስተዳደር ህግ መካከል ያለው የጠበቀ ግንኙነት ልዩነታቸው የላላ መሆኑን ያሳያል፡፡ ሊጠቀስ የሚችል ቀጭን ልዩነት ቢኖር የወሰን እና የህጎች የተፈጻሚነት ደረጃ (Hierarchy of Laws) ልዩነት ነው፡፡ ከወሰን አንፃር ህገ መንግስት አጠቃላዩን የመንግስት አወቃቀርና የሶስቱን የመንግስት አካላት ብሎም በፌደራልና በክልል መንግስታት ያለውን የስልጣን ክፍፍል ስለሚወስን በይዘቱ በጣም ሰፊ ነው፡፡ በአንፃሩ የአስተዳደር ህግ የአንደኛውን የመንግስት አካል ማለትም የስራ አስፈፃሚውን ስልጣን፣ ግዴታና ተግባር ብሎም የውሳኔዎቹን ህጋዊነት የሚመለከት ህግ ነው፡፡ በህግ አውጭው የሚወጣ ህግ እና ፍ/ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ ህገ መንግስታዊነት ከጥናት አድማሱ በላይ ነው፡፡ ስለሆነም ከወሰናቸው አንጻር ህገ መንግስት መስፋቱ የአስተዳደር ህግ መጥበቡ እንደ አንድ የልዩነት ነጥብ ተደርጐ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ሁለተኛው ልዩነት የህጎች መሰላል (Hierarchy of Laws) ሲሆን በህጐች መካከል ያለውን የደረጃ ዝምድና ይመለከታል፡፡ ህገ መንግስት የአንድ አገር የበላይ ህግ እንደመሆኑ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረኑ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና የአሰራር ልምዶች ዋጋ የላቸውም፡፡ የአስተዳደር ህግ በደረጃው ከህገ መንግስት ዝቅ ብሎ የሚገኝ እንደመሆኑ መቼም ቢሆን ከህገ መንግስቱ ጋር መጣጣም አለበት፡፡ ግጭት በተነሳ ጊዜ የበላይ የሆነው ህገ መንግስት ሁልጊዜ ተፈፃሚነት አለው፡፡

Pecuniary Effects of Marriage Article 57. – personal property of Spouses


Pecuniary Effects of Marriage Article 57. – personal property of Spouses (1) property not acquired by Onerous Title. The property which the spouses possess on the day of their marriage, or which they acquire after their marriage by succession or donation, shall remain their personal property. Article 58. – (2) Property Acquired by Onerous Title. 1) Property acquired, by onerous title, by one of the spouses after marriage shall also be personal property of such spouse where such acquisition has been made by exchange for property owned personally, or with monies owned personally or derived from the sale of property owned personally. 2) The provisions of Sub-Article (1) of this Article shall apply only when the court, at the request of one of the spouses, has decided that the property thus acquired shall be owned personally by such spouse. Article 59. – Administration of Personal Property (1) Principle. 1) Each spouse shall administer his respective personal property and receive the income thereof. 2) Each spouse may freely dispose of his personal property. Article 60. – (2) Determination by Contract of Marriage. 1) It may be agreed in the contract of marriage that one of the spouse shall administer all or part of the personal property of the other spouse and that he may dispose of such property. 2) The spouse who is entrusted with the power of administering the property under Sub-Article (1) of this Article shall, at the request of the other spouse, submit an annual statement of accounts of the management of such property. Article 61. – (3) Agency. One of the spouse may freely entrust to the other spouse the administration of all or part of his personal property. Article 62. – Common Property of Spouses. 1) All income derived by personal efforts of the spouses and from their common or personal property shall be common property. 2) All property acquired by the spouses during marriage by an onerous title shall be common property unless declared personal under Article 58 (2) of this Code. 3) Unless otherwise stipulated in the act of donation or will, Property donated or bequeathed conjointly to the spouses shall be common property. Article 63. – Legal Presumption 1) All property shall be deemed to be common property even if registered in the name of one of the spouses unless such spouse proves that he is the sole owner thereof. 2) The fact that certain property is personal may not be set up by the spouse against third parties unless the latter knew or should have known such fact. Article 64. – Income of Spouse(1) Normal Management. 1) Each spouse shall receive his earnings. 2) The spouses may deposit their respective earnings either in personal or joint bank account. 3) One of the spouses shall, at the request of the other spouse, render an account to the latter of the income received by him. Article 65. – (2) Exception. 1) One of the spouses may freely give the other spouse a mandate to receive the income which is due to him. 2) The court may, at the request of one of the spouses, authorize such spouse to receive the income of the other spouse and to give receipt thereof. 3) Unless other laws provide otherwise, the court may also order the full or partial attachment of the income of either spouse. Article 66. – Administration of Common Property. 1) Common property shall be administered conjointly by the spouse unless there is an arrangement which empowers one of them to administer all part of the common property. 2) Where one of the spouse is declared incapable, or is deprived of his right of property management or for any other reason is unable to administer the common property, the other spouse shall alone administer such common property. Article 67. – Duty to give Notice. The spouse who performs an act of management in respect of common property is duty bound to inform the other spouse thereof. Article 68. – (1) Requisite of Agreement of Spouses Unless provided otherwise by other laws, the agreement of both spouses shall be required to; (a) Sale, exchange, rent out, pledge or mortgage or alienate in any other way a common immovable property to confer a right to third parties on such property; (b) Sale, exchange, pledge or mortgage, or alienate in any other way, a common movable property or securities registered in the name of both spouses: the value of which exceeds five hundred Ethiopian birr. (c) Transfer by donation of a common property the value of which exceeds one hundred Ethiopian birr, or money which exceeds such amount; (d) Borrow or lend money exceeding five hundred Ethiopian birr or to stand surety for a debt of such amount to another person. Article 69. – (2) Absence of Agreement. 1) Where one of the spouses has entered into obligations in violation of the provision of the preceding Article, the court may, at the request of the other spouse, revoke such obligations. 2) An application for cancellation may not be made six months after the day on which the other spouse came to know the existence of such obligation, or, in any case, two years after such obligation is entered. Article 70. – Debts of Spouses. 1) Debts due by one spouse may be recovered on the personal property of the indebted spouse, and in the absence of such personal property, it may be recovered on the common property. 2) Where the dept is incurred in the interest of the household, it shall be deemed to be joint and several debt of both spouses and may be recovered on the common property and on the personal property of either of the spouses. Article 71. – Debts in the Interest of Household. The following debts shall be deemed to be debts incurred in the interest of the household: (a) Debts incurred to fulfill the livelihood of the spouses and their children: (b) Debts incurred in order to fulfill an obligation of maintenance to which both the spouses or one of them is bound; (c) Other debts which are acknowledged to be such by the court at the request of either of the spouses or the creditor. Article 72. – Contribution to Household Expenses. The spouses shall contribute to the household expenses in proportion to their respective means. Article 73. – Contracts Between Spouses. Contracts entered into between spouses during marriage shall be of no effect unless approved by the court.  

ግልጽና ተጓዳኝ ስልጣን


ጽና ተጓዳኝ ስልጣን

ስልጣንአብዛኛውን ጊዜ ለመንግስት አካላት የሚደለደለው ስልጣን አሻሚ ባልሆነ አነጋገር ይገለጻል፡፡ ግልጽና ቀጥተኛ ስልጣን በአስተዳደሩ ውስጥ ህጋዊነትን ያሰፍናል፡፡ በተጨማሪም ስልጣንን በመገልገል ረገድ ጥርጣሬና ብዥታን ያስወግዳል፡፡ በተግባር ሲታይ ግን ለውጤታማ አስተዳደር አስፈላጊ የሆኑትን ስልጣናትና ተግባራት መዘርዘር ያዳግታል፡፡ ስለሆነም በግልጽ ስልጣን ውስጥ አስፈላጊ የሆነ በዝምታ የሚተላለፍ ተጓዳኝ ስልጣን ይኖራል፡፡ አንድን ድርጊት ለመፈፀም ግልጽ የሆነ ስልጣን ሲሰጥ የድርጊቱ አካል የሆኑና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራትን ለማከናወን የሚያስችል በዝምታ የሚሰጥ ስልጣን ስለመኖሩ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ የህጉን ዓላማና ግብ እንዲሁም የህጉን ድንጋጌዎች አነጋገር በጥልቀት መፈተሽ ይጠይቃል፡፡ ተጓዳኝ ስልጣን መኖሩን ለመወሰን የሚከተሉት ነጥቦች ግምት ውስጥ ይገባሉ፡፡የህጉ አነጋገርይህ የህግ አውጭውን ሀሳብ ለማወቅ ወሳኝነት አለው፡፡ ለምሳሌ የመንግስት እና የግል ድርጅት ሠራተኞች ኤጀንሲዎች በሚያስፈጽሟቸው አዋጆች መሰረት ለማናቸውም ዓይነት አበል ብቁ የሚያደርጉ ሁኔታዎች መሟላታቸውን የማረጋገጥና የአበሉን ዓይነትና መጠን የመወሰን ስልጣን አላቸው፡፡ ለአበል ብቁ የሚያደርጉ ሁኔታዎች በአዋጅ ቁ. 714/2003 እና 715/2003 የተለያዩ ድንጋጌዎች በዝርዝር ተለይተዋል፡፡ ኤጀንሲዎቹ እነዚህን ሁኔታዎች መኖራቸውን የመወሰን ስልጣናቸው ክርክር አያስነሳም፡፡ ለምሳሌ በአዋጅ ቁ. 714/2003 አንቀጽ 41 መሰረት ለሟች ሚስት ወይም ባል የሚከፈለው የጡረታ አበል ሟች ያገኝ ወይም ሊያገኝ ይችል የነበረው የጡረታ አበል 50 በመቶውን ነው፡፡ በዚሁ ድንጋጌ ላይ ባል ወይም ሚስት የጡረታ አበል በመቀበል ላይ እያሉ ጋብቻ ከፈጸሙ አበሉ የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች ተመልክተዋል፡፡ እነዚህን ጉዳዮች መወሰን በኤጀንሲዎቹ ስልጣን ስር ቢሆንም የባልነት ወይም ሚስትነት ጥያቄ በተነሳ ጊዜ ይህንን ማረጋገጥ ከስልጣናቸው ክልል በላይ ነው፡፡ ይህን መወሰን በመደበኛ የዳኝነት አካላት ስልጣን ስር ይወድቃል፡፡ ስለሆነም ‘ለአበል ብቁ የሚያደርጉ ሁኔታዎች’ የሚለው አነጋገር በሁለቱም አዋጆች ላይ መለኪያና መስፈርት የተቀመጠላቸውን ሁኔታዎች እንጂ በሌሎች ህጎች የሚወሰኑትን አያካትትም፡፡ የህግ አውጨው ሀሳብም ኤጀንሲዎቹ ለአበል ብቁ የሆኑ የሟች ሚስት ወይም ባል የሚከፈላቸውን መጠንና እና ክፍያውን የሚቋረጥባቸውን ሁኔታዎች እንዲወስኑ እንጂ ከመነሻው ባልነት ወይም ሚስትነትን በተመለከተ ማስረጃ አሰባስበው ውሳኔ እንዲሰጡ አይደለም፡፡በግልጽ የተሰጠው ስልጣን ወሰን
ስልጣኑ በጠባቡ ከተሰጠ ተጓዳኝ ስልጣን ስለመኖሩ በጠባቡ መተርጐም ይኖርበታል፡፡ በአንጻሩ ሰፊ የሆነ ስልጣን በውስጡ አስፈላጊ የሆኑ ተጓዳኝ ስልጣናትን ያቅፋል፡፡ለምሳሌ በተሽከርካሪ አደጋ የሶስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁ. 799/2005 አንቀጽ 13 ላይ እንደተመለከተው አንድ ተሽከርካሪ የመድን ተለጣፊ ምልክት ከሌለው የመድን ሽፋን እንደሌለው ስለሚያስቆጥረው የመድን ዋስትና ሰርተፊኬት እስኪመጣ ድረስ ፖሊስ ተሽከርካሪውን ይዞ የማቆየት ስልጣን አለው፡፡ በዚህ ድንጋጌ የፖሊስ የስልጣኑ ወሰን ጠባብ ነው፡፡ መኪናውን ከመያዝና ለማቆያ በተዘጋጀ ስፍራ ላይ ከማስቀመጥ ውጪ ሊወስድ የሚችለው ተጓዳኝ እርምጃ የለም፡፡ይህንን የፖሊስ ስልጣን አካባቢንና ብክለትን የመቆጣጠር ኃላፊነት ካለባቸው አካላት ስልጣን ጋር ብናነጻጽረው ልዩነቱ በግልጽ ይታያል፡፡
የአካባቢ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስቴር ወይም የሚመለከተው የክልል ባለስልጣን በአካባቢ ላይ አደጋ እንዳያስከትል ከሚያሰጋ የስራ እንቅስቃሴ ሊመጣ የሚችል ጉዳትን ለመከላከል ድርጅትን እስከ መዝጋት ወይም ወደ ሌላ ቦታ እስከማዛወር የሚደርስ ማንኛውንም አስፈላጊ እርምጃ መውሰድ ይችላል፡፡
ድርጅትን እስከመዝጋትና ወደ ሌላ ቦታ እስከማዛወር የሚደርስ ስልጣን ድርጅቱን የማሸግና ሠራተኞች እንዳይገቡ የመከልከል እንዲሁም ጉዳት ለመቀነስ የሚያስፈልጉ ተጓዳኝ እርምጃዎችን የመውሰድ ስልጣን ጭምር ያካትታል፡፡የህጉ ዓላማ የህጉ አጠቃላይ ዓላማና ግብ በግልጽ ከተቀመጠው ስልጣን በተጨማሪ የህጉን ዓላማ ለማሳካት የሚረዱ ስልጣናት ስለመኖራቸው አመላካች ነው፡፡ ተጓዳኝ ስልጣን ሳይኖር የህጉን ዓላማ በተግባር ማሳካት የማይቻል ከሆነ በዝምታ የተሰጠ ስልጣን ስለመኖሩ ግምት ይወሰድበታል፡፡የድርጊቱ ዓይነትና /ባህርይ/ ይዘትበግልጽ የተሰጠው ስልጣን ማዕቀብ የሚጥል ድርጊት ወይም እርምጃ ከሆነ ተጓዳኝ ስልጣን ስለመኖሩ በጠባቡ መተርጐም ይኖርበታል፡፡ ለምሳሌ የመቆጣጠር ስልጣን በውስጠ ታዋቂነት የመከልከል ስልጣንን አይጨምርም፡፡

Administrative law and human rights enforcement.


Administrative law and human rights enforcement. It has been repeatedly stated that as the power of the state expands, it is against the rights and freedoms of citizens. Administrative law recognizes the importance of authority. Effective governance and efficient service delivery are needed, not just tyranny. However, power that deviates from the law and the constitution weighs the benefits. Arbitrary actions, such as ‘I can do whatever I want, I can do whatever I want!’, Undermine the basic right to live, move freely, to speak, to express one’s opinion, and to own property. The role of administrative law in protecting human rights clearly illustrates the connection between the two. In order to better understand the positive impact of the law on the protection and implementation of human rights, it is appropriate to analyze the government’s commitment to human rights. These roles are to protect respect and enforcement. First, the role of government in respecting rights restricts interference from any part of the government when citizens exercise their rights freely. Especially in the so-called basics of living, writing, speaking; To follow the religion of your choice; The rights and freedoms of freedom of movement and property are guaranteed in practice when the government raises its hand. These rights are determined by the government, particularly by the executive and its subordinate administration; Order: They may be endangered by rules and regulations. As the Constitution is the supreme law, not all laws, decisions and practices that contradict this will be enforced. Such a question of constitutionality does not fall into the category of administrative law. However, the question of what constitutes a constitution is more likely to be covered by the administrative law framework. If a directive issued by a governing body violates the human rights of citizens beyond the power of attorney given by the legislature, it is a matter of constitutionality, but it is a matter of legality that must be addressed by the administrative law. To better understand the difference, let’s look at the following instructions from the former Ministry of Revenue and the current Revenue and Customs Authority. No customs officer can strike or strike. The right to peaceful assembly is guaranteed by the FDRE Constitution. Article 30, sub-paragraph 1, which gives him the right, reads as follows: Everyone has the right to freedom of peaceful assembly and association. When a directive is issued by the executive, there must be a clear delegate from the legislature. The directive is beyond the scope of the power of attorney (Ulta vires). It is therefore null and void before the law. When the Ministry of Revenue issued this directive, the proclamation to establish the source of power and the decision of the Customs Authority. 368/1995 refers to Article 8 (2) (c). This legal provision reads as follows. The Ministry of Police, assigned by the Federal Police Commission to enforce customs law, shall operate in accordance with the directives issued by the Federal Police Proclamation. Manages. When disaster strikes, he dismisses it. This article does not authorize the Ministry of Revenue to prohibit customs officers from conducting peaceful demonstrations. This directive, issued without the explicit authorization of the House of Representatives, is neither valid nor enforceable. Administrative law enforces the government’s obligation to respect human rights by enforcing such directives in various ways to prevent the violation of citizens’ rights and freedoms. Government enforcement responsibilities are often social; It is directly related to economic and cultural rights. It is not enough for the government not to interfere in the rights of citizens or to raise its hand. If he does not provide basic services to the citizen, such as health, electricity, water, roads, etc., he will not be free. The relationship between administrative law and human rights can also be examined in terms of the government’s obligation to enforce it. In this regard, the government must strengthen its regulatory and institutional mechanisms to ensure that human rights are not violated, and that it must establish a system of immediate justice for victims of human rights abuses. In short, in order for human rights to be respected, the government needs to formulate, establish, and develop a well-developed administrative law and administrative system.

መሰረታዊ የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች፣


መሰረታዊ የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች መልካም አስተዳደር ምንም እንኳን በጥቅሉ ሲታይ ፖለቲካዊ፤
ኢኮኖሚያዊና ተቋማዊ እንዲሁም የአመራር እና የአሰራር ሂደቶችን የሚመለከቱ ዘርፈ ብዙ እንደምታዎች ያሉት ቢሆንም በህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሲታይ ግን ከአስተዳደር ፍትህ ጋር አቻ ሆኖ ሊገለጽ ይችላል፡፡
መልካም አስተዳደር ዋና ግቡ ዜጐች ብቁና ውጤታማ አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል እንዲሁም የሚደርስባቸውን አስተዳደራዊ በደል መቅረፍ እና አስተዳደራዊ ፍትህን እውን ማድረግ እንደመሆኑ ሁለቱን ነጣጥሎ ማየት ያስቸግራል፡፡
መልካም አስተዳደር ሆነ የአስተዳደር ህግ በራሳቸው አቅጣጫና ሂደት ተጉዘው የግባቸው መድረሻ አስተዳደራዊ ፍትህን ማስፈን ነው፡፡
ስለሆነም በይዘቱ ሰፊ በሆነ የመልካም አስተዳደር እሳቤ ውስጥ የአስተዳደር ህግ አንድ ቁስ ሆኖ በማገልገል የተቆራኘና የተዛመደ ተግባራዊ እገዛ ያደርጋል፡፡ በመልካም አስተዳደርና በአስተዳደር ህግ መካከል ያለውን ተዛምዶ በቅጡ ለመቃኘት ህግ በአስተዳደሩ አካሄድ (Administrative behavior) ወይም በስራ አስፈፃሚው እንቅስቃሴ ላይ ምን አይነት አዎንታዊ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል? ለሚለው ጥያቄ በተግባር የታገዘ ጥልቅ ጥናት ምላሽ መስጠት ይጠይቃል፡፡ ይሁን እንጂ በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉትን ሚናዎችና ተግባራት ቢያንስ እንደጠቅላላ ሀሳብ በመውሰድ የአስተዳደር ህግ እንደ አንድ የህግ ዘርፍ የራሱ አዎንታዊ ፋይዳ እንዳለው መደምደም እንችላለን፡፡ ያም ሆኖ ግን አስተዳደሩ መልካም እንዲሆን የአስተዳደር ህግ ስልጣን ከመቆጣጠር ባሻገር እንዴት ተቃኝቶ መቀረጽ አለበት? የሚለው ጥያቄ ለአስተዳደር ህግ አጥኚዎች ሆነ ምሁራን የውይይት ምንጭ ብቻ ሳይሆን የጥናት መሰረት መሆን ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ የመልካም አስተዳደር እና የአስተዳደር ህግን ተዛምዶ ለማየት የሁለቱም መድረሻ ከሆነው የአስተዳደር ፍትህ ትርጓሜ እንነሳለን፡፡ የአስተዳደር ፍትህ በህግ ስልጣን የተሰጣቸው የመንግስት አካላት ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ወቅት ከዜጐች መብትና ነፃነት አንጻር ፍትሃዊ መሆን እንዳለባቸው የሚደነግግ መርህ ነው፡፡ የመንግስት አስተዳደር ፍትሃዊ ሲሆን መልካም ይሆናል፡፡ የአስተዳደር ፍትህን በማሳካት ረገድ ሁለት ዓበይት ነጥቦች ቁልፍ ቦታ ይኖራቸዋል፡፡ ይኸውም፡- አንደኛ፦ የመንግስት ባለ ስልጣናት ወይም የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ወቅት አነስተኛ ለሆኑ የስነ-ስርዓት ደንቦች እና ተቀባይነት ላላቸው መርሆዎች መገዛት አለባቸው፡፡ ከአነስተኛ የስነ-ስርዓት ደንቦች በተጨማሪ የመንግስት አስተዳደር ተቀባይነት ባላቸው የህግ፣ የአስተዳደርና የፍትህ መርሆዎች መመራት አለበት፡፡ ከእነዚህ መካከል በዋናነት የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ የህጋዊነት መርህ (ህጋዊ ስልጣን ሳይኖር አንዳችም እርምጃ አለመውሰድ፤ በህጉ መሰረት መወሰን) የሚዛናዊት መርህ (የአስተዳደር አካላት ውሳኔ ወይም እርምጃ እንደየሁኔታው ብዙ ነገሮች ግምት ያስገባ እንጂ ፍርደገምድል መሆን የለበትም፡፡) የተመጣጣኝነት መርህ (የሚወሰደው እርምጃ ተፈጸመ ከተባለው ጥፋት አንፃር ተመጣጣኝ መሆን አለበት፡፡) የእኩልነት መርህ (ተመሳሳይ በሆኑ ሁኔታዎች ወይም ጉዳዮች አስተዳደሩ የተለያየ ውሳኔ ላይ መድረስ የለበትም፡፡ ተመሳሳይ ሁኔታዎች በተመሳሳይ መንገድ መወሰን አለባቸው፡፡) ለውሳኔ በቂ ምክንያት መስጠት (አስተዳደራዊ ውሳኔ የተወሰደበት ምክንያት በግልጽ መጠቀስ አለበት፡፡ ውሳኔውም ፈጽሞ የማያሳምንና ኢ- ምክንያታዊ መሆን የለበትም፡፡) ሁለተኛ፦ ከላይ የተመለከቱትን ደንቦችና መርሆዎች በመጻረር በህግ ከተወሰነው ስልጣን በላይ እርምጃ ከተወሰደ መብታቸው የተጐዳ ዜጐች አቤቱታ አቅርበው ፍትህ (መፍትሄ) የሚያገኙበት መንገድ መኖር አለበት፡፡ በአስተዳደር አካላት መብታቸው የተጣሰ ሰዎች ቀላል በሆነ ስነ-ስርዓት አቤቱታ አቅርበው ቀልጣፋ መፍትሔ የሚያገኙበት አሰራር ወይም መንገድ ከሌለ የአስተዳደር ፍትህ አለ ለማለት አይቻልም፡፡ ለምሳሌ አካልን ነፃ የማውጣት መብት በህገ-ወጥ መንገድ ከ48 ሰዓት በላይ የታሰረ ሰው ራሱ በቀጥታ ወይም በሌላ ሶስተኛ ወገን በቀላሉ አቤቱታ አቅርቦ ነፃ የሚለቀቅበት ፈጣን ስነ-ስርዓት ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በህገ ወጥ መንገድ ንብረቱን በአስተዳደደሩ የተቀማ ወይም ፈቃዱ አለአግባብ የተሰረዘበት ሰው ቀላል በሆነ ስነ-ስርዓት መፍትሔ የሚያገኝበት የህግ ድንጋጌ ሊኖር ይገባል፡፡ ለዚህም ነው የአስተዳደር ህግ መኖር ለአስተዳደራዊ ፍትህ ሆነ ለመልካም አስተዳደር ወሳኝ መሳሪያ ነው የሚባለው፡፡ የአቤቱታው ስርዓት እንዳለ ሆኖ የአስተዳደራዊ ፍትህ የሚገኝበት ተቋም ገለልተኛ፣ ተደራሽ እና ነፃ ሆኖ ቀልጣፋና ውጤታማ ግልጋሎት መስጠት መቻሉ የአስተዳደር ፍትህን በማሳካት ረገድ ዋናውና መሰረታዊው ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡

EFFECTS OF VIOLATIONS OF ESSENTIAL CONDITIONS OF MARRIAGE


EFFECTS OF VIOLATIONS OF ESSENTIAL CONDITIONS OF MARRIAGE

  Article 31. – Age

1) Without prejudice to Sub-Article (2) of Article 7 of this Code, marriage concluded by a man or a woman under the age of eighteen years shall dissolve on the application of any interested person or the public prosecutor. 2) It may no longer be applied for after the age required by law of marriage is satisfied.   Article 32. – Consanguinity of Affinity. The dissolution of marriage concluded in violation of impediments arising out of consanguinity or affinity shall be ordered on the application of any interested person or the public prosecutor. Article 33. – Bigamy 1) The dissolution of a bigamous marriage shall be ordered on the application if either of the spouses of bigamous marriage or the public prosecutor. 2) The dissolution mentioned on Sub-Article (1) of this Article may no longer be applied for where the former spouse of the bigamous marriage has died. Article 34 . – Dissolution of Marriage of a Judicially Interdicted person. 1) Where a judicially interdicted person has contracted marriage without prior authorization of the court, the dissolution of such marriage may be requested from the court by the judicially interdicted person himself or by his guardian. 2) The judicially interdicted person may no longer make an application for dissolution six months after the date of termination of his disability. 3) An application for dissolution by the guardian may no longer be made six months after the day on which the guardian came to know the existence of the marriage or in any case, after the disability of the interdicted person has ceased. Article 35. – Act of Violence 1) Whosoever has concluded marriage under the influence of violence may apply to the court to order the dissolution thereof. 2) Such an application may not be made six months after the cessation of such violence and, in any case, two years after the conclusion of the marriage. Article 36. – Error 1) Whosoever has concluded marriage due to fundamental error, may apply to the court to order the dissolution thereof. 2) Such an application may not be made six months after the discovery of such error, and , in any case, two years after the conclusion of the marriage. Article 37. – Period of Widowhood. The dissolution of marriage may not be ordered for the sole reason that the period of widowhood specified under Sub-Article (1) of Article 16 has not been observed. Article 38. – Incompetence of Officer of Civil Status. The dissolution of marriage may not be ordered solely on the ground of incompetence of the officer of civil status who celebrated the marriage. Article 39. – Non-Observance of Formalities. The dissolution of marriage may not be ordered on the sole ground that the formalities of celebration specified under Sub Articles (3) and (6) of Article 25 have not been observed.

Defendant—Judge —Lawyer–


Defendant—— “I request that the Honorable Court appoint another lawyer”
Judge —— “What is your reason?”
Defendant—— “This defense attorney ignored my case”
Judge —— turned to the defense and said, “Uh! Do you have anything to complain about? ”
Defendant —— “😱 !? Lawyer _____What did they tell me? I’m sorry, my lord, I was not listening ”

የስልጣን ምንጭ⚖️



የስልጣን ምንጭ


የመንግስት ስልጣን በህግ ከተቀመጠለት ገደብ እንዳያልፍና ይህንንም በተግባር ለማረጋገጥ መጀመሪያ የስልጣንን ምንጭ እና መገለጫ ባህርያት በቅጡ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ለመሆኑ ስልጣን ከየት ይመነጫል? እንዴትስ ይገለጻል? የስራ አስፈፃሚውና የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች የስልጣን ምንጭ ህግና ህገ መንግስት ብቻ ነው፡፡ በህገ መንግስታዊ እና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ውስጥ ህዝብ የስልጣን ባለቤት መሆኑ የሚረጋገጠው የመንግስት ባለስልጣናት ስልጣን በህዝብ ከተመረጡ ተወካዮች የመነጨ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትሩንና የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ስልጣናት ጠቅለል ባለ አነጋገር ይዘረዝራል፡፡ የእያንዳንዱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ስልጣንና ተግባር ብዙውን ጊዜ አዲስ የምርጫ ዘመንን ተከትሎ በተወካዮች ምክር ቤት የሚወጣው የስራ አስፈፃሚውን ስልጣንና ተግባር የሚወስን አዋጅ ላይ ተዘርዝሮ ይቀመጣል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት በይፋ ከታወጀ ወዲህ የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጡ አዋጆች የሚከተሉት ናቸው፡፡ ይህ መጽሐፍ ወደ ህትመት እስከገባበት ጊዜ ድረስ ፀንተው ያሉ ህጎች አዋጅ ቁ. 916/2008 እና አዋጅ ቁ. 942/2008 (ማሻሻያ) ሲሆኑ የተቀሩት በሙሉ ተሽረዋል፡፡

የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጡ አዋጆች ዝርዝር፤

አዋጅ ቁ. 4/1987

አዋጅ ቁ. 93/1990 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 134/1991 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 256/1994

አዋጅ ቁ. 380/1996 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 411/1996 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 465/1997 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 471/1998

አዋጅ ቁ. 546/1999 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 603/2001 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 641/2001 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 642/2001 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 691/2003

አዋጅ ቁ. 723/2004 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 803/2005 (ማሻሻያ)

አዋጅ ቁ. 916/2008

አዋጅ ቁ. 942/2008 (ማሻሻያ)

የሌሎች የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ስልጣን ደግሞ የተወካዮች ምክር ቤት በሚያወጣው አዋጅ እንዲሁም ከ2002 ዓ.ም. ጀምሮ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብa በግልጽ ወይም በተዘዋዋሪ ተደንግጐ ይገኛል፡፡ እነዚህ በየጊዜው የሚወጡ ማቋቋሚያና ሌሎች ተጓዳኝ ህጐች የአስተዳደሩ የስልጣን ምንጭ በመሆን ያገለግላሉ፡፡

ስለሆነም የአስተዳደር መ/ቤቶችን የስልጣን ገደብ ለመወሰን የተወካዮች ም/ቤት ያወጣውን አዋጅ ብቻ ሳይሆን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንቦችን ማመሳከር ያስፈልጋል፡፡ ከሁለቱ ህጎች ውጭ ከልማድ፣ ከመመሪያ ወይም ከሌላ የስልጣን ምንጭ በማንኛውም የአስተዳደር መ/ቤት የተፈጸመ ድርጊት፣ የተሰጠ ውሳኔ፣ የወጣ መመሪያ ወይም ደንብ ከስልጣን በላይ እንደ መሆኑ ህጋዊነት ኖሮት በህግ ፊት ሊፀና ሆነ ውጤት ሊኖረው አይችልም፡፡ በህግና በህጉ መሰረት መሰረት ብቻ መስራት የህግ የበላይነት የቆመበት ምሶሶ እንደመሆኑ የህዝብ ወይም የመንግስት አስተዳደር ሊከናወን የሚገባው ከህግ በመነጨ ስልጣን መሰረት ብቻ ነው፡፡

The UN Human Rights Commissioner is warning that reports of mass killings in Ethiopia, would, if verified, amount to war crimes.


The UN Human Rights Commissioner is warning that reports of mass killings in Ethiopia, would, if verified, amount to war crimes.

This comes after Amnesty International reported that scores of civilians had been killed in a town in Tigray state.

Speaking in Geneva, Michelle Bachelet called for a full investigation and said those responsible must be held accountable.

The authorities in Tigray have denied eyewitness reports that Tigrayan forces carried out the killings.

Ms Bachelet said the first priority must be ending the fighting. The UN fears the conflict could spiral out of control and even spread across Ethiopia’s borders.

Thousands of people are already fleeing the fighting into neighbouring Sudan.

The UN refugee agency said many are children who are arriving exhausted and ter

BBC

The international community and all Ethiopians should realize that this is a lie that Prime Minister Abiy Ahmed is talking about. The reason why Prime Minister Abiy Ahmed fought for Tigray is because the TPLF party does not accept the prosperity of the Tigray government. Share it with all of you.


The international community and all Ethiopians should realize that this is a lie that Prime Minister Abiy Ahmed is talking about. The reason why Prime Minister Abiy Ahmed fought for Tigray is because the TPLF party does not accept the prosperity of the Tigray government. It should be made clear that the people of Tigray have not given up their rights in accordance with the constitution. The international community must understand that Abiy Ahmed’s statement is completely untrue. It should also be noted that Prime Minister Abiy Ahmed is launching a defamation and defamation campaign against the TPLF. According to the Ethiopian constitution, states have the right to self-government. In this regard, the TPLF has the right to govern the people of Tigray. After the TPLF government decided not to hold the elections on time in accordance with the constitution, Abiy Ahmed decided to extend the term of his term. We cannot overthrow the constitution. We have to hold elections in accordance with the constitution !! Dr. Abby says we will not hold an election. He then decided that the country should be governed by a non-elected transitional government, and that Abiy Ahmed would not hold elections without the consent of the people and the rights of the people. Tigray does not accept this illegal act, saying that our rights should be respected in accordance with the constitution. They objected, saying that they would not accept a decision that was not in line with the law. He threatened other ethnic groups and continued to arrest and kill them. Abiy Ahmed has declared war on the people of Tigray, citing various false reasons just because the people of Tigray have said they will not give up their rights. This is the reality of the war and the cause of the war on the ground! Dr. Abiy Ahmed we will not hold an election. He then decided that the country should be governed by a non-elected transitional government, and that Abiy Ahmed would not hold elections without the consent of the people and the rights of the people. Tigray does not accept this illegal act, saying that our rights should be respected in accordance with the constitution. They objected, saying that they would not accept a decision that was not in line with the law. He threatened other ethnic groups and continued to arrest and kill them. Abiy Ahmed has declared war on the people of Tigray, citing various false reasons just because the people of Tigray have said they will not give up their rights. This is the reality of the war and the cause of the war on the ground! Share it with all of you.

የሕገመንግስቱ አንቀጽ 50


የሕገመንግስቱ ንቀጽ 50፡ ስለ ሥልጣን አካላት አወቃቀር

⚖️—–የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብ ሊክ በፌዴራል መንግሥትና በክልሎች የተዋቀረ ነው።

⚖️——የፌዴራሉ መንግሥትና ክልሎች የሕግ አውጪነት፣ የሕግ አስፈጻሚነትና የዳኝነት ሥልጣን አላቸው።

⚖️——–የፌዴራሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥልጣን አካል የፌዴራሉ መንግሥት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው። ተጠሪነቱየአንቀጽገሪቱ ሕዝብ ነው።

⚖️—–የክልል ከፍተኛ የሥልጣን አካል የክልሉ ምክር ቤት ነው፣ ተጠሪነቱም ለወከለው ክልል ሕዝብ ነው። ክልሎች፣ በክልልነትና ክልሎች አስፈላጊ ሆነው በሚያገኙአቸው የአስተዳደር እርከኖች ይዋቀራሉ። ሕዝቡ በዝቅተኛ የአስተዳደር እርከኖች በቀጥታ ይሳተፍ ዘንድ ለዝቅተኛ እርከኖች በቂ ሥልጣን ይሰጣል።

⚖️——–የክልል ምክር ቤት በክልሉ ሥልጣን ስር በሆኑ ጉዳዮች የክልሉ የሕግ አውጪ አካል ነው። ይህንን ሕገ መንግሥት መሰረት በማድረግ የክልሉን ሕገ መንግሥት ያዘጋጃል፣ ያጸድቃል፣ ያሻሽላል።

⚖️——– የክልል መስተዳድር የክልሉ ከፍተኛ የሕግ አስፈጻሚ አካል ነው።

⚖️⚖️⚖️——– የክልል የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ብቻ ነው።

⚖️⚖️⚖️ የፌዴራሉ መንግሥትና የክልሎች ሥልጣን በዚህ ሕገ መንግሥት ተወስኗል።

⚖️⚖️⚖️ለፌዴራሉ መንግሥት የተሰጠው ሥልጣን በክልሎች መከበር አለበት፡፤

ለክልሎች የተሰጠው ሥልጣን በፌዴራሉ መንግሥት መከበር አለበት።

⚖️⚖️ የፌዴራል መንግሥት በዚህ ሕገ መንግ ሥት አንቀጽ ፶1 ከተሰጡት ሥልጣን እና ተግባሮች እንደአስፈላጊነቱ ለክልሎች በውክልና ሊሰጥ ይችላል።

The witness was not very pleased with the judge’s decision. And the judge twisted the question a little bit, giving the judge a ‘twist’. እስቲ ዛሬ በዚህ የፍርድ ቤት የችሎት ቀልድ ሁላችሁም ተዝናኑልኝ!


The witness was not very pleased with the judge’s decision. And the judge twisted the question a little bit, giving the judge a ‘twist’.

Judge —— “What is your name?”

Witness —— “They call me Mamush and Mamushet”

Judge —— “How old are you?”

Witness —— “I Will Be Forty-Fifty”

Judge —— “Where do you live?”

Witness —— “Here and There”

Judge —— “What are you doing?”

Witness —— “This and That” The Honorable Judge’s patience was running out.

“Submit it!” They gave orders. The witness was shocked to learn that he would be imprisoned with his own tongue

Witness — “Wait! When will leave? ” He asked.

Judge —— “Sooner or later!”

THE CONSTITUTION OF ETHIOPIA


The Constitution of Ethiopia


The so-called “Ethiopian constitution” is the “constitution of the people” of Ethiopia. I believe it is necessary to make a law that can accommodate the tribes, and if it is necessary to make it possible for the people to come to power, it will be possible for the people to come to power, and for the people to come to power.

Because in order for the law to prevail and to be enforced, it must be upheld by all legislators, leaders and students. Human Rights Since every citizen has his or her rights and freedoms, his or her rights and freedoms must not be violated in any way that causes harm to his or her body or life.

To this end, we will do our part to fulfill the obligation and protect the rights of all citizens, and we will do our part to save the looming disintegration issue that is looming in our country.

➢➢➢➢➢➢➢History➢➢➢➢➢➢➢➢

1) The 1931 Constitution of Haile Selassie

-It is the first modern constitution of Ethiopia.

-Justice is a constitution that came to replace kings.

– The advent of the constitution was first announced at a great party on July 16, 1931, during Haile Selassie’s reign.

It has 7 chapters and 55 sub-chapters.

Chapter 1: The Conditions of Transfer of Power About Heirs

Chapter 2: The Power of Haile Selassie

Chapter 3: Obligations and Rights Recognized by the Trinity

Chapter 4 – The Ethiopian Parliament

Chapter 5 – About Ministries

Chapter 7 – Work Budgeting

-This constitution has been in place for 26 years.

2) The 1955 Haile Selassie Constitution

– In November 1955, Emperor Haile Selassie proclaimed a new amended constitution.

Why the 1931 Constitution was amended:

1st to improve relations with the international community

2nd because of the need for a new law regarding Eritrea

-The Constitution has 8 chapters and 131 sub-chapters.

-This constitution was repealed in 1974 by the Derg.

– After the overthrow of Haile Selassie’s government in 1974, the Derg remained in power for 11 years without a constitution.

-The ensuing Derg constitution served for four years.

3) The 1987 Constitution

-This is Ethiopia’s third constitution.

– Used on February 22, 1987, and was written as a result of the February 1 referendum.

– After the formation of the Labor Party in 1984, its first task was to establish a new constitution that could govern the new national and the Ethiopian People’s Federal Democratic Republic.

-The 1987 Constitution had 17 chapters and 119 sub-chapters. 4) The 1995 Constitution

-Ethiopia is the current constitution.

-This Constitution is the supreme constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia.

-The constitution was drafted by a drafting committee elected in 1994.

It was inaugurated in December 1994 by the Transitional Federal Government of Ethiopia.

– Approved following the May-June 1995 general election.

-The constitution has 11 chapters and 106 articles.


የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት’ የሚለው

የኢትዮጵያ “ሕገ ሕዝብ” ተብሎ ቢጠራ መንግስት እሚለውን በሕዝብ በመተካት አመሰራረቱ አሁን ባለው ተኮርጆ የተጻፈ ከምእራባውያን የተቀዳ በተግባር የማይፈጸም በመሆኑ፡ ለወደፊቱ የሀገሪቱ መመርያ ከሕዝቡ የወጣ ከያንዳንዱ ግዛት ከምክትል ወረዳ ጀምሮ እስከ ክፍለ ሀገር፡ ያለባቸውን ችግርና መፍትሔ የሚመሩበት ሕግ በማውጣት፡ ባጠቃላይ ሁሉንም ጎሳዎች ሊያስተናግድ የሚችል ሕግ በመቅረጽ፡ በሁሉም ሕዝቦች ድምጽ የጸደቀ፡ የማይሻር ከስልጣን የሚቀመጡት የማይቀየር የማሻሻያና፡ በሕዝብ ሸንጎ የሚፈጸም እንዲሆን ቢደረግ አስፈላጊ ብዮ አምንበታለሁኝ፡፤
ምክንያቱም ሕግ የሁሉም በላይ ሆኖ ሁሉንም እንዲያስተናግድ ተፈጻሚነትም እንዲያገኝ የሕግ አውጮችና መሪና ተመሪዎችን ቤኩል ማስተናገድ ሁሉም ተገዥዎች መሆን ገባቸዋል፡ የሰው ልጅ መብት በፍጹም መደፈርና በሕግ ስም መደርመስ አይገባውም ይህ ከተፈጥሮ የተሰጠው በመሆኑ መጠበቅ ይኖርበታል። ሰብዓዊ መብት ማንኛውም ዜጋ መብቱና ነፃነቱን የማይነጠቅ አሳልፎም የማይሰጥ በመሆንኑ፡ በማንኛውም መንገድ በሰውነቱ በሕይወቱ ጉዳት ቁስልና ጠባሳ የሚያደርስ ጥሰት እንዳይገኘው፡ በስልጣን ያለው የስራዓቱ አገልጋዮች እንዳይደርስበት ደሕንነቱ ነፃነትና መብቱ መጠበቅ ግዴታ አለባቸው።
ለዚህም ሁሉም ዜጎች ግዴታቸውን ለመፈጸምና መብታቸውን ለማስጠበቅ በዚህ ጉዳይ በመግባት ይጠቅማል ብለን የምናስበውን የየበኩላችን አስተዋጻኦ በማድረግ በሀገራችን እያንዣበበ ያለውን የማፍረስ የሕዝቦች መነጣተል ጉዳይ ለመታደግ ያስችላል።

ታሪክ

1) የ1931 የሀይለስላሴ ህገ-መንግስት

-የመጀመሪያ የኢትዮጵያ ዘመናዊ ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ፍትሀ ነገስትን ለመተካት የመጣ ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ህገ-መንግስቱ መምጣቱ ለመጀመሪያ የታወጀው በሀይለስላሴ ጊዜ በ ሀምሌ 16/ 1931 ዓ.ም የተካሄደ ታላቅ ድግስ ላይ ነው፡፡

-7 ምዕራፍና 55 ንዑስ ምዕራፍ አሉት፡፡

1ኛ ምዕራፍ- ስለ ስልጣን ርክክብ ሁኔታዎች ስለ አልጋ ወራሾች

2ኛ ምዕራፍ- የሀይለስላሴ ስልጣን

3ኛ ምዕራፍ- ስለግዴታዎች እና በሀይለስላሴ እውቅና
ስለተሰጣቸው መብቶች

4ኛ ምዕራፍ- ስለ ኢትዮጵያ ፓርላማ

5ኛ ምዕራፍ- ስለ ሚኒስቴሮች

7ኛ ምዕራፍ- ስራ በጀት አወጣጥ

-ይህ ሕገ-መንግስት ለ26 አመታት አገልግሏል፡፡

2) የ1955 የሀይለስላሴ ህገ-መንግስት

-እ.ኤ.አ በህዳር 1955 አፄ ሀይለስላሴ አዲስ የተሻሻለ ህገ-መንግስት አወጀ፡፡

-የ1931 ህገ-መንግስት የተሻሻለበት ምክንያት፦

1ኛ ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማሻሻል

2ኛ ኤርትራን በተመለከተ አዲስ ህግ በማስፈለጉ ምክንያት ነው

-ህገ-መንግሰቱ 8 ምዕራፍና 131 ንዑስ ምዕራፎች አሉት፡፡

-ይህ ህገ-መንግስት በ1974 ደርግ ሲገባ ተሽሯል፡፡

-በ1974 የሀይለስላሴ መንግስት ከተሻረ እና ደርግ ከገባ በኃላ ደርግ ለ11 ዓመት ያህል ያለ ህገ-መንግስት በስልጣን ላይ ነበር፡፡

-ከዚያ በኃላ የወጣው የደርግ ህገ-መንግስት ለአራት አመታት ያህል አገልግሏል፡፡

3) የ1987 ህገ-መንግስት

-ይህ የኢትዮጵያ ሶስተኛ ህገመንግስት ነው፡፡

-ጥቅም ላይ መዋል የጀመረው የካቲት 22 1987 ዓ.ም ሲሆን የተፃፋው በየካቲት 1 በተደረገ ህዝበ-ውሳኔ የተነሳ ነው፡፡

-የሰራተኛ ፓርቲ በ1984 ከተመሰረተ በኃላ አንደኛ ቀዳሚ ስራ ተግባሩ አዲሱን ብሔራዊ እና የኢትዮጵያን ህዝባዊ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሊመራ የሚችል ህገ-መንግስት መመስረት ነበር፡፡

-የ1987 ህገ-መንግስት 17 ምዕራፍ እና 119 ንዑስ ምዕራፎች ነበሩት 4) የ1995 ህገ-መንግስት

-ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ እየተገለገለባቸው ያለው ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ይህ ህገ-መንግስት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የበላይ ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ህገ-መንግስት የተራቀቀው በ1994 በተመረጠው አርቃቂ ኮሚቴ ነው፡፡

-በስራ ላይ የዋለው በኢትዮጵያ የሽግግር መንግስት በታህሳስ 1994 ነው፡፡

-የፀደቀው ከግንቦት-ሰኔ 1995 ባለው ጊዜ በተካሄደው ከአጠቃለይ የመንግስት ምርጫ ተከትሎ ነው፡፡

-ህገ-መንግስቱ 11 ምዕራፍና 106 አንቀፆች አሉት፡፡

ጥንታዊ ሕገ መንግስት

ፍትሐ ነገሥት ይዩ

ዘመናዊ ሕገ መንግስት

ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ፲፱፻፳፫ ዓመተ ምኅረት በቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ ፲፱፻፵፰ ዓ.ም. ካገለገለ በኋላ በዚያ ዓመት የንጉሠ ነገሥቱ ኢዮቤልዩ የዘውድ በዓል በሚከበረበት ዕለት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት አብዮት እስከፈነዳበት ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ድረስ በአገልግሎት ላይ ከዋለ በኋላ በደርግ ውሳኔ፣ ሕገ መንግሥታዊ ባልሆነ ሂደት ተሰረዘ።

የቁጥጥር ስልቶች


የቁጥጥር ስልቶች
ፓርላማ ስራ አስፈፃሚውንና በስሩ ያሉትን የአስተዳደር አካላት የሚቆጣጠርበትና የሚከታተልበት መንገድና ስርዓት የተለያየ መልክ ይይዛል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት የተለያዩ የቁጥጥር ስርዓቶችን ጠቅለል ባለ መልኩ ያስቀመጠ ሲሆን ዝርዝር አፈፃፀሙ በተለያዩ ህጎችና የተወካዮች ምክር ቤት የውስጥ ደንቦች ተደንግጎ ይገኛል፡፡
እስከ 1994 ዓ.ም ድረስ ምክር ቤቱ ህገ መንግስታዊ ሚናውን በህግ አውጪነት ብቻ ገድቦታል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1988 ዓ.ም ያወጣው የህግ አወጣጥ ስነ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 14/1988 ሆነ ይህንኑ አዋጅ ያሻሻለው አዋጅ ቁ. 33/1988 የህግ አወጣጥን ብቻ ከሚመለከቱት ጥቂት ያልተብራሩ ድንጋጌዎች በስተቀር ስለ ቁጥጥር ስርዓት የሚሉት ነገር የላቸውም፡፡
አዋጅ ቁ. 14 እና ማሻሻያውን አዋጅ ቁ. 33/1998 ‘ን’ የሻረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ስነ-ስርዓት፣ የኮሚቴዎች አደረጃጀትና አሠራር አዋጅ ቁ. 271/1994 ምክር ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አስፈፃሚውን መቆጣጠር ህገ መንግስታዊ ሚናው መሆኑን የተረዳበት ተግባራዊ ጅማሮ ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡ በቀጣይ በ1997 ዓ.ም የወጣውና አዋጅ ቁ. 272/1994 ‘ን’ የተካው የተሻሻለው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ተወካዮች ምክር ቤት የአሠራርና የስነ ምግባር አዋጅ ቁ. 470/1997 ምክር ቤቱ ስር አስፈፃሚውን የሚቆጣጠርበትን ስርዓት በዝርዝርና በተብራራ መልኩ በመደንገግ ምክር ቤት ህገ መንግስታዊ ግዴታውን እንዲወጣ ውጤታማ የህግ ማዕቀፍ ዘርግቷል፡፡ ይህ አዋጅ ከአንድ ዓመት ላልበለጠ ጊዜ ስራ ላይ ሳይቆይ በአዋጅ ቁ. 503/1998 ሙሉ በሙሉ ተሸሯል፡፡ በአዋጁ መግቢያ ላይ እንደተመለከተው ምክር ቤቱ የህግ አወጣጡንና አሰራሩን በራሱ ደንብ መወሰን አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘው አዋጁን መሻር አስፈልጓል፡፡
በዚሁ መሰረት አሰራሩንና የህግ አወጣጥ ስርዓቱን በራሱ ውስጠ ደንብ የተካው ሲሆን ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ ተፈጻሚነት ያገኘውና ተሻሽሎ የወጣው የአሰራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁ. 6/2008 በቁጥጥር ስርዓቱ ላይ አዳዲስ አካሄዶችን በማካተት ለተግባራዊ የቁጥጥር ስርዓት መኖር አመቺ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚውን የመቆጣጠር ስልጣኑ ከህግ መንግስቱ አንቀጽ 55 /7/፣ /11/፣ /13/፣/17/ እና /18/ እና 77/2/ ይመነጫል፡፡ የስራ አስፈፃሚውን የተጠያቂነት መርህ የሚወስነው የህገ መንግስቱ አንቀጽ 77/2/ ጠቅላይ ሚኒስትሩና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ እንደሆኑ ይደነግጋል፡፡ የተጠሪነት መርህ ስራ አስፈፃሚው ለድርጊቱ፣ ውሳኔውና እርምጃው ፖለቲካዊ ተገቢነትና ህገ መንግስታዊነት ለህግ አውጭው መግለጫና ማብራሪያ እንዲሰጥና ለውድቀቶቹ ኃላፊነት እንዲሸከም ያስገድዳል፡፡ ይህንን በሚያጠናክር መልኩ የአንቀጽ 55/17/ ድንጋጌ የተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩንና ሌሎች የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ለጥያቄ የመጥራትና የህግ አስፈፃሚውን አካል አሰራር የመመርመር ስልጣን አጎናጽፎታል፡፡
በአንቀጽ 55/7/ ላይ የተመለከተው የመከላከያ፣ የፀጥታ ኃይሎችና የፖሊስ አደረጃጀት የመወሰን እንዲሁም ሰብዓዊ መብት የመጣስ ተግባራት ሲፈጸሙ አጣርቶ እርምጃ የመውሰድ ስልጣን በእርግጥ በተግባር ስራ ላይ ከዋለ የዜጎችን ህገ መንግስታዊ መብት ውጤታማ በሆነ መንገድ ያስጠብቃል፡፡ በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 11 እና 13 የተመለከቱት በጀት የማጽደቅ እንዲሁም የዳኞችና የከፍተኛ ባለስልጣናትን ሹመት የማጽደቅ ስልጣን ቀጥተኛ የስልጣን መቆጣጠሪያ መንገድ ባይሆንም ከሌሎች የቁጥጥርና የክትትል መንገዶች ጋር ተዳምሮ ህግ አውጭው በተግባር ሊጠቀምበት የሚችል ውጤታማ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልት ነው፡፡
የቁጥጥር ስልቶች
ፓርላማ ስራ አስፈፃሚውንና በስሩ ያሉትን የአስተዳደር አካላት የሚቆጣጠርበትና የሚከታተልበት መንገድና ስርዓት የተለያየ መልክ ይይዛል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት የተለያዩ የቁጥጥር ስርዓቶችን ጠቅለል ባለ መልኩ ያስቀመጠ ሲሆን ዝርዝር አፈፃፀሙ በተለያዩ ህጎችና የተወካዮች ምክር ቤት የውስጥ ደንቦች ተደንግጎ ይገኛል፡፡
እስከ 1994 ዓ.ም ድረስ ምክር ቤቱ ህገ መንግስታዊ ሚናውን በህግ አውጪነት ብቻ ገድቦታል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1988 ዓ.ም ያወጣው የህግ አወጣጥ ስነ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 14/1988 ሆነ ይህንኑ አዋጅ ያሻሻለው አዋጅ ቁ. 33/1988 የህግ አወጣጥን ብቻ ከሚመለከቱት ጥቂት ያልተብራሩ ድንጋጌዎች በስተቀር ስለ ቁጥጥር ስርዓት የሚሉት ነገር የላቸውም፡፡
አዋጅ ቁ. 14 እና ማሻሻያውን አዋጅ ቁ. 33/1998 ‘ን’ የሻረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ስነ-ስርዓት፣ የኮሚቴዎች አደረጃጀትና አሠራር አዋጅ ቁ. 271/1994 ምክር ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አስፈፃሚውን መቆጣጠር ህገ መንግስታዊ ሚናው መሆኑን የተረዳበት ተግባራዊ ጅማሮ ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡ በቀጣይ በ1997 ዓ.ም የወጣውና አዋጅ ቁ. 272/1994 ‘ን’ የተካው የተሻሻለው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ተወካዮች ምክር ቤት የአሠራርና የስነ ምግባር አዋጅ ቁ. 470/1997 ምክር ቤቱ ስር አስፈፃሚውን የሚቆጣጠርበትን ስርዓት በዝርዝርና በተብራራ መልኩ በመደንገግ ምክር ቤት ህገ መንግስታዊ ግዴታውን እንዲወጣ ውጤታማ የህግ ማዕቀፍ ዘርግቷል፡፡ ይህ አዋጅ ከአንድ ዓመት ላልበለጠ ጊዜ ስራ ላይ ሳይቆይ በአዋጅ ቁ. 503/1998 ሙሉ በሙሉ ተሸሯል፡፡ በአዋጁ መግቢያ ላይ እንደተመለከተው ምክር ቤቱ የህግ አወጣጡንና አሰራሩን በራሱ ደንብ መወሰን አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘው አዋጁን መሻር አስፈልጓል፡፡
በዚሁ መሰረት አሰራሩንና የህግ አወጣጥ ስርዓቱን በራሱ ውስጠ ደንብ የተካው ሲሆን ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ ተፈጻሚነት ያገኘውና ተሻሽሎ የወጣው የአሰራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁ. 6/2008 በቁጥጥር ስርዓቱ ላይ አዳዲስ አካሄዶችን በማካተት ለተግባራዊ የቁጥጥር ስርዓት መኖር አመቺ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚውን የመቆጣጠር ስልጣኑ ከህግ መንግስቱ አንቀጽ 55 /7/፣ /11/፣ /13/፣/17/ እና /18/ እና 77/2/ ይመነጫል፡፡ የስራ አስፈፃሚውን የተጠያቂነት መርህ የሚወስነው የህገ መንግስቱ አንቀጽ 77/2/ ጠቅላይ ሚኒስትሩና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ እንደሆኑ ይደነግጋል፡፡ የተጠሪነት መርህ ስራ አስፈፃሚው ለድርጊቱ፣ ውሳኔውና እርምጃው ፖለቲካዊ ተገቢነትና ህገ መንግስታዊነት ለህግ አውጭው መግለጫና ማብራሪያ እንዲሰጥና ለውድቀቶቹ ኃላፊነት እንዲሸከም ያስገድዳል፡፡ ይህንን በሚያጠናክር መልኩ የአንቀጽ 55/17/ ድንጋጌ የተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩንና ሌሎች የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ለጥያቄ የመጥራትና የህግ አስፈፃሚውን አካል አሰራር የመመርመር ስልጣን አጎናጽፎታል፡፡
በአንቀጽ 55/7/ ላይ የተመለከተው የመከላከያ፣ የፀጥታ ኃይሎችና የፖሊስ አደረጃጀት የመወሰን እንዲሁም ሰብዓዊ መብት የመጣስ ተግባራት ሲፈጸሙ አጣርቶ እርምጃ የመውሰድ ስልጣን በእርግጥ በተግባር ስራ ላይ ከዋለ የዜጎችን ህገ መንግስታዊ መብት ውጤታማ በሆነ መንገድ ያስጠብቃል፡፡ በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 11 እና 13 የተመለከቱት በጀት የማጽደቅ እንዲሁም የዳኞችና የከፍተኛ ባለስልጣናትን ሹመት የማጽደቅ ስልጣን ቀጥተኛ የስልጣን መቆጣጠሪያ መንገድ ባይሆንም ከሌሎች የቁጥጥርና የክትትል መንገዶች ጋር ተዳምሮ ህግ አውጭው በተግባር ሊጠቀምበት የሚችል ውጤታማ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልት ነው፡፡

የአስተዳደር ህግ ውልደትና ዕድገት በኢትዮጵያ


የአስተዳደር ህግ ውልደትና ዕድገት በኢትዮጵያ

ስለ ኢትዮጵያ የአስተዳደር ህግ ብሎም ውልደቱ፣ አነሳሱና ታሪካዊ ዕድገቱ ለመጻፍ ብዕሩን የሚያሾል ጸሐፊ ጭብጥ እንዳጣ የልብለወለድ ደራሲ ከየት ልጀምር? በሚል ጭንቀት ተውጦ ጣራ ላይ ማፍጠጥ አይቀርለትም፡፡ ስራውን ፈታኝ የሚያደርገው በህዝብ አስተዳደር እና በአስተዳደር ህግ ላይ የተጻፉ የታሪክ መዛግብት፣ የምርምር ጽሑፎችና መጻህፍት አለመኖር ብቻ አይደለም፡፡ በእርግጥ ለጀማሪ አጥኚ ይህ በራሱ ራስ ምታት ነው፡፡ ከመነሻ ምንጭ እጥረት ባሻገር ሌሎች ዐቢይ ምክንያቶች የአገሪቱን የአስተዳደር ህግ ጉዞ መዘገብ አድካሚ ያደርጉታል፡፡ ለመጥቀስ ያህል፤

የጥናት አድማሱ ወጥነት እና ትኩረት ማጣት።

የዲሞክራሲና ህገ መንግስታዊ ዳራው።

የፖለቲካና አስተዳደር መደበላለቅ።

የህግ አውጭውና የፍርድ ቤቶች ሚና ማነ

ባደጉት አገራት የአስተዳደር ህግ ዕድገት ጥርት ባለ መልኩ ራሱን የቻለ የህግ ክፍል ሆኖ ብቅ ማለት የጀመረው የዘመናው ‘የአስተዳደር መንግስት’ (Administrative State) መከሰት ተከትሎ ስለመሆኑ ብዙዎች የመስኩ አጥኚዎች ይስማሙበታል፡፡ በተመሳሳይ ቅኝት ስለ አገራችን አስተዳደር ህግ ታሪካዊ ገጽታዎችና መገለጫዎች ከዘመናዊ አስተዳደር ማቆጥቆጥ ጋር አስታኮ አጠቃላይ ገለጻ መስጠት ይቻላል፡፡

በርካታ የአገራችን ሆኑ የውጭ አገር ታሪክ ጸሐፊዎች በአገራን ዘመናዊ አስተዳደር የተተከለው የኃይለስላሴ ዙፋን ላይ መውጣት ተከትሎ በነበሩት ዓመታት ውስጥ እንደሆነ ይስማሙበታል፡፡ በተለይም ከኢጣሊያ ወረራ ማብቃትና የንጉሱ ዙፋን መልሶ መረከብ አንስቶ ዘመናዊ አስተዳደር ፈጣን ለውጦች አሳይቷል፡፡

ስለ ኢትዮጵያ የመንግስት አስተዳደር ሲወራ የአጼ ቴዎድሮስ ውጥን እና ጥረት ሳይጠቀስ አይታለፍም፡፡ አጼ ቴዎድሮስ ብሔራዊ ጦር ለማደራጀት፣ የቤተክስርስትያን የመሬት ይዞታ ለመቆጣጠር፣ የአካባቢ የጦር አበጋዞች በማዕከላዊ መንግስት ስር ለማዋቀር እንዲሁም የመንገድ ግንባታና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ለመዘርጋት ያደረጓቸው ጥረቶች ለቀጣይ ነገስታት መሰረት ጥለዋል፡፡ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግስት ለማቆም እና ዘመናዊ አስተዳደር ለመትከል የነበራቸው ህልም፣ ውጥን እና ፖሊሲ እንዲሁም እነዚህን ለመተግበር የወሰዷቸው ስር ነቀል እርምጃዎች የለውጥና የስልጣኔ በር ከፍተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የአስተዳደር ህግ ውልደት ከቴዎድሮስ ይጀምራል፡፡ አስተዳደራዊ ብልሹነት እንዲቀረፍና ሹመኞች በህዝብ አገልጋይነታቸው በደል እንዳይፈጽሙ በጊዜው ሲያደርጉት የነበረው ክትትል እና የስልጣን ቁጥጥር በኢትዮጵያ የታሪክ መጻህፍት ጎልቶ ባይወጣም በአንዳንድ ጽሁፎች ተዘግቦ ይገኛል፡፡ በደርግ ወታደራዊ መንግስት ልዩ ፍርድ ቤት ይዘጋጅ የነበረው ሕግና ፍትሕ መጽሔት በመጋቢት 1987 እትሙ አጼ ቴዎድሮስ ሙስና እና የአስተዳደር ብልሹነት እንዲወገድ ሲያደርጉት የነበረውን ተጋድሎ ሌላ ምንጭ ጠቅሶ እንደሚከተለው ዘግቦታል፡፡e

ቴዎድሮስ ወዘልውጥ በመሆንና አልባሌ ልብስ በመልበስ በመንግስቱ ውስጥ ያለው የአስተዳደር መበላሸት መቆጣጠር፣ ጉቦኞች ሹማምንቶቻቸውን መከታተልና ማጋለጥ ያዘውትሩ ነበር፡፡ በሕዝብ ችግር የጨከኑትን፣ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የመንግስቱን ስራ የሚበድሉትንና ኅብረተሰቡን ያጉላሉትን ሹማምንት ከስልጣን ወንበራቸው ገልብጠዋል፡፡ አባ ታጠቅ ስልጣን በጨበጡ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ውስጥ የጯሂ ጠባቂ (የህዝብ ዕንባ ጠባቂ) ሹማቸው ጉቦ መቀበሉን በማወቃቸውና ራሳቸውም ሲቀበል በማየታቸው በአደባባይ አጋልጠው ሽረውታል፡፡…የጯሂ ጠባቂነቱንም ሥራ ራሳቸው ይዘዋል፡፡

አጼ ቴዎድሮስ የመንግስት ስልጣን በህግና በስርዓት እንዲገራ የነበራቸው ቆራጥ አቋም በታሪክ በተዘገቡ ጥቂት የጊዜው ፍርዶች ላይ ይታያል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንደኛው በጳውሎስ ኞኞ ‘አጤ ቴዎድሮስ’ መጽሐፍ ላይ እንደሚከተለው ተዘግቧል፡፡

ቴዎድሮስ ጋይንት ላይ ሰፍረው ሳለ ወታደሮቻቸውን በባላገሩ ላይ ተሰሪ አስገቡ፡፡ ባላገሩ እንዲቀልብ በየቤቱ ማስገባት ማለት ነው፡፡ ተሰሪ ከገቡት ወታደሮች መሀል አንዱ ወታደር አንዱን ባላገር ገደለው፡፡ የሟች ወገንም ከቴዎድሮስ ዘንድ መጥቶ አመለከተ፡፡ ቴዎድሮስም ወታደራቸውን ሁሉ አፈርሳታ አስቀምጠው ገዳዩን አውጣ ብለው ያዙ፡፡ ወታደሩም በመላው አድሞ ገዳዩን አላየንም እያለ በቄስ እየተገዘተ ወጣ፡፡ የሟች ገዳይ ወታደር በመጥፋቱ ቴዎድሮስ ተናደው ‘ወታደር ብላ፤ ባላገር አብላ ያልሁ እኔ ነኝ፡፡ ደመኛህም እኔ ነኝና እኔን ግደል’ ብለው ብለው ተነስተው ለከሳሹ ነገሩት፡፡ ከሳሹም ‘እኔ ንጉስ መግደል አይቻለኝም’ አለ፡፡ ቴዎድሮስም ደም በከንቱ አይቀርም ብለው ለሟቹ ወገን የደም ገንዘብ ዋጋ ሰጥተው ሸኙት፡፡f

በሌላ ፍርድ ላይ እንዲሁ ለሁለት ወታደሮቻቸው የሰጡት እርስ በርሱ የሚጋጭ ትዕዛዝ የአንደኛውን ወታደር ሞት በማስከተሉ ለሞቱ መከሰት ተጠያቂ ተደርገው ስለተፈረደባቸው በዚያ ንጉስ በማይከሰስበት፤ ሰማይ በማይታረስበት ዘመን ቅጣታቸውን ተቀብለው ፍርዱን ፈጽመዋል፡፡ ታሪኩ በአጭሩ እንደዚህ ነው፡፡

ቴዎድሮስ አንዱን ወታደራቸውን ‘በፍርቃ በር በኩል እርጉዝ ሴት እንኳን ብትሆን እንዳታልፍ ጠንክረህ ጠብቅ’ ብለው ካዘዙት በኋላ በሌላ ቀን ደግሞ ሌላውን ወታደር ጠርተው ‘ፈረስ እያለዋወጥህ ይህን ወረቀት የጁ ሰጥተህ በአስቸኳይ በስድስት ቀን ውስጥ ተመልሰህ እንድትመጣ’ ብለው ሲልኩት እየጋለበ ሄዶ ፍርቃ በር ላይ ሲደርስ ጠብቅ ከተባለው ወታደር ጋር ‘አልፋለው! አታልፍም!’ እሰጥ አገባ ገጥሙ፡፡ በግዴታ ለማለፍ መንገድ ሲጀምር ዘበኛው ተኩሶ ገደለው፡፡ የንጉስ ትዕዛዝ ሲፈጽም የነበረ የንጉስ መልዕክተኛ በዚህ መልኩ መገደሉ ያንገበገባቸው የሟች ወገኖች ገዳዩን በመክሰስ ከቴዎድሮስ ዘንድ አቀረቡት፡፡ ቴዎድሮስም ችሎት አስችለው ፍርድ እንዲፈረድ አደረጉ፡፡

በችሎት የተቀመጠው ፈራጅ ሁሉ እየተነሳ ገዳዩን ‘በደለኛ ነህ እምቢ አልፋለው ቢልህስ ለንጉስ ታሰማ ነበር እንጂ ራስህ ፈርደህ እንዴት የንጉስ መልዕክተኛ ትገድላለህ? አሁንም ስትሞት ይታየናል’ እያሉ ፈረዱ፡፡ አንደኛው ፈራጅ ግን ከተቀመጡበት ተነስተው ከሌሎቹ ፈራጆች በመለየት ሁለት ተቃራኒ ንጉሳዊ ትዕዛዝ መስጠት አግባብ ስላልሆነ ጥፋቱ የሚመለከተው ንጉሠ ነገሥቱን እንደሆ ከተናገሩ በኋላ ‘ነገር ግን እሳቸው ብርሀን ስለሆኑ ምን ይደረግ?’ በማለት የፍርድ ሀሳባቸውን አሳርገው ተቀመጡ፡፡ አጤ ቴዎድሮስም ይህን የልዩነት የፍርድ ሀሳብ አድንቀው ከተቀመጡበት ተነስተው በተከሳሹ ወታደር ቦታ ወርደው ቆሙ፡፡ በመጨረሻም ፈራጆች በፈረዱት መሰረት በጊዜው የሚከፈለውን የደም ዋጋ አጠፌታውን ብር 500 ከፍለው ጉዳዩ በስምምነት አለቀ፡፡g

የቴዎድሮስ ሞትን ተከትሎ የተነሱት ነገስታት ማለትም አጼ ዮሐንስ እና አጼ ምኒልክ በተለያየ ጊዜ በተደረጉ የውስጥና የውጭ የጦርነት ዘመቻዎች በመጠመዳቸው ዘመናዊ አስተዳደር መሰረታዊ ለውጥ አላሳየም፡፡ ሆኖም ከአድዋ ጦርነት በኋላ ማዕከላዊ መንግስት እየተጠናከረ ሲሄድ የተወሰኑ መሻሻሎች ታይዋል፡፡ በሚኒልክ ዘመነ መንግስት ዘመናዊ አስተዳደር ለመትከል ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በ1900 ዓ.ም. የሚኒስትሮች መሾም በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡ ጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም. የተሰየሙት ሚኒስትሮች የሚከተሉት ናቸው፡፡h

የፍርድ ሚኒስትር

የጦር ሚኒስትር

የጽህፈት ሚኒስትር

የአገር ግዛት ሚኒስትር

የገንዘብ ሚኒስትር እና የንግድ ሚኒስትር

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

የእርሻና መስሪያ ሚኒስትር

የግቢ ሚኒስትር

የመንግስቱን ስራ እንዲሰሩ የተደለደሉት ሚኒስትሮች ስልጣንና ተግባራቸው በዝርዝር ደንብ ተወስኖላቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እያንዳንዱ ሚኒስትር የሚያስፈጽማቸው የተለያዩ ህጎች ወጥተዋል፡፡ እነዚህ ህጎች እስከ ጣሊያን ወረራ ድረስ በአጼ ምኒልክና ሀይለስላሴ አልጋ ወራሽ በነበሩባቸው ዓመታት በግብር ብቻ ተወስኖ የነበረውን የመንግስትና የግለሰብ ግንኙነት አድማሱን አስፍተውታል፡፡ በእነዚህ ጊዜያት የመንግስት ሚና ከጠባቂነት ቀስ በቀስ ወደ የክትትልና ቁጥጥር (regulation) እና ማህበራዊ አገልግሎት አቅራቢነት ተሸጋግሯል፡፡

በቁጥጥር ረገድ በርካታ የንግድ እና የግብርና ተግባራት በቅድሚያ ከሚመለከተው ሚኒስቴር ፈቃድ እንደሚያስፈልግ በተለያዩ ህጎች ተደንግጓል፡፡ ለአብነት ያህል፤

የወፍጮ መዘውር ማቆምና መፍጨትi

ትምባሆ መዝራትና መሸጥj

አውሬ ማደን እና ዓሣ መያዝ (ማጥመድ)k

በማህበራዊ አገልግሎት አቅርቦት ትምህርት ቤት፣ ሆስፒታል፣ ቴሌፎን እና ፖስታ፣ ባቡር እና ሌሎችም ቀስ በቀስ ተስፋፍተዋል፡፡ በ1927 ዓ.ም. የጡረታ ስርዓት ለጉምሩክ ሠራተኞችና የጉምሩክ ወታደሮች (እንደ አሁኑ ፌደራል ፖሊስ ዓይነት) ተዘርግቷል፡፡ የጡረታ መውጫ ዕድሜ ለወታደሮች ሃምሳ፣ ለሠራተኞች 60 ዓመት ሲሆን ለአበል የሚያበቃው የአገልግሎት ዘመን እንደ ቅደም ተከተሉ ሃያ አምስት እና ሰላሳ ዓመት ነው፡፡l

በጊዜው የነበረው የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ከሞላ ጎደል አሁን ካለንበት ዘመን ጋር ተቀራራቢ ነበር ለማለት ይቻላል፡፡ በጊዜው የነበረው የጉምሩክ ሹማምንትና ሠራተኞች ዲሲፕሊን አፈጻጸም ለዚህ አባባል ዐቢይ ምስክር ነው፡፡

የጉምሩክ ሠራተኛ በስራው ላይ ጥፋትና የሚጎዳ ነገር ከሰራ በየክፍሉ ያሉ ሹሞች ከስራ አግደው ስራውን በሌላ ሰራተኛ ያሰራሉ፡፡ ሆኖም በራሳቸው የቅጣት እርምጃ ለመውሰድ ስልጣኑ የላቸውም፡፡ ስለ ጥፋቱ አኳኋን መግለጫ አዘጋጅተው ከበላያቸው ላለው ዳይሬክተር ያስታውቃሉ፡፡ ዳይሬክተሩ እንደ ጥፋቱ ክብደት እና ድግግሞሽ እስከ አንድ ወር ሙሉ ደመወዝ ‘ቅጣት’ ለመወሰን ስልጣን ነበረው፡፡ ሆኖም ቅጣቱ አስገዳጅ ሳይሆን የውሳኔ ሀሳብ ዓይነት ይዘት ያለው ነው፡፡ ዳይሬክተሩ የወሰነውን ቅጣት እና የጥፋቱን ሁኔታ ገልጾ ማስታወቂያ ለሠራተኛው ከሰጠው በኋላ ሠራተኛው ዋስ ጠርቶ አዲስ አበባ ለነበረው የዋናው ዲሬክተር ጽ/ቤት ይልከዋል፡፡ በመቀጠል ክርክር የሚካሄድበት ቀነ ቀጠሮ ይቆረጣል፡፡

በቀጠሮ ቀን ጥፋት የሚገኝባቸውን ሠራተኞች ሥርዓት ለማየት የተመረጡት ሹማምንት ተሰብስበው ነገሩን ከመረመሩ በኋላ ፍርድ ይሰጣሉ፡፡ የፍርዱንም ግልባጭ ለሠራተኛው ይሰጠቱታል፡፡ በፍርዱ ቅሬታ ካለው ለንግድ ሚኒስትር ይግባኝ ማሰማት ይችላል፡፡ ሚኒስትሩም ፍርዱንና ነገሩን አይቶ መርምሮ የመጨረሻ ፍርድ ይሰጣል፡፡

ይህ ስርዓት ተፈጻሚነቱ በዋናው ዳይሬክተርና ሚኒስትሩ ለተቀጠሩ የበታች ሠራተኞች ብቻ ነው፡፡ በንጉሱ አዋጅ ስራ የተቀጠሩ ሠራተኞችና ሹማምንት ጉዳይ የመጀመሪያ ደረጃ ውሳኔ የሚያገኘው በሚኒስትሩ ሲሆን ይግባኝ 

የክልል የአስተዳደር ህግ ፌደራላዊ የመንግስት


የክልል የአስተዳደር ህግ ፌደራላዊ የመንግስት
አወቃቀር የመንግስትንና የግለሰብን ግንኙነት ሁለትዮሽ ገፅታ ያላብሰዋል፡፡ በፌደራል ደረጃ በፌደራሉ መንግስትና በግለሰቡ መካከል የሚፈጠር ግንኙት ሲኖር ይኸው ተመሳሳይ ግንኙነት በክልል ደረጃ በክልሉ መንግስትና በግለሰቡ መካከል ይፈጠራል፡፡ የኢትዮጵያ የአስተዳደር ህግ ይዘት፣ ወሰንና መገለጫ ባህሪያት ከዚህ ሀሳብ ይነሳል፡፡ መንግስትና የህዝብ የአስተዳደር በፌዴራልና በክልል ደረጃ የተዋቀረ እንደመሆኑ የአገራችን የአስተዳደር ህግ የፌደራል እና የክልል አስተዳደር ህግ ድምር ውጤት ነው፡፡ ከድምሩና ከውጤቱ በፊት ግን በፌደራላዊ የመንግስት ስርዓት ውስጥ ሁለት ዓይነት የአስተዳደር ህግ የመኖሩ ጉዳይ ግልጽ መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም ክልሎች የራሳቸውን የአስተዳደር ህግ ማውጣት ይችላሉ? የሚል የስልጣን ክፍፍል ጥያቄ ሊነሳ አይገባም፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በፌደራል እና በክልል የተዋቀረ ሲሆን ሁለቱም በተመሳሳይ መልኩ ህግ አውጪ፤ አስፈፃሚና ህግ ተርጓሚ የሚባሉ የመንግስት አካላት አቅፈዋል፡፡a እነዚህ ሶስት የመንግስት አካላት በህገ-መንግስቱ ለፌደራል እና ለክልሎች በተሰጡት ስልጣናት ስር ህግ የማውጣት፤ የመተግበር እና የመተርጐም ተግባራትን ያከናውናሉ፡፡ በክልል ደረጃ ህግ አስፈፃሚው አካል የክልሉ መስተዳድር ሲሆን የክልሉ ምክር ቤት ያወጣቸውን ህጐች ይተገብራል፡፡b ስልጣንን በመገልገል የሚፈጸሙ ተግባራት አስተዳደራዊ (ለምሳሌ የምርመራ፤ የክትትል፤ ቁጥጥርና ምክር መስጠት)፣ ህጉን ለመተግበር የሚረዱ መመሪያዎችን የማውጣት እንዲሁም የአስተዳደር ውሳኔዎችንና እርምጃዎችን የመውሰድ (ለምሳሌ የንግድ ድርጅት የመዝጋት፤ የንግድ ፍቃድ የመስጠት፤ የማገድ፤ የመሰረዝ) ተግባራትን ያጠቃልላል፡፡ የክልል አስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ህጋዊነትና ፍትሐዊነት በተመለከተ የክልል ምክር ቤት እና የክልል ፍ/ቤቶች የየራሳቸውን ሚና ይጫወታሉ፡፡ ለምሳሌ የክልሉ ምክር ቤት አነስተኛ የውሳኔ እና የመመሪያ አወጣጥ ስነ-ስርዓቶችን ሊደነግግ ይችላል፡፡ ፍ/ቤቶች ደግሞ የአስተዳደራዊ ውሳኔዎችና መመሪያዎች ህጋዊነት በመመርመር መስተዳደሩ ለህግ ተገዢ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ በዚህ መልኩ የአስተዳደር ህግ በእያንዳንዱ ክልል የግድ ይፈጠራል፡፡ በአሁኑ ወቅት ያለው የፌደራል የአስተዳደር ህግ ገና በቅጡ ያልዳበረና ጥልቀት ያለው ጥናትና ምርምር ተደርጐበት ትክክለኛ ይዘቱ፤ ቅርፁ፤ መገለጫውና ወሰኑ ተለይቶ የሚታወቅ አይደለም፡፡ ከዚህ በባሰ ደግሞ በክልሎች ያለው የአስተዳደር ህግ በአግባቡ ሊጠናና ሊታወቅ ቀርቶ እስከ መኖሩ ሳይቀር ተዘንግቷል ማለት ይቻላል፡፡ በዚህ የተነሳ በፌደራሉ የአስተዳደር ህግ እና በክልል የአስተዳደር ህግ መካከል ያለው ዝምድና እና መወራረስ ራሱን የቻለ ጥናትና ምርምር ይፈልጋል፡፡ በየክልሉ ያሉትን አዋጆች፤ ደንቦች፤ መመሪያዎችና የፍ/ቤት ውሳኔዎች ብሎም የየአስተዳደር መስሪያ ቤቱ ውሳኔዎችና ሌሎች የህጉን ምንጮች ለማግኘት ካለው አዳጋችነት የተነሳ የዚህ መጽሀፍ ዋነኛ ትኩረትም የፌደራል የአስተዳደር ህግ ብቻ ነው፡፡

የአስተዳደር ህግ እና የህገ መንግስት ትስስር እና ተዛምዶ


የአስተዳደር ህግ እና የህገ መንግስት ትስስር እና ተዛምዶ

የአስተዳደር ህግ ጽንስቱ ሆነ ውልደቱ ከህገ መንግስት እንደመሆኑ ከዚህ የህግ ክፍል ጋር ብዙ ባህርያትን ይጋራል፡፡ ሁለቱም የመንግስትና የግለሰብ ግንኙነትን በሚመራው ‘የህዝብ አስተዳደር ህግ’ ተብሎ በሚጠራው የህግ ክፍል ውስጥ ይመደባሉ፡፡ አብዛኛዎቹ የአስተዳደር ህግ ጥያቄዎች በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የህገ መንግስታዊነት ጥያቄዎችን ያስነሳሉ፡፡ የአስተዳደር ህግን በጥልቀት ለመረዳት ከተፈለገ ሂደቱ መጀመር ያለበት ህገ መንግስትን በማጥናት ነው፡፡ በምሁራኑ አንደበት ይኸው እውነታ እንዲህ ይገለፃል፡፡ የአስተዳደር ህግ ከህገ መንግስታዊ መሰረቱ ተለይቶ በደንብ ሊታወቅ ሆነ ሊጠና አይችልም፡፡ የአስተዳደር ህግ በህገ መንግስት ማስፈጸሚያ መሳሪያነቱ የዝምድናቸውን ገጽታ በሚገባ ለማወቅ ይረዳናል፡፡ በዚህ የተግባሪነት ሚናው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ላይ የተቀመጡትን የህገ መንግስታዊነትና የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች እንዲሁም የግለሰቦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በተጨባጭ እንዲረጋገጡ በማድረግ ህገ መንግስቱን በማስፈጸም ረገድ እንደ አንድ መሳሪያ ያገለግላል፡፡ እ.ኤ.አ በ1959 ዓ.ም. የጀርመን የፌደራል አስተዳደር ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት እንደተናገሩት የአስተዳደር ህግ ‘ተጨባጭ ህገ መንግስት’ ማለትም በተግባር የሚታይ ህገ መንግስት ነው፡፡a የአንድ አገር ህገ መንግስት በዋነኛነት የዜጐችን ሰብአዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፖለቲካዊ መብቶችና ነጻነቶች ይደነግጋል፡፡ የዜጐች መብት በሌላ ግለሰብ፣ ማህበር ወይም የንግድ ድርጅት ሊጣስ ይችላል፡፡ ትልቁ አደጋ ያለው ግን ከመንግስት በተለይም ከስራ አስፈፃሚው አካል በኩል ነው፡፡ መብቶች በሚገባ እንዲጠበቁ የመንግስት አስተዳደር ልኩ ተለይቶ በታወቀ የስልጣን ገደብ ውስጥ ሊከናወን ይገባል፡፡ ሆኖም ስልጣን ሁልጊዜ በህጉ መሰረት ግልጋሎት ላይ ይውላል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ የግድ በአግባቡ ሊገራና ልጓም ሊበጅለት ይገባል፡፡ የአስተዳደር ህግ የስልጣን መቆጣጠሪያ መሳሪያ ነው፡፡ በዚህ ተግባሩ ውጤታማ የስልጣን ቁጥጥር የዜጐች ህገ መንግስታዊ መብትና ነፃነት እንዳይጣስ ዋስትና ይሰጣል፡፡ መንግስቱን በተግባር እንዲተረጐም የሚደርገውም በዚህ መንገድ ነው፤ ስልጣንን በመቆጣጠር የዜጐችን መብት በተጨባጭ ማቀዳጀት፡፡ ይህ ሚናውን በሌሎች ህገ መንግስታዊ መርሆዎች አንጻርም ጎልቶ ይታያል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት በዋነኛነት ከሚደነግጋቸው የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች መካከል ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና የህዝብ ተሳትፎ ይገኙበታል፡፡b ግልጽነት እውን የሚሆነው የመንግስት ባለስልጣናትና የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ለዜጐች መረጃ የመስጠት ግዴታቸው ከነዝርዝር አፈፃፀሙ ጭምር በህግ ተደንግጐ ሲገኝ ነው፡፡ ተጠያቂነት፤ ጠያቂውና ተጠያቂው ተለይቶ የተጠያቂነት ስልቱ በዝርዝር ህግ ካልተቀመጠ በተግባር አይረጋገጥም፡፡ የህዝብ ተሳትፎ እንዲሁ የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች በሚሰጡት ውሳኔ በተለይም ደንብና መመሪያ ሲያወጡ በጉዳዩ ጥቅም ካላቸው ወገኖች ሀሳብና አስተያየት እንዲቀበሉ የሚያስገድድ የህግ ድንጋጌ ከሌለ የህዝብ ተሳትፎ በተጨባጭ አይታይም፡፡ ግልፅነትን፣ ተጠያቂነትንና የህዝብ ተሳትፎን በተግባር ለማረጋገጥ የሚወጡ ህጐች በአስተዳደር ህግ የሚካተቱ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ህጉ እነዚህ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች በተግባር እንዲረጋገጡ በማድረግ ህገ መንግስቱን ያስፈጽማል፡፡ በህገ መንግስትና በአስተዳደር ህግ መካከል ያለው የጠበቀ ግንኙነት ልዩነታቸው የላላ መሆኑን ያሳያል፡፡ ሊጠቀስ የሚችል ቀጭን ልዩነት ቢኖር የወሰን እና የህጎች የተፈጻሚነት ደረጃ (Hierarchy of Laws) ልዩነት ነው፡፡ ከወሰን አንፃር ህገ መንግስት አጠቃላዩን የመንግስት አወቃቀርና የሶስቱን የመንግስት አካላት ብሎም በፌደራልና በክልል መንግስታት ያለውን የስልጣን ክፍፍል ስለሚወስን በይዘቱ በጣም ሰፊ ነው፡፡ በአንፃሩ የአስተዳደር ህግ የአንደኛውን የመንግስት አካል ማለትም የስራ አስፈፃሚውን ስልጣን፣ ግዴታና ተግባር ብሎም የውሳኔዎቹን ህጋዊነት የሚመለከት ህግ ነው፡፡ በህግ አውጭው የሚወጣ ህግ እና ፍ/ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ ህገ መንግስታዊነት ከጥናት አድማሱ በላይ ነው፡፡ ስለሆነም ከወሰናቸው አንጻር ህገ መንግስት መስፋቱ የአስተዳደር ህግ መጥበቡ እንደ አንድ የልዩነት ነጥብ ተደርጐ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ሁለተኛው ልዩነት የህጎች መሰላል (Hierarchy of Laws) ሲሆን በህጐች መካከል ያለውን የደረጃ ዝምድና ይመለከታል፡፡ ህገ መንግስት የአንድ አገር የበላይ ህግ እንደመሆኑ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረኑ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና የአሰራር ልምዶች ዋጋ የላቸውም፡፡ የአስተዳደር ህግ በደረጃው ከህገ መንግስት ዝቅ ብሎ የሚገኝ እንደመሆኑ መቼም ቢሆን ከህገ መንግስቱ ጋር መጣጣም አለበት፡፡ ግጭት በተነሳ ጊዜ የበላይ የሆነው ህገ መንግስት ሁልጊዜ ተፈፃሚነት አለው፡፡

የአስተዳደር ህግ ውልደትና ዕድገት በኢትዮጵያ ስለ ኢትዮጵያ


የአስተዳደር ህግ ውልደትና ዕድገት በኢትዮጵያ ስለ ኢትዮጵያ

የአስተዳደር ህግ ብሎም ውልደቱ፣ አነሳሱና ታሪካዊ ዕድገቱ ለመጻፍ ብዕሩን የሚያሾል ጸሐፊ ጭብጥ እንዳጣ የልብለወለድ ደራሲ ከየት ልጀምር? በሚል ጭንቀት ተውጦ ጣራ ላይ ማፍጠጥ አይቀርለትም፡፡ ስራውን ፈታኝ የሚያደርገው በህዝብ አስተዳደር እና በአስተዳደር ህግ ላይ የተጻፉ የታሪክ መዛግብት፣ የምርምር ጽሑፎችና መጻህፍት አለመኖር ብቻ አይደለም፡፡ በእርግጥ ለጀማሪ አጥኚ ይህ በራሱ ራስ ምታት ነው፡፡ ከመነሻ ምንጭ እጥረት ባሻገር ሌሎች ዐቢይ ምክንያቶች የአገሪቱን የአስተዳደር ህግ ጉዞ መዘገብ አድካሚ ያደርጉታል፡፡ ለመጥቀስ ያህል፤ የጥናት አድማሱ ወጥነት እና ትኩረት ማጣትa የዲሞክራሲና ህገ መንግስታዊ ዳራውb የፖለቲካና አስተዳደር መደበላለቅc የህግ አውጭውና የፍርድ ቤቶች ሚና ማነስd ባደጉት አገራት የአስተዳደር ህግ ዕድገት ጥርት ባለ መልኩ ራሱን የቻለ የህግ ክፍል ሆኖ ብቅ ማለት የጀመረው የዘመናው ‘የአስተዳደር መንግስት’ (Administrative State) መከሰት ተከትሎ ስለመሆኑ ብዙዎች የመስኩ አጥኚዎች ይስማሙበታል፡፡ በተመሳሳይ ቅኝት ስለ አገራችን አስተዳደር ህግ ታሪካዊ ገጽታዎችና መገለጫዎች ከዘመናዊ አስተዳደር ማቆጥቆጥ ጋር አስታኮ አጠቃላይ ገለጻ መስጠት ይቻላል፡፡ በርካታ የአገራችን ሆኑ የውጭ አገር ታሪክ ጸሐፊዎች በአገራን ዘመናዊ አስተዳደር የተተከለው የኃይለስላሴ ዙፋን ላይ መውጣት ተከትሎ በነበሩት ዓመታት ውስጥ እንደሆነ ይስማሙበታል፡፡ በተለይም ከኢጣሊያ ወረራ ማብቃትና የንጉሱ ዙፋን መልሶ መረከብ አንስቶ ዘመናዊ አስተዳደር ፈጣን ለውጦች አሳይቷል፡፡ ስለ ኢትዮጵያ የመንግስት አስተዳደር ሲወራ የአጼ ቴዎድሮስ ውጥን እና ጥረት ሳይጠቀስ አይታለፍም፡፡ አጼ ቴዎድሮስ ብሔራዊ ጦር ለማደራጀት፣ የቤተክስርስትያን የመሬት ይዞታ ለመቆጣጠር፣ የአካባቢ የጦር አበጋዞች በማዕከላዊ መንግስት ስር ለማዋቀር እንዲሁም የመንገድ ግንባታና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ለመዘርጋት ያደረጓቸው ጥረቶች ለቀጣይ ነገስታት መሰረት ጥለዋል፡፡ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግስት ለማቆም እና ዘመናዊ አስተዳደር ለመትከል የነበራቸው ህልም፣ ውጥን እና ፖሊሲ እንዲሁም እነዚህን ለመተግበር የወሰዷቸው ስር ነቀል እርምጃዎች የለውጥና የስልጣኔ በር ከፍተዋል፡፡ የኢትዮጵያ የአስተዳደር ህግ ውልደት ከቴዎድሮስ ይጀምራል፡፡ አስተዳደራዊ ብልሹነት እንዲቀረፍና ሹመኞች በህዝብ አገልጋይነታቸው በደል እንዳይፈጽሙ በጊዜው ሲያደርጉት የነበረው ክትትል እና የስልጣን ቁጥጥር በኢትዮጵያ የታሪክ መጻህፍት ጎልቶ ባይወጣም በአንዳንድ ጽሁፎች ተዘግቦ ይገኛል፡፡ በደርግ ወታደራዊ መንግስት ልዩ ፍርድ ቤት ይዘጋጅ የነበረው ሕግና ፍትሕ መጽሔት በመጋቢት 1987 እትሙ አጼ ቴዎድሮስ ሙስና እና የአስተዳደር ብልሹነት እንዲወገድ ሲያደርጉት የነበረውን ተጋድሎ ሌላ ምንጭ ጠቅሶ እንደሚከተለው ዘግቦታል፡፡e ቴዎድሮስ ወዘልውጥ በመሆንና አልባሌ ልብስ በመልበስ በመንግስቱ ውስጥ ያለው የአስተዳደር መበላሸት መቆጣጠር፣ ጉቦኞች ሹማምንቶቻቸውን መከታተልና ማጋለጥ ያዘውትሩ ነበር፡፡ በሕዝብ ችግር የጨከኑትን፣ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የመንግስቱን ስራ የሚበድሉትንና ኅብረተሰቡን ያጉላሉትን ሹማምንት ከስልጣን ወንበራቸው ገልብጠዋል፡፡ አባ ታጠቅ ስልጣን በጨበጡ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ውስጥ የጯሂ ጠባቂ (የህዝብ ዕንባ ጠባቂ) ሹማቸው ጉቦ መቀበሉን በማወቃቸውና ራሳቸውም ሲቀበል በማየታቸው በአደባባይ አጋልጠው ሽረውታል፡፡…የጯሂ ጠባቂነቱንም ሥራ ራሳቸው ይዘዋል፡፡ አጼ ቴዎድሮስ የመንግስት ስልጣን በህግና በስርዓት እንዲገራ የነበራቸው ቆራጥ አቋም በታሪክ በተዘገቡ ጥቂት የጊዜው ፍርዶች ላይ ይታያል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንደኛው በጳውሎስ ኞኞ ‘አጤ ቴዎድሮስ’ መጽሐፍ ላይ እንደሚከተለው ተዘግቧል፡፡ ቴዎድሮስ ጋይንት ላይ ሰፍረው ሳለ ወታደሮቻቸውን በባላገሩ ላይ ተሰሪ አስገቡ፡፡ ባላገሩ እንዲቀልብ በየቤቱ ማስገባት ማለት ነው፡፡ ተሰሪ ከገቡት ወታደሮች መሀል አንዱ ወታደር አንዱን ባላገር ገደለው፡፡ የሟች ወገንም ከቴዎድሮስ ዘንድ መጥቶ አመለከተ፡፡ ቴዎድሮስም ወታደራቸውን ሁሉ አፈርሳታ አስቀምጠው ገዳዩን አውጣ ብለው ያዙ፡፡ ወታደሩም በመላው አድሞ ገዳዩን አላየንም እያለ በቄስ እየተገዘተ ወጣ፡፡ የሟች ገዳይ ወታደር በመጥፋቱ ቴዎድሮስ ተናደው ‘ወታደር ብላ፤ ባላገር አብላ ያልሁ እኔ ነኝ፡፡ ደመኛህም እኔ ነኝና እኔን ግደል’ ብለው ብለው ተነስተው ለከሳሹ ነገሩት፡፡ ከሳሹም ‘እኔ ንጉስ መግደል አይቻለኝም’ አለ፡፡ ቴዎድሮስም ደም በከንቱ አይቀርም ብለው ለሟቹ ወገን የደም ገንዘብ ዋጋ ሰጥተው ሸኙት፡፡f በሌላ ፍርድ ላይ እንዲሁ ለሁለት ወታደሮቻቸው የሰጡት እርስ በርሱ የሚጋጭ ትዕዛዝ የአንደኛውን ወታደር ሞት በማስከተሉ ለሞቱ መከሰት ተጠያቂ ተደርገው ስለተፈረደባቸው በዚያ ንጉስ በማይከሰስበት፤ ሰማይ በማይታረስበት ዘመን ቅጣታቸውን ተቀብለው ፍርዱን ፈጽመዋል፡፡ ታሪኩ በአጭሩ እንደዚህ ነው፡፡ ቴዎድሮስ አንዱን ወታደራቸውን ‘በፍርቃ በር በኩል እርጉዝ ሴት እንኳን ብትሆን እንዳታልፍ ጠንክረህ ጠብቅ’ ብለው ካዘዙት በኋላ በሌላ ቀን ደግሞ ሌላውን ወታደር ጠርተው ‘ፈረስ እያለዋወጥህ ይህን ወረቀት የጁ ሰጥተህ በአስቸኳይ በስድስት ቀን ውስጥ ተመልሰህ እንድትመጣ’ ብለው ሲልኩት እየጋለበ ሄዶ ፍርቃ በር ላይ ሲደርስ ጠብቅ ከተባለው ወታደር ጋር ‘አልፋለው! አታልፍም!’ እሰጥ አገባ ገጥሙ፡፡ በግዴታ ለማለፍ መንገድ ሲጀምር ዘበኛው ተኩሶ ገደለው፡፡ የንጉስ ትዕዛዝ ሲፈጽም የነበረ የንጉስ መልዕክተኛ በዚህ መልኩ መገደሉ ያንገበገባቸው የሟች ወገኖች ገዳዩን በመክሰስ ከቴዎድሮስ ዘንድ አቀረቡት፡፡ ቴዎድሮስም ችሎት አስችለው ፍርድ እንዲፈረድ አደረጉ፡፡ በችሎት የተቀመጠው ፈራጅ ሁሉ እየተነሳ ገዳዩን ‘በደለኛ ነህ እምቢ አልፋለው ቢልህስ ለንጉስ ታሰማ ነበር እንጂ ራስህ ፈርደህ እንዴት የንጉስ መልዕክተኛ ትገድላለህ? አሁንም ስትሞት ይታየናል’ እያሉ ፈረዱ፡፡ አንደኛው ፈራጅ ግን ከተቀመጡበት ተነስተው ከሌሎቹ ፈራጆች በመለየት ሁለት ተቃራኒ ንጉሳዊ ትዕዛዝ መስጠት አግባብ ስላልሆነ ጥፋቱ የሚመለከተው ንጉሠ ነገሥቱን እንደሆ ከተናገሩ በኋላ ‘ነገር ግን እሳቸው ብርሀን ስለሆኑ ምን ይደረግ?’ በማለት የፍርድ ሀሳባቸውን አሳርገው ተቀመጡ፡፡ አጤ ቴዎድሮስም ይህን የልዩነት የፍርድ ሀሳብ አድንቀው ከተቀመጡበት ተነስተው በተከሳሹ ወታደር ቦታ ወርደው ቆሙ፡፡ በመጨረሻም ፈራጆች በፈረዱት መሰረት በጊዜው የሚከፈለውን የደም ዋጋ አጠፌታውን ብር 500 ከፍለው ጉዳዩ በስምምነት አለቀ፡፡g የቴዎድሮስ ሞትን ተከትሎ የተነሱት ነገስታት ማለትም አጼ ዮሐንስ እና አጼ ምኒልክ በተለያየ ጊዜ በተደረጉ የውስጥና የውጭ የጦርነት ዘመቻዎች በመጠመዳቸው ዘመናዊ አስተዳደር መሰረታዊ ለውጥ አላሳየም፡፡ ሆኖም ከአድዋ ጦርነት በኋላ ማዕከላዊ መንግስት እየተጠናከረ ሲሄድ የተወሰኑ መሻሻሎች ታይዋል፡፡ በሚኒልክ ዘመነ መንግስት ዘመናዊ አስተዳደር ለመትከል ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በ1900 ዓ.ም. የሚኒስትሮች መሾም በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡ ጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም. የተሰየሙት ሚኒስትሮች የሚከተሉት ናቸው፡፡h የፍርድ ሚኒስትር የጦር ሚኒስትር የጽህፈት ሚኒስትር የአገር ግዛት ሚኒስትር የገንዘብ ሚኒስትር እና የንግድ ሚኒስትር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የእርሻና መስሪያ ሚኒስትር የግቢ ሚኒስትር የመንግስቱን ስራ እንዲሰሩ የተደለደሉት ሚኒስትሮች ስልጣንና ተግባራቸው በዝርዝር ደንብ ተወስኖላቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እያንዳንዱ ሚኒስትር የሚያስፈጽማቸው የተለያዩ ህጎች ወጥተዋል፡፡ እነዚህ ህጎች እስከ ጣሊያን ወረራ ድረስ በአጼ ምኒልክና ሀይለስላሴ አልጋ ወራሽ በነበሩባቸው ዓመታት በግብር ብቻ ተወስኖ የነበረውን የመንግስትና የግለሰብ ግንኙነት አድማሱን አስፍተውታል፡፡ በእነዚህ ጊዜያት የመንግስት ሚና ከጠባቂነት ቀስ በቀስ ወደ የክትትልና ቁጥጥር (regulation) እና ማህበራዊ አገልግሎት አቅራቢነት ተሸጋግሯል፡፡ በቁጥጥር ረገድ በርካታ የንግድ እና የግብርና ተግባራት በቅድሚያ ከሚመለከተው ሚኒስቴር ፈቃድ እንደሚያስፈልግ በተለያዩ ህጎች ተደንግጓል፡፡ ለአብነት ያህል፤ የወፍጮ መዘውር ማቆምና መፍጨትi ትምባሆ መዝራትና መሸጥj አውሬ ማደን እና ዓሣ መያዝ (ማጥመድ)k በማህበራዊ አገልግሎት አቅርቦት ትምህርት ቤት፣ ሆስፒታል፣ ቴሌፎን እና ፖስታ፣ ባቡር እና ሌሎችም ቀስ በቀስ ተስፋፍተዋል፡፡ በ1927 ዓ.ም. የጡረታ ስርዓት ለጉምሩክ ሠራተኞችና የጉምሩክ ወታደሮች (እንደ አሁኑ ፌደራል ፖሊስ ዓይነት) ተዘርግቷል፡፡ የጡረታ መውጫ ዕድሜ ለወታደሮች ሃምሳ፣ ለሠራተኞች 60 ዓመት ሲሆን ለአበል የሚያበቃው የአገልግሎት ዘመን እንደ ቅደም ተከተሉ ሃያ አምስት እና ሰላሳ ዓመት ነው፡፡l በጊዜው የነበረው የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ከሞላ ጎደል አሁን ካለንበት ዘመን ጋር ተቀራራቢ ነበር ለማለት ይቻላል፡፡ በጊዜው የነበረው የጉምሩክ ሹማምንትና ሠራተኞች ዲሲፕሊን አፈጻጸም ለዚህ አባባል ዐቢይ ምስክር ነው፡፡ የጉምሩክ ሠራተኛ በስራው ላይ ጥፋትና የሚጎዳ ነገር ከሰራ በየክፍሉ ያሉ ሹሞች ከስራ አግደው ስራውን በሌላ ሰራተኛ ያሰራሉ፡፡ ሆኖም በራሳቸው የቅጣት እርምጃ ለመውሰድ ስልጣኑ የላቸውም፡፡ ስለ ጥፋቱ አኳኋን መግለጫ አዘጋጅተው ከበላያቸው ላለው ዳይሬክተር ያስታውቃሉ፡፡ ዳይሬክተሩ እንደ ጥፋቱ ክብደት እና ድግግሞሽ እስከ አንድ ወር ሙሉ ደመወዝ ‘ቅጣት’ ለመወሰን ስልጣን ነበረው፡፡ ሆኖም ቅጣቱ አስገዳጅ ሳይሆን የውሳኔ ሀሳብ ዓይነት ይዘት ያለው ነው፡፡ ዳይሬክተሩ የወሰነውን ቅጣት እና የጥፋቱን ሁኔታ ገልጾ ማስታወቂያ ለሠራተኛው ከሰጠው በኋላ ሠራተኛው ዋስ ጠርቶ አዲስ አበባ ለነበረው የዋናው ዲሬክተር ጽ/ቤት ይልከዋል፡፡ በመቀጠል ክርክር የሚካሄድበት ቀነ ቀጠሮ ይቆረጣል፡፡ በቀጠሮ ቀን ጥፋት የሚገኝባቸውን ሠራተኞች ሥርዓት ለማየት የተመረጡት ሹማምንት ተሰብስበው ነገሩን ከመረመሩ በኋላ ፍርድ ይሰጣሉ፡፡ የፍርዱንም ግልባጭ ለሠራተኛው ይሰጠቱታል፡፡ በፍርዱ ቅሬታ ካለው ለንግድ ሚኒስትር ይግባኝ ማሰማት ይችላል፡፡ ሚኒስትሩም ፍርዱንና ነገሩን አይቶ መርምሮ የመጨረሻ ፍርድ ይሰጣል፡፡ ይህ ስርዓት ተፈጻሚነቱ በዋናው ዳይሬክተርና ሚኒስትሩ ለተቀጠሩ የበታች ሠራተኞች ብቻ ነው፡፡ በንጉሱ አዋጅ ስራ የተቀጠሩ ሠራተኞችና ሹማምንት ጉዳይ የመጀመሪያ ደረጃ ውሳኔ የሚያገኘው በሚኒስትሩ ሲሆን ይግባኝ የሚቀርበውና የመጨረሻ ፍርድ የሚሰጠው በንጉሱ ችሎት ነው፡፡m ከዲሲፕሊን ጉዳዮች በተጨማሪ በሌሎች ጉዳዮችም የውሳኔ አሰጣጥ እና ቅሬታ አፈታት ስርዓት በዘመኑ ህጎች በስፋት የሚታይ ነበር፡፡ ለምሳሌ በትምባሆ ሬዢ አፈጻጸም ደንብ በ30ኛው ክፍል ደንቡን በመተላለፍ የተቀጣ ሰው እንዳገሩ ርቀት ካንድ ወር እስከ አራት ወር ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ለእርሻ ሚኒስቴር ሊያመልክት እንደሚችልና ሚኒስቴሩም ነገሩን እንደገና እንደሚያደላድለው (ነገሩን ሰምቶ ውሳኔ እንደሚሰጥ) በደንቡ ላይ ተመልክቷል፡፡n የ1923 ህገ መንግስት ዜጎች የሚደርስባቸውን የአስተዳደር በደል ቅሬታ የማሰማት መብታቸውን ህገ መንግስታዊ ዕውቅና በመስጠት የመጀመሪያው ነው፡፡ በአንቀጽ 28 ላይ እንደተደነገገው ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለመንግስት አቤቱታ የማቅረብ መብት ተጠብቆላቸዋል፡፡ በተሻሻለው የ1948 ህገ መንግስት ላይም ተመሳሳይ ይዘት ያለው ድንጋጌ በአንቀጽ 62 ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ደርግ ስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ በታወጀው የኢ.ህ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 52 በመንግስት አካላት እና ህዝባዊ ድርጅቶች ላይ ቅሬታ የማሰማት መብት ተጠብቋል፡፡ በተጨማሪም የሚቀርቡ ቅሬታዎች ተመርምረው ምላሽ እንደሚሰጣቸው በድንጋጌው ላይ ተመልክቷል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የተከተለው አቅጣጫ ከባለፉት ይለያል፡፡ አቤቱታ የማሰማት መብትን በተለይ ዕውቅና ከመስጠት ይልቅ በአንቀጽ 37 የዜጎችን ፍትሕ የማግኘት መብት ደንግጓል፡፡ የዚህ ድንጋጌ ርዕስና ይዘት በወሰን (scope) አይጣጣሙም፡፡ ፍትሕ የማግኘት መብት ዜጎች ለሚደርስባቸው አስተዳደራዊ በደል በመደበኛ እና ኢ-መደበኛ የፍትሕ ተቋማት ቅሬታ አቅርበው መፍትሄ የማግኘት መብታቸውን ያካትታል፡፡o ይህን መሰረተ ሀሳብ በሚያንጸባርቅ አኳኋን የተቀረጸው የአንቀጽ 37 ርስስ በንዑስ አንቀጽ አንድ ላይ የሚደነግገው በፍርድ የሚያልቁ ጉዳዮችን ለመደበኛና ፍ/ቤቶች እና ለአስተዳደር ጉባዔዎች (Administrative tribunals) አቅርቦ ዳኝነት የማግኘት መብት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የመብቱ ወሰን ለህግ አውጨው፣ ለአስተዳደሩና ለሌሎች ተቋማት (ለምሳሌ እንባ ጠባቂና ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን) ቅሬታ የማሰማት መብትን አይጨምርም፡፡ በአስተዳደር ህግ ታሪካዊ ዕድገት ውስጥ የአስተዳደር ጉባዔዎች (Administrative tribunals) ሚና ጉልህ ስፍራ ይይዛል፡፡ በብዙ አገራት እየተለጠጠና እየተወሳሰብ የመጣው የመንግስት አስተዳደር በግለሰብና በመንግስት መካከል የሚካሄዱ ክርክሮችን ሙሉ በሙሉ በመደበኛ ፍ/ቤቶች አማካይነት መዳኘት አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ በዚህ የተነሳ የአስተዳደር ጉባዔዎች (Administrative tribunals) አብዛኞቹን ክርክሮች በመዳኘት ውጤታማ የዳኝነት አካላት ለመሆን በቅተዋል፡፡ ሆኖም በአገራችን በተጨባጭ የሚታይ የረባ ውጤት አላስመዘገቡም፡፡ ድሮም ሆነ ዘንድሮ እነዚህን ተቋማት ከፍትሕ ስርዓቱና ከአስተዳደር ሂደቱ ጋር በማቆራኘት ለማደራጀት ሙከራዎች አልተደረጉም፡፡ የ1923 ህገ መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ለአስተዳደር ጉባዔዎች ህገ መንግስታዊ ዕውቅና በመስጠት አስተዳደራዊ ጉዳዮችን የመወሰን ስልጣን እንዳላቸው የደነገገ ቢሆንም በተግባር ግን ተቋማዊ መዋቅር ተዘርግቶላቸው አልተቋቋሙም፡፡ በዚህ ህገ መንግስት አንቀጽ 54 ላይ እንደተመለከተው፤ በማናቸውም በመንግስት ስራ ምክንያት የሚነሡትን ነገሮች የሚፈርዱ በተለይ የቆሙት የፍርድ ቤቶች ናቸው እንጂ ሌሎች ዳኞች እነዚህን ነገሮች ለመፍረድ አይችሉም፡፡ የድንጋጌው ሀሳብ በእንግሊዝኛው ቅጂ ላይ ግልጽ ተደርጓል፡፡ Special courts shall judge all matters relating to administrative affairs, which are withdrawn from the jurisdiction of other courts. ህገ መንግስቱ በአማርኛው ‘በተለይ የቆሙት ፍርድ ቤቶች’ በእንግሊዝኛው Special courts በሚል በጥቅል የጠቀሳቸው ፍርድ ቤቶች ምን ዓይነት ፍርድ ቤቶች ሊቋቋሙ እንደታሰበ አይጠቁምም፡፡ ሆኖም ስለሚያዩት ጉዳይ የተቀመጠው ገለጻ የአስተዳደር ፍርድ ቤቶች እንደሆኑ እንረዳለን፡፡ የህገ መንግስቱ ምንጭ ይህንን አባባል የበለጠ ያጠናክራል፡፡ የ1923 የኢትዮጵያ ህገ መንግስቱ በአብዛኛው የተቀዳው በጃፓን እ.ኤ.አ በ1889 ዓም. በይፋ ከታወጀው የመጂ ህገ መንግስት (Meji Constitution) ነው፡፡ በወቅቱ የነበሩት የጃፓን ገዢዎች አስተዳደራዊ ጉዳዮችን ከመደበኛ ፍ/ቤቶች ለማግለል የነበራቸውን ጽኑ ፍላጎት የሚደግፍ የአስተዳደር ህግ ስርዓት ሲያጠኑ ከመደበኛ ፍ/ቤት ትይዩ ሆኖ ራሱን ችሎ የተቋቋመው የጀርመን የአስተዳደር ፍ/ቤት ተመራጭ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚሁ መሰረት በመንግስት ላይ የሚቀርቡ ክሶች ከመደበኛው በተለየ በሚቋቋሙ የአስተዳደር ፍርድ ቤቶች እንደሚዳኙ በህገ መንግስታቸው በመደንገግ እ.ኤ.አ በ1890 ላይ ይህን ፍ/ቤት አቋቁመዋል፡፡p በኢትዮጵያ እስከ 1928 ዓ.ም. ድረስ የዳኝነት መብት ከአስተዳደር ስልጣን ጋር የተያያዘ ስለነበር ዳኝነት ሲሰጥ የነበረው በአካባቢው ሹማምንት፣ አገረ ገዢዎችና በራሳቸው በነገስታቱ አማካይነት ነው፡፡q ዳኝነት ከአስተዳደር ተለይቶ መደበኛ ፍ/ቤቶች የተቋቋሙት በ1934 ዓ.ም. ነው፡፡r ዓበይት ህግጋት እስከተጠናቀሩበት እስከ 1950ዎቹ ድረስ እነዚህ ፍ/ቤቶች የሚሰሩባቸው ህጎች ከሞላ ጎደል ልማዳዊ ነበሩ፡፡ ስለሆነም የተጠናከረ አስተዳደር ሆነ ዘመናዊ የህግና የዳኝነት ስርዓት ባልነበረበት በ1923 ዓ.ም. እና ቀጣይ ዓመታት የአስተዳደር ፍ/ቤቶችን አስፈላጊ የሚያደርግ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሁኔታ አልነበረም፡፡ በተግባር ሲታይም ከወረቀት የዘለለ ህልውና አልነበራቸውም፡፡ እስካሁን ድረስ በአገራችን ራሱን ችሎ በተለይ የቆመ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ የለም፡፡ በንጉሱ ጊዜ እ.አ.አ በ1967 የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ረቂቅ ተዘጋጅቶ የነበረ ቢሆንም ከረቂቅነት ደረጃ አላለፈም፡፡ ቀጣይ ሙከራዎች የተደረጉት በ1993 ዓ.ም. እና 2001 ዓ.ም. ሲሆንም በሁለቱም ጊዜያት በፍትሕ እና የህግ ስርዓት ምርምር ኢንስቲትዩት አማካይነት ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህጎች ተዘጋጅተዋል፡፡ እንደባለፈው ሁሉ የእነዚህም እጣ ፈንታ ከረቂቅነት መሻገር አልቻለም፡፡  

የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት አፈፃፀም


የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት አፈፃፀም

ተደጋግሞ እንደተገለፀው የመንግስት ስልጣን በወርድም በቁመትም እየሰፋ በመጣ ቁጥር ለዜጐች መብትና ነፃነት ፀር ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ የስልጣንን አስፈላጊነት አምኖ ተቀብሎታል፡፡ ውጤታማ አስተዳደር እንዲሁም ቀልጣፋ የአገልግሎት አቅርቦት እንዲኖር የሚያስር ሳይሆን የሚፈታ ስልጣን ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም ከህግና ከህገ መንግስት የሚያፈነግጥ ስልጣን ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ የበዘፈቀደ ድርጊት፣ ‘እንደፈለግኩኝ እሆናለው እፈልጣለው እቆርጣለው!’ የሚል አካሄድ አቅመ ቢስ የሆነውን ዜጋ የመኖር፣ በነፃነት የመንቀሳቀስ፣ የመናገር፣ ሀሳብን የመግለፅና ንብረት የማፍራት መሰረታዊ መብት አለገደብ ይሸረሽራል፡፡ የአስተዳደር ህግ የሰብዓዊ መብትን በማስጠበቅ ረገድ ያለው ሚና የሁለቱን ትስስር በሚገባ ያሳየናል፡፡ ህጉ በሰብዓዊ መብት አጠባበቅና አፈፃፀም ላይ ያለውን አዎንታዊ ተፅእኖ በሚገባ ለመረዳት ከሰብዓዊ መብቶች አተገባበር አንፃር የመንግስትን ግዴታ መተንተኑ አግባብነት ይኖረዋል፡፡ እነዚህም ሚናዎች (ግዴታዎች) የማክበር (respect) የማስከበር (protect) እንዲሁም የመፈጸምና የማስፈፀም (enforcement) ናቸው፡፡ በመጀመሪያው መብቶችን የማክበር የመንግስት ሚና ዜጐች ነፃ ሆነው መብታቸውን ሲጠቀሙ ከየትኛውም የመንግስት አካል የሚመጣ ጣልቃ ገብነትን ይገድባል፡፡ በተለይም መሰረታዊ በሚባሉት በህይወት የመኖር፣ የመፃፍ፣ የመናገር፤ የፈለጉትን ሀይማኖት የመከተል፤ በነፃነት የመዘዋወርና ንብረት የማፍራት መብቶችና ነፃነቶች በተግባር የሚረጋገጡት መንግስት እጁን ሲሰበስብ ነው፡፡ እነዚህ መብቶች በመንግስት በተለይ በስራ አስፈፃሚውና በስሩ ባሉት የአስተዳደር ተቋማት ውሳኔ፤ ትዕዛዝ፤ ደንብና መመሪያ አማካይነት አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ፡፡ ህገ መንግስቱ የበላይ ህግ እንደመሆኑ ይህን የሚቃረን ህግ፣ ውሳኔና አሰራር ሁሉ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ይህን መሰሉ የህገ መንግስታዊነት ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ውስጥ አይወድቅም፡፡ ይሁን እንጂ የህገ መንግስታዊነት ብቻ የሚመስል ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ማእቀፍ የሚሸፈንበት አጋጣሚ ሰፊ ነው፡፡ በአንድ የአስተዳደር ተቋም የወጣ መመሪያ በህግ አውጭው ከተሰጠ የውክልና ስልጣን በማለፍ የዜጐችን ሰብዓዊ መብት የሚገድብ ሆኖ ከተገኘ በውስጡ የህገ መንግስታዊነት (constitutionality) ጥያቄ ያዘለ ቢሆንም በዋናነት ግን የአስተዳደር ህግ ሊመልሰው የሚገባ የህጋዊነት (legality) ጥያቄ ነው፡፡ ልዩነታቸውን የበለጠ መረዳት እንዲያስችልን የሚከተለውን የድሮው የገቢዎች ሚኒስቴር የአሁኑ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መመሪያ እንመልከት፡፡ ማንኛውም የጉምሩክ ፖሊስ ሰላማዊ ስልፍና የስራ ማቆም አድማ ማድረግ አይችልም፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ለማንኛውም ሰው የተረጋገጠ መብት ነው፡፡ መብቱን የሚያጎናጽፈው የአንቀጽ 30 ንዑስ ቁጥር 1 እንዲህ ይነበባል፡፡ ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነፃነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ አንድ መመሪያ በስራ አስፈፃሚው አካል ሲወጣ ከህግ አውጭው በግልጽ የተሰጠ የውክልና ስልጣን (Delegation) ሊኖር ይገባል፡፡ መመሪያው የውክልና ስልጣኑን ገደብ ካለፈ ከስልጣን በላይ (Ulta vires) ነው፡፡ ስለሆነም በህግ ፊት ዋጋ አልባ (null and void) ነው፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር ይህን መመሪያ ሲያወጣ የስልጣን ምንጩን የጉምሩክ ባለስልጣንን ለማቋቋምና አስራሩን ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁ. 368/1995 አንቀጽ 8 (2) (ሐ) እንደሆነ ይጠቅሳል፡፡ ይህ የተጠቀሰው የህግ ድንጋጌ እንዲህ ይነበባል፡፡ የጉምሩክ ህግ እንዲያስከብር ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የተመደበን የፖሊስ ኃይል ሚኒስቴሩ የፌደራል ፖሊስ አዋጅን ተከትሎ በሚያወጣው መመሪያ መሰረት በስራ ያሰማራል፡፡ ያስተዳድራል፡፡ ጥፋት ሲገኝም ያሰናብታል፡፡ ይህ አንቀጽ የጉምሩክ ፖሊስ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርግ በመመሪያ እንዲከለክል ለገቢዎች ሚኒስቴር ስልጣን አይሰጥም፡፡ ከተወካዮች ምክር ቤት ግልፅ ስልጣን ባልተሰጠበት ሁኔታ የወጣው ይህ መመሪያ ህጋዊነት ሆነ ተፈፃሚነት የለውም፡፡ የአስተዳደር ህግ ይህን መሰል መመሪያዎች በዘፈቀደ እየወጡ የዜጐችን መብትና ነፃነት እንዳይጥሱ በተለያዩ መንገዶች በመቆጣጠር መንግስት ሰብዓዊ መብት የማክበር ግዴታውን እንዲወጣ ያደርጋል፡፡ የመንግስት የማስፈፀም ኃላፊነት አብዛኛውን ጊዜ ከማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ መብቶች ጋር በቀጥታ ተያይዞ ይነሳል፡፡ መንግስት በዜጐች መብት ላይ ጣልቃ አለመግባቱ ወይም እጁን መሰብሰቡ ብቻ አይበቃም፡፡ ለዜጋው መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማለትም ጤና፣ መብራት፣ ውሃ፣ መንገድ ወዘተ… ካላቀረበ ነፃ መሆን በራሱ ፋይዳ የለውም፡፡ የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት ትሰስር ከመንግስት የማስከበር ግዴታ አንጻርም ሊቃኝ ይችላል፡፡ ከዚህ አንጻር መንግስት ሰብዓዊ መብትን በማስከበር ኃላፊነቱ መብት እንዳይጣስ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶች በህግ እና በተቋማዊ አደረጃጀት የማጠናከር፣ በመብት መጣስ ጉዳት ለደረሰበት ዜጋ ፈጣን ፍትህ የሚያገኝበትን ስርዓት መዘርጋት አለበት ማለት ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ መንግስት የዳበረ የአስተዳደር ህግ እና የአስተዳደር ህግ ስርዓት መቅረጽ፣ መትከልና ማጐልበት ይጠበቅበታል፡፡

የሕግ የበላይነት


የህግ የበላይነት
ብዙ ምሁራን በየፊናቸው በምርምርና ጥናት ባገኙት እውቀት ተመርኩዘው የህግ የበላይነት መርህ ምንነት፤ ይዘትና ፋይዳውን አስመልክቶ አያሌ ንድፈ ሀሳባዊ ትንታኔዎችን አቅርበዋል፡፡ በአገራችን ደግሞ አባቶችና እናቶች በልባቸው ከተጻፈው እውነትና ከልምድ ከቀዱት ቱባ እውቀት በመነሳት የህግ የበላይነትን ጽንስ ሀሳብ በአንድ አባባል እንዲህ ይገልጹታል፡፡ “በፍርድ ከሄደች በቅሎዬ ያለፍርድ የሄደች ዶሮዬ!” የዚህ ተረትና ምሳሌ አንኳር መልዕክት ለጥቂት ሰዎች ብቻ የተገለጠ ሳይሆን በመላው ማህበረሰብ ዘልቆ የገባ ሀቅ ነው፡፡ እናም ይህን የህግ የበላይነት ፅንሰ ሓሳብን ጠንቅቆ ያወቀው ማህበረሰብ ህግ ሲጣስ፤ ፍትህ ሲጓደል፤ መብት ሲታፈን፤ ስርዓት አልበኝነት ሲነግስ፤ ማን አለብኝነትና በዘፈቀደኝነት ሲንሰራፋ፤ የግሉ የሆነችው ዶሮ ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ሲቀማ ድምፁን አጉልቶ ይጮሀል፤ በህግ አምላክ! ይላል፡፡ የጮኸው የዶሮዋ ዋጋ አንገብግቦት አይደለም፡፡ የተወሰደችበት መንገድ እንጂ፡፡ በፍርድ ከሆነ፤ በህጉ መሰረት ከሆነ እንኳንስ ለዶሮ ለበቅሎም ቄብ አይሰጠውም፡፡ በህዝብ አስተዳደር፤ ፖለቲካ ሳይንስ፤ ህግ እና በሌሎችም የጥናት መስኮች የሚገኙ ምሁራን ስለ የህግ የበላይነት ምንነትና ይዘት ያላቸው ግንዛቤና አስተሳሰብ የተራራቀ ከመሆኑ የተነሳ ጽንሰ ሀሳቡ አሁንም ድረስ ቁርጥ ያለ ትርጓሜ አልተገኘለትም፡፡ አንድ የመስኩ ምሁር ይህንን ሀሳብ በማጠናከር እንዳብራራው፤ ‘[T]he rule of law’, like ‘democracy’, has no single meaning: it is not a legal rule, but a moral principle, which means different things to different people according to their particular moral positions.a በዚህ የተነሳ በተለያዩ አገራት የፖለቲካና የህገ መንግስት ስርዓት ውስጥ ይዘቱና አፈጻጸሙ የተለያየ አንዳንዴ የማይጣጣም መልክ በመያዙ መሰረታዊ እሳቤው ወጥነት ርቆታል፡፡ ለምሳሌ በእንግሊዝ አንደኛውና የህግ የበላይነት መገለጫ በመንግስትና በግለሰብ መካከል የሚነሱ ክርክሮች በመደበኛ ፍ/ቤቶች ብቻ መዳኘታቸው ነው፡፡ ያ ማለት በእንግሊዛዊ አይን ፈረንሳይ ውስጥ የህግ የበላይነት የለም እንደ ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በፈረንሳይ በግለሰብና በመንግስት መካከል የሚነሱ ክርክሮች ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ድረስ የሚዳኙት ከመደበኛ ፍ/ቤት ትይዩ ራሱን ችሎ በተቋቋመ የአስተዳደር ፍ/ቤት ስርዓት አማካይነት ነው፡፡ በእንግሊዝ ሌላኛው የህግ የበላይነት ትርጉም የግለሰቦች መብትና ነፃነት መደበኛ ፍ/ቤቶች በቀረቡላቸው ተጨባጭ ጉዳዮች የሚሰጡት ውሳኔ ውጤት ነው የሚል ይዘት አለው፡፡ ይህ አስተሳሰብ በእንግሊዝ እውነት ቢሆንም የኛን አገር ጨምሮ የተጻፈ ህገ መንግስት ባላቸው እንደ አሜሪካ ባሉ አገራት የዜጐች መብቶችና ነፃነቶች በህገ መንግስቱ ላይ በጽሑፍ ይዘረዘራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሊብራል ዲሞክራሲ ስርዓት ውስጥ የህግ የበላይነት ማለት በህጉ መሰረት ከመግዛትና ከማስተዳደር ባለፈ የህጉ ይዘት (ለምሳሌ ፍትሐዊነቱ፤ የዜጐችን መብት ማክበሩ፣ ህጉ የወጣው ህዝብ ወዶና ፈቅዶ በመረጣቸው ተወካዮች መሆኑ ወዘተ…) ብሎም የገለልተኛና ነፃ ፍ/ቤቶች፤ የዲሞክራዊ ተቋማት፤ ነፃ ፕሬስ ወዘተ… መኖር ሁሉም በህግ የበላይነት ጽንስ ሀሳብ ውስጥ የሚካተቱ ናቸው፡፡ ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ የሊብራል ዲሞክራሲ ጠበል አልተጠመቁም በሚባልላቸው መንግስታት (ለምሳሌ በቻይና) ጽንሰ ሀሳቡ ስልጣን ያለው አካል በሚያወጣቸው ህጐች መሰረት መግዛትና ማስተዳደር ላይ ብቻ የተገደበ ነው፡፡ የህግ የበላይነት መርህ የአስተዳደር ህግ (በተለይ በእንግሊዝ) የተተከለበት መሰረት ነው፡፡ በዚህ መርህ መሰረት ስራ አስፈፃሚው፣ የአስተዳደር መ/ቤቶች እና የአስተዳደር ጉባዔዎች የሚሰጡት ውሳኔ በህጉ መሰረት መሆን ይኖርበታል፡፡ በመንግስት አስተዳደር ውስጥ ህጋዊነት የሚሰፍነው ስልጣን የተሰጠው ማናቸውም የመንግስት አካል የሚወስዳቸው እርምጃዎች፣ የሚፈጽማቸው ድርቶች፣ የሚሰጣቸው ውሳኔዎች እና የሚያወጣቸው ደንብና መመሪያዎች በህግ ጥላ ስር መሆናቸው ሲረጋገጥ ነው፡፡ የመንግስት ባለስልጣናት የሚሰጡት ውሳኔ በህግ ከተቀመጠው የስልጣን ክልል በላይ ከሆነ ውሳኔው የህግ የበላይነት መርህን እንደሚጥስ ጥርጥር የለውም፡፡ ህጋዊነት መከበሩን ማረጋገጥ ማለት አስተዳደራዊ ድርጊት፣ ውሳኔ፣ እርምጃ፣ ደንብና መመሪያ በህግ በተቀመጠው የስልጣን ገደብ ውስጥ መሆኑን አሊያም አለመሆኑን ማረጋገጥ ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የመደበኛ የፍርድ ቤቶች ተግባር ነው፡፡ ይህንን ተግባር በሚያሳንስ መልኩ በፍርድ ቤቶች የዳኝነት ስልጣን ላይ በህግ አውጭው የሚደረግ ገደብ በውጤቱ የህግ የበላይነት መርህን ይሸረሽራል፡፡ ገደቡ በህግ የበላይነት መርህ ላይ ከሚፈጥረው አደጋ በተጨማሪ የዜጎችን ፍትህ የማግኘት መብት ያጣብባል፡፡ በተለይም ይህ መብት ህገ-መንግስታዊ እውቅና የተሰጠው ከሆነ የፍርድ ቤቶችን ስልጣን መገደብ ዞሮ ዞሮ የዜጎችን ህገ-መንገስታዊ መብት መገደብ ነው፡፡ የህግ የበላይነት መርህ የአስተዳደር ህግ መሰረት ብቻ ሳይሆን ገደብ ጭምር እንደሆነ ማውሳት ያስፈልጋል፡፡ የውሳኔን ህጋዊነት ማረጋገጥ በይዘቱ ላይ መቆጠብን ያስከትላል፡፡ ፍ/ቤቶች የህግ የበላይነት በማስከበር ሚናቸው የአስተዳደራዊ ውሳኔዎች ይዘት እንዳያጣሩ ወይም በፖሊሲ ጥያቄዎች ጣልቃ እንዳይገቡ ይገድባቸዋል፡፡

መሰረታዊ የመንግሥት አስተዳደር መርሆዎች


መሰረታዊ የመንግስት አስተዳደር መርሆዎች

መልካም አስተዳደር ምንም እንኳን በጥቅሉ ሲታይ ፖለቲካዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ተቋማዊ እንዲሁም የአመራር እና የአሰራር ሂደቶችን የሚመለከቱ ዘርፈ ብዙ እንደምታዎች ያሉት ቢሆንም በህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሲታይ ግን ከአስተዳደር ፍትህ ጋር አቻ ሆኖ ሊገለጽ ይችላል፡፡ መልካም አስተዳደር ዋና ግቡ ዜጐች ብቁና ውጤታማ አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል እንዲሁም የሚደርስባቸውን አስተዳደራዊ በደል መቅረፍ እና አስተዳደራዊ ፍትህን እውን ማድረግ እንደመሆኑ ሁለቱን ነጣጥሎ ማየት ያስቸግራል፡፡ መልካም አስተዳደር ሆነ የአስተዳደር ህግ በራሳቸው አቅጣጫና ሂደት ተጉዘው የግባቸው መድረሻ አስተዳደራዊ ፍትህን ማስፈን ነው፡፡ ስለሆነም በይዘቱ ሰፊ በሆነ የመልካም አስተዳደር እሳቤ ውስጥ የአስተዳደር ህግ አንድ ቁስ ሆኖ በማገልገል የተቆራኘና የተዛመደ ተግባራዊ እገዛ ያደርጋል፡፡ በመልካም አስተዳደርና በአስተዳደር ህግ መካከል ያለውን ተዛምዶ በቅጡ ለመቃኘት ህግ በአስተዳደሩ አካሄድ (Administrative behavior) ወይም በስራ አስፈፃሚው እንቅስቃሴ ላይ ምን አይነት አዎንታዊ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል? ለሚለው ጥያቄ በተግባር የታገዘ ጥልቅ ጥናት ምላሽ መስጠት ይጠይቃል፡፡ ይሁን እንጂ በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉትን ሚናዎችና ተግባራት ቢያንስ እንደጠቅላላ ሀሳብ በመውሰድ የአስተዳደር ህግ እንደ አንድ የህግ ዘርፍ የራሱ አዎንታዊ ፋይዳ እንዳለው መደምደም እንችላለን፡፡ ያም ሆኖ ግን አስተዳደሩ መልካም እንዲሆን የአስተዳደር ህግ ስልጣን ከመቆጣጠር ባሻገር እንዴት ተቃኝቶ መቀረጽ አለበት? የሚለው ጥያቄ ለአስተዳደር ህግ አጥኚዎች ሆነ ምሁራን የውይይት ምንጭ ብቻ ሳይሆን የጥናት መሰረት መሆን ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ የመልካም አስተዳደር እና የአስተዳደር ህግን ተዛምዶ ለማየት የሁለቱም መድረሻ ከሆነው የአስተዳደር ፍትህ ትርጓሜ እንነሳለን፡፡ የአስተዳደር ፍትህ በህግ ስልጣን የተሰጣቸው የመንግስት አካላት ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ወቅት ከዜጐች መብትና ነፃነት አንጻር ፍትሃዊ መሆን እንዳለባቸው የሚደነግግ መርህ ነው፡፡ የመንግስት አስተዳደር ፍትሃዊ ሲሆን መልካም ይሆናል፡፡ የአስተዳደር ፍትህን በማሳካት ረገድ ሁለት ዓበይት ነጥቦች ቁልፍ ቦታ ይኖራቸዋል፡፡ ይኸውም፡- አንደኛ፦ የመንግስት ባለ ስልጣናት ወይም የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ወቅት አነስተኛ ለሆኑ የስነ-ስርዓት ደንቦች እና ተቀባይነት ላላቸው መርሆዎች መገዛት አለባቸው፡፡ ከአነስተኛ የስነ-ስርዓት ደንቦች በተጨማሪ የመንግስት አስተዳደር ተቀባይነት ባላቸው የህግ፣ የአስተዳደርና የፍትህ መርሆዎች መመራት አለበት፡፡ ከእነዚህ መካከል በዋናነት የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ የህጋዊነት መርህ (ህጋዊ ስልጣን ሳይኖር አንዳችም እርምጃ አለመውሰድ፤ በህጉ መሰረት መወሰን) የሚዛናዊት መርህ (የአስተዳደር አካላት ውሳኔ ወይም እርምጃ እንደየሁኔታው ብዙ ነገሮች ግምት ያስገባ እንጂ ፍርደገምድል መሆን የለበትም፡፡) የተመጣጣኝነት መርህ (የሚወሰደው እርምጃ ተፈጸመ ከተባለው ጥፋት አንፃር ተመጣጣኝ መሆን አለበት፡፡) የእኩልነት መርህ (ተመሳሳይ በሆኑ ሁኔታዎች ወይም ጉዳዮች አስተዳደሩ የተለያየ ውሳኔ ላይ መድረስ የለበትም፡፡ ተመሳሳይ ሁኔታዎች በተመሳሳይ መንገድ መወሰን አለባቸው፡፡) ለውሳኔ በቂ ምክንያት መስጠት (አስተዳደራዊ ውሳኔ የተወሰደበት ምክንያት በግልጽ መጠቀስ አለበት፡፡ ውሳኔውም ፈጽሞ የማያሳምንና ኢ- ምክንያታዊ መሆን የለበትም፡፡) ሁለተኛ፦ ከላይ የተመለከቱትን ደንቦችና መርሆዎች በመጻረር በህግ ከተወሰነው ስልጣን በላይ እርምጃ ከተወሰደ መብታቸው የተጐዳ ዜጐች አቤቱታ አቅርበው ፍትህ (መፍትሄ) የሚያገኙበት መንገድ መኖር አለበት፡፡ በአስተዳደር አካላት መብታቸው የተጣሰ ሰዎች ቀላል በሆነ ስነ-ስርዓት አቤቱታ አቅርበው ቀልጣፋ መፍትሔ የሚያገኙበት አሰራር ወይም መንገድ ከሌለ የአስተዳደር ፍትህ አለ ለማለት አይቻልም፡፡ ለምሳሌ አካልን ነፃ የማውጣት መብት በህገ-ወጥ መንገድ ከ48 ሰዓት በላይ የታሰረ ሰው ራሱ በቀጥታ ወይም በሌላ ሶስተኛ ወገን በቀላሉ አቤቱታ አቅርቦ ነፃ የሚለቀቅበት ፈጣን ስነ-ስርዓት ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በህገ ወጥ መንገድ ንብረቱን በአስተዳደደሩ የተቀማ ወይም ፈቃዱ አለአግባብ የተሰረዘበት ሰው ቀላል በሆነ ስነ-ስርዓት መፍትሔ የሚያገኝበት የህግ ድንጋጌ ሊኖር ይገባል፡፡ ለዚህም ነው የአስተዳደር ህግ መኖር ለአስተዳደራዊ ፍትህ ሆነ ለመልካም አስተዳደር ወሳኝ መሳሪያ ነው የሚባለው፡፡ የአቤቱታው ስርዓት እንዳለ ሆኖ የአስተዳደራዊ ፍትህ የሚገኝበት ተቋም ገለልተኛ፣ ተደራሽ እና ነፃ ሆኖ ቀልጣፋና ውጤታማ ግልጋሎት መስጠት መቻሉ የአስተዳደር ፍትህን በማሳካት ረገድ ዋናውና መሰረታዊው ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡

አንቀጽ 10


የሕገመንግስቱ አንቀጽ 10፡ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች
1-➢ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች ከሰው ልጅ ተፈ ጥሮ የሚመነጩ፣
2-➢የማይጣሱና የማይገፈፉ ናቸው። የዜጐች እና የሕዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲ ያዊ መብቶች ይከበራሉ።

THE RULE OF LAW


The rule of law
What is the principle of the rule of law, based on the knowledge and experience of many scholars? He presented a number of theoretical analyzes regarding its content and benefits. In our country, fathers and mothers express the concept of the rule of law in one way or another, based on the truth written in their hearts and the knowledge they have learned from experience. “If she goes to court, my mule will go without justice!” The central message of this parable and parable is not just for a few people but for the whole community. And when a society that is well versed in this concept of the rule of law violates the law; When injustice is done, When rights are suppressed: When lawlessness reigns; Who spreads arbitrarily and arbitrarily; When the private chicken is snatched outside the law and justice, it shouts loudly; God of law! Says. The screaming chicken did not bother him. But the way she was taken. If in judgment, According to the law, even chickens and buffaloes are not allowed to eat. In public administration; Political Science; Scholars in the field of law and other fields of thought and understanding of the nature and content of the rule of law are so diverse that the concept has yet to be fully defined. As one scholar in the field reinforces this idea, ‘[T] he rule of law’, like ‘democracy’, has no single meaning: it is not a legal rule, but a moral principle, which means different things to different people according to their particular moral positions.a As a result, in the political and constitutional systems of different countries, the content and performance are different and sometimes inconsistent. In the UK, for example, one of the hallmarks of the rule of law is that disputes between the government and the individual are settled only by ordinary courts. That means there is no rule of law in France in the eyes of the English. Because in France, disputes between individuals and the government are adjudicated from beginning to end through an independent administrative court system parallel to the regular court. Another interpretation of the rule of law in the United Kingdom is that it is the result of decisions made by the formal courts on individual rights and freedoms. While this view is true in the United Kingdom, the rights and freedoms of citizens in countries such as the United States, including our own, are enshrined in the constitution. In addition, in a liberal democracy, the rule of law means more than just ruling and governing the rule of law (eg, fairness, respect for the rights of citizens, the rule of law by elected representatives, etc.) and independent and independent courts; Democratic Institutions: The existence of a free press, etc., is all part of the concept of the rule of law. In contrast, in liberal democracies, the concept of unbaptized governments (for example, in China) is limited to the rule of law. The rule of law is the basis on which administrative law (especially in the UK) is based. According to this principle, decisions made by the executive, administrative offices and governing councils must be in accordance with the law. Legal authority in government is vested in the government when it is established that the actions, actions, decisions, and directives of any government body are subject to the rule of law. If the decision of a government official is beyond the scope of the jurisdiction, the decision will undoubtedly violate the rule of law. Ensuring that legitimacy is upheld means that administrative actions, decisions, actions, rules and regulations are within the limits of the law. This is the function of ordinary courts. To minimize this practice, the legislature’s restriction on the jurisdiction of the courts undermines the rule of law. In addition to the threat to the rule of law, the restriction restricts citizens’ access to justice. In particular, if this right is constitutionally recognized, the power of the courts is limited, and in turn, the constitutional right of citizens is limited. It should be noted that the principle of the rule of law is not only the basis of administrative law but also the limit. Verifying the legitimacy of a decision results in saving on content. The courts’ role in upholding the rule of law prevents them from reviewing the content of administrative decisions or interfering with policy matters.

The assassination of Dr. Abiy Ahmed Ali by the tyrants and the attacks on civilians by the dictator Abiy Ahmed’s group. በአንባገነኖች የዶክተር የአብይ አህመድ አሊ በኢትዮጵያ ህዝብና ዜጎች ላይ አንባገነን መሪ በሆነው አብይ አህመድ ቡድኖች የተፈጸመው ግድያዎችና በሰላማዊ ዜጎች ላይ የደረሱበትን ጥቃቶች።


የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት አፈጻጸም።


የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት አፈፃፀም
ተደጋግሞ እንደተገለፀው የመንግስት ስልጣን በወርድም በቁመትም እየሰፋ በመጣ ቁጥር ለዜጐች መብትና ነፃነት ፀር ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ የስልጣንን አስፈላጊነት አምኖ ተቀብሎታል፡፡ ውጤታማ አስተዳደር እንዲሁም ቀልጣፋ የአገልግሎት አቅርቦት እንዲኖር የሚያስር ሳይሆን የሚፈታ ስልጣን ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም ከህግና ከህገ መንግስት የሚያፈነግጥ ስልጣን ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ የበዘፈቀደ ድርጊት፣ ‘እንደፈለግኩኝ እሆናለው እፈልጣለው እቆርጣለው!’ የሚል አካሄድ አቅመ ቢስ የሆነውን ዜጋ የመኖር፣ በነፃነት የመንቀሳቀስ፣ የመናገር፣ ሀሳብን የመግለፅና ንብረት የማፍራት መሰረታዊ መብት አለገደብ ይሸረሽራል፡፡ የአስተዳደር ህግ የሰብዓዊ መብትን በማስጠበቅ ረገድ ያለው ሚና የሁለቱን ትስስር በሚገባ ያሳየናል፡፡ ህጉ በሰብዓዊ መብት አጠባበቅና አፈፃፀም ላይ ያለውን አዎንታዊ ተፅእኖ በሚገባ ለመረዳት ከሰብዓዊ መብቶች አተገባበር አንፃር የመንግስትን ግዴታ መተንተኑ አግባብነት ይኖረዋል፡፡ እነዚህም ሚናዎች (ግዴታዎች) የማክበር (respect) የማስከበር (protect) እንዲሁም የመፈጸምና የማስፈፀም (enforcement) ናቸው፡፡ በመጀመሪያው መብቶችን የማክበር የመንግስት ሚና ዜጐች ነፃ ሆነው መብታቸውን ሲጠቀሙ ከየትኛውም የመንግስት አካል የሚመጣ ጣልቃ ገብነትን ይገድባል፡፡ በተለይም መሰረታዊ በሚባሉት በህይወት የመኖር፣ የመፃፍ፣ የመናገር፤ የፈለጉትን ሀይማኖት የመከተል፤ በነፃነት የመዘዋወርና ንብረት የማፍራት መብቶችና ነፃነቶች በተግባር የሚረጋገጡት መንግስት እጁን ሲሰበስብ ነው፡፡ እነዚህ መብቶች በመንግስት በተለይ በስራ አስፈፃሚውና በስሩ ባሉት የአስተዳደር ተቋማት ውሳኔ፤ ትዕዛዝ፤ ደንብና መመሪያ አማካይነት አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ፡፡ ህገ መንግስቱ የበላይ ህግ እንደመሆኑ ይህን የሚቃረን ህግ፣ ውሳኔና አሰራር ሁሉ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ይህን መሰሉ የህገ መንግስታዊነት ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ውስጥ አይወድቅም፡፡ ይሁን እንጂ የህገ መንግስታዊነት ብቻ የሚመስል ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ማእቀፍ የሚሸፈንበት አጋጣሚ ሰፊ ነው፡፡ በአንድ የአስተዳደር ተቋም የወጣ መመሪያ በህግ አውጭው ከተሰጠ የውክልና ስልጣን በማለፍ የዜጐችን ሰብዓዊ መብት የሚገድብ ሆኖ ከተገኘ በውስጡ የህገ መንግስታዊነት (constitutionality) ጥያቄ ያዘለ ቢሆንም በዋናነት ግን የአስተዳደር ህግ ሊመልሰው የሚገባ የህጋዊነት (legality) ጥያቄ ነው፡፡ ልዩነታቸውን የበለጠ መረዳት እንዲያስችልን የሚከተለውን የድሮው የገቢዎች ሚኒስቴር የአሁኑ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መመሪያ እንመልከት፡፡ ማንኛውም የጉምሩክ ፖሊስ ሰላማዊ ስልፍና የስራ ማቆም አድማ ማድረግ አይችልም፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ለማንኛውም ሰው የተረጋገጠ መብት ነው፡፡
መብቱን የሚያጎናጽፈው የአንቀጽ 30 ንዑስ ቁጥር 1 እንዲህ ይነበባል፡፡ ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነፃነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ አንድ መመሪያ በስራ አስፈፃሚው አካል ሲወጣ ከህግ አውጭው በግልጽ የተሰጠ የውክልና ስልጣን (Delegation) ሊኖር ይገባል፡፡
መመሪያው የውክልና ስልጣኑን ገደብ ካለፈ ከስልጣን በላይ (Ulta vires) ነው፡፡
ስለሆነም በህግ ፊት ዋጋ አልባ (null and void) ነው፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር ይህን መመሪያ ሲያወጣ የስልጣን ምንጩን የጉምሩክ ባለስልጣንን ለማቋቋምና አስራሩን ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁ. 368/1995 አንቀጽ 8 (2) (ሐ) እንደሆነ ይጠቅሳል፡፡ ይህ የተጠቀሰው የህግ ድንጋጌ እንዲህ ይነበባል፡፡ የጉምሩክ ህግ እንዲያስከብር ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የተመደበን የፖሊስ ኃይል ሚኒስቴሩ የፌደራል ፖሊስ አዋጅን ተከትሎ በሚያወጣው መመሪያ መሰረት በስራ ያሰማራል፡፡ ያስተዳድራል፡፡ ጥፋት ሲገኝም ያሰናብታል፡፡
ይህ አንቀጽ የጉምሩክ ፖሊስ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርግ በመመሪያ እንዲከለክል ለገቢዎች ሚኒስቴር ስልጣን አይሰጥም፡፡ ከተወካዮች ምክር ቤት ግልፅ ስልጣን ባልተሰጠበት ሁኔታ የወጣው ይህ መመሪያ ህጋዊነት ሆነ ተፈፃሚነት የለውም፡፡
የአስተዳደር ህግ ይህን መሰል መመሪያዎች በዘፈቀደ እየወጡ የዜጐችን መብትና ነፃነት እንዳይጥሱ በተለያዩ መንገዶች በመቆጣጠር መንግስት ሰብዓዊ መብት የማክበር ግዴታውን እንዲወጣ ያደርጋል፡፡
የመንግስት የማስፈፀም ኃላፊነት አብዛኛውን ጊዜ ከማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ መብቶች ጋር በቀጥታ ተያይዞ ይነሳል፡፡ መንግስት በዜጐች መብት ላይ ጣልቃ አለመግባቱ ወይም እጁን መሰብሰቡ ብቻ አይበቃም፡፡ ለዜጋው መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማለትም ጤና፣ መብራት፣ ውሃ፣ መንገድ ወዘተ… ካላቀረበ ነፃ መሆን በራሱ ፋይዳ የለውም፡፡ የአስተዳደር ህግ እና የሰብዓዊ መብት ትሰስር ከመንግስት የማስከበር ግዴታ አንጻርም ሊቃኝ ይችላል፡፡ ከዚህ አንጻር መንግስት ሰብዓዊ መብትን በማስከበር ኃላፊነቱ መብት እንዳይጣስ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶች በህግ እና በተቋማዊ አደረጃጀት የማጠናከር፣ በመብት መጣስ ጉዳት ለደረሰበት ዜጋ ፈጣን ፍትህ የሚያገኝበትን ስርዓት መዘርጋት አለበት ማለት ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ መንግስት የዳበረ የአስተዳደር ህግ እና የአስተዳደር ህግ ስርዓት መቅረጽ፣ መትከልና ማጐልበት ይጠበቅበታል፡፡

አንቀጽ 9፡ የሕገ መንግሥት የበላይነት/Article 9 Rule of the Constitution


Article 9 Rule of the Constitution

አንቀጽ 9፡ የሕገ መንግሥት የበላይነት/Article 9 Rule of the Constitution

1- The constitution is the supreme law of the land. Any law, customary practice, or decision of a government body or authority that is inconsistent with this Constitution shall not apply.

2. Every citizen, government body, political association, other associations and their officials shall have the responsibility to uphold the Constitution and abide by the Constitution.

3. It is prohibited to hold public office in any capacity other than that provided for in this Constitution.

4. The international conventions ratified by Ethiopia are part of the country’s law.

አንቀጽ 9፡ የሕገ መንግሥት የበላይነት

1- ሕገ መንግሥቱ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ ነው። ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣ እንዲ ሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለሥ ልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም።

2- ማንኛወም ዜጋ፣ የመንግሥት አካላት፣ የፖ ለቲካ ድርጅቶች፣ ሌሎች ማኅበራት እን ዲሁም ባለሥልጣኖቻቸው፣ ሕገ መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለባቸው።

3- በዚህ ሕገንግሥት ከተደነገገው ውጭ በማናቸውም አኳኋን የመንግሥት ሥልጣን መያዝ የተከለከለ ነው።

4- ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምም ነቶች የሀገሪቱ ሕግ አካል ናቸው።