
የሕገመንግስቱ ንቀጽ 50፡ ስለ ሥልጣን አካላት አወቃቀር
⚖️—–የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብ ሊክ በፌዴራል መንግሥትና በክልሎች የተዋቀረ ነው።
⚖️——የፌዴራሉ መንግሥትና ክልሎች የሕግ አውጪነት፣ የሕግ አስፈጻሚነትና የዳኝነት ሥልጣን አላቸው።
⚖️——–የፌዴራሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥልጣን አካል የፌዴራሉ መንግሥት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው። ተጠሪነቱየአንቀጽገሪቱ ሕዝብ ነው።
⚖️—–የክልል ከፍተኛ የሥልጣን አካል የክልሉ ምክር ቤት ነው፣ ተጠሪነቱም ለወከለው ክልል ሕዝብ ነው። ክልሎች፣ በክልልነትና ክልሎች አስፈላጊ ሆነው በሚያገኙአቸው የአስተዳደር እርከኖች ይዋቀራሉ። ሕዝቡ በዝቅተኛ የአስተዳደር እርከኖች በቀጥታ ይሳተፍ ዘንድ ለዝቅተኛ እርከኖች በቂ ሥልጣን ይሰጣል።
⚖️——–የክልል ምክር ቤት በክልሉ ሥልጣን ስር በሆኑ ጉዳዮች የክልሉ የሕግ አውጪ አካል ነው። ይህንን ሕገ መንግሥት መሰረት በማድረግ የክልሉን ሕገ መንግሥት ያዘጋጃል፣ ያጸድቃል፣ ያሻሽላል።
⚖️——– የክልል መስተዳድር የክልሉ ከፍተኛ የሕግ አስፈጻሚ አካል ነው።
⚖️⚖️⚖️——– የክልል የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ብቻ ነው።
⚖️⚖️⚖️ የፌዴራሉ መንግሥትና የክልሎች ሥልጣን በዚህ ሕገ መንግሥት ተወስኗል።
⚖️⚖️⚖️ለፌዴራሉ መንግሥት የተሰጠው ሥልጣን በክልሎች መከበር አለበት፡፤
ለክልሎች የተሰጠው ሥልጣን በፌዴራሉ መንግሥት መከበር አለበት።
⚖️⚖️ የፌዴራል መንግሥት በዚህ ሕገ መንግ ሥት አንቀጽ ፶1 ከተሰጡት ሥልጣን እና ተግባሮች እንደአስፈላጊነቱ ለክልሎች በውክልና ሊሰጥ ይችላል።
