የሕገመንግስቱ አንቀጽ 50


የሕገመንግስቱ ንቀጽ 50፡ ስለ ሥልጣን አካላት አወቃቀር

⚖️—–የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብ ሊክ በፌዴራል መንግሥትና በክልሎች የተዋቀረ ነው።

⚖️——የፌዴራሉ መንግሥትና ክልሎች የሕግ አውጪነት፣ የሕግ አስፈጻሚነትና የዳኝነት ሥልጣን አላቸው።

⚖️——–የፌዴራሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥልጣን አካል የፌዴራሉ መንግሥት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው። ተጠሪነቱየአንቀጽገሪቱ ሕዝብ ነው።

⚖️—–የክልል ከፍተኛ የሥልጣን አካል የክልሉ ምክር ቤት ነው፣ ተጠሪነቱም ለወከለው ክልል ሕዝብ ነው። ክልሎች፣ በክልልነትና ክልሎች አስፈላጊ ሆነው በሚያገኙአቸው የአስተዳደር እርከኖች ይዋቀራሉ። ሕዝቡ በዝቅተኛ የአስተዳደር እርከኖች በቀጥታ ይሳተፍ ዘንድ ለዝቅተኛ እርከኖች በቂ ሥልጣን ይሰጣል።

⚖️——–የክልል ምክር ቤት በክልሉ ሥልጣን ስር በሆኑ ጉዳዮች የክልሉ የሕግ አውጪ አካል ነው። ይህንን ሕገ መንግሥት መሰረት በማድረግ የክልሉን ሕገ መንግሥት ያዘጋጃል፣ ያጸድቃል፣ ያሻሽላል።

⚖️——– የክልል መስተዳድር የክልሉ ከፍተኛ የሕግ አስፈጻሚ አካል ነው።

⚖️⚖️⚖️——– የክልል የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ብቻ ነው።

⚖️⚖️⚖️ የፌዴራሉ መንግሥትና የክልሎች ሥልጣን በዚህ ሕገ መንግሥት ተወስኗል።

⚖️⚖️⚖️ለፌዴራሉ መንግሥት የተሰጠው ሥልጣን በክልሎች መከበር አለበት፡፤

ለክልሎች የተሰጠው ሥልጣን በፌዴራሉ መንግሥት መከበር አለበት።

⚖️⚖️ የፌዴራል መንግሥት በዚህ ሕገ መንግ ሥት አንቀጽ ፶1 ከተሰጡት ሥልጣን እና ተግባሮች እንደአስፈላጊነቱ ለክልሎች በውክልና ሊሰጥ ይችላል።

Leave a Reply

Please log in using one of these methods to post your comment:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.