የጋብቻ ምዝገባ


ስለጋብቻ ምዝገባ

 

አንቀጽ ፳፰ ጋብቻን ስለማስመዝገብ

 

፩. ጋብቻው የተፈፀመው በማንኛውም የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓት ቢሆንም፣ አግባብ ባለው የክብር መዝገብ ሹም መመዝገብ አለበት፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) መሠረት ምዝገባውን ያከናወነ የክብር መዝገብ ሹም ለተጋቢዎቹ የጋብቻ የምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡

፫. ማንኛውም ጋብቻ ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ ውጤት ይኖረዋል፡፡

 

አንቀጽ ፳፱ የጋብቻ መዝገብ ስለማደራጀት

 

፩. በዚህ ሕግ አንቀጽ ፳፰ ንዑስ አንቀጽ (፩) መሠረት ተጋቢዎች ጋብቻውን ያላስመዘገቡ ቢሆንም እንኳን፣ የክብር መዝገብ ሹሙ ጋብቻ መፈፀሙን ያወቀ እንደሆነ የጋብቻ መዝገብ በሥልጣኑ ያደራጃል፡፡

፪. ይህ በሚሆንበት ጊዜ የክብር መዝገብ ሹሙ ተጋቢዎቹና እንደ ነገሩ ሁኔታ ምስክሮች ቀርበው በጋብቻው መዝገብ ላይ እንዲፈርሙ ያደርጋል፡፡

 

አንቀጽ ፴ የጋብቻ መዝገብ ይዘት

 

የጋብቻ መዝገብ የሚያመለክተው፣

 

ሀ) የተጋቢዎችን ሙሉ ስም፣ የተወለዱበትን ቀንና ቦታ፣ የመኖሪያ አድራሻቸውን፣

ለ) የምስክሮችን ሙሉ ስም፣ የተወለዱበትን ቀንና ቦታ፣ የመኖሪያ አድራሻቸውን፣

ሐ) ጋብቻው የተፈፀመበትን ሥርዓት፣ ቀንና ቦታ እንዲሁም የተመዘገበበትን ቀን ይሆናል፡፡

Leave a Reply

Please log in using one of these methods to post your comment:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.