የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ
የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል የጥናትና ምርምር ስራ አንዱና ዋንኛው ነው፡፡ በመሆኑም ተቋማችን በፍትህ ሥርዓቱ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመለየት የህብረተሰቡን ወቅታዊ የፍትህ ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዱ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን በጥራትና በስፋት እያከናወነ ይገኛል፡፡፡
የፍትሕና የሕግ ሥርዓት ጥናትና ምርምር ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር የጥናትና ምርምር ስራዎችን ለመስራት የተደራጀ ሲሆን፣ በስሩ ሶስት ዳይሬክቶሬቶች የያዘና ተጠሪነቱም ለኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ሲሆን የሚከተሉት ተግባራት ያከናዉናል፡-
• ዳይሬክተሩ በሚሰጠው ውክልና መሠረት ዳይሬክተሩ ሳይኖር የሱን ሥራ ተክቶ ይሠራል፣
• የሕግና ፍትህ ምርምሩን የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅድ መርሃ ግብርና በጀት አዘጋጅቶ ለዳሬክተሩ ያቀርባል፣ሲፈቅድም በሥራ ላይ ያውላል፣
• የቢሮውን ተግባር ያቅዳል ፣በሥሩ የተደረጁትን ዲፓርትመንቶች ሥራ በበላይነት ይመራል፣ያስተባብራል፣ይቆጣጠራል፣
• የሚካሄደው ምርምርና በአገሪቷ ውስጥ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማትን ለማፋጠን በሚያስችል መልኩ እንዲነደፉ ያደርጋል፣
• የፐብሊክ ሕግ፣ የሲቪልሕግ እና የፍትሕ ሥርዓት ጥናት ጥናትና ምርምር ስራዎችን ማቀድ፣ ማስተባበር፣ መምራት እና መደገፍ፣
• የፍትሃብሄር ፍትህ፣ የወንጀል ፍትህ እና የአስተዳደር ፍትህ ተቋማት አፈጻጸም ከቅልጥፍና፣ ውጤታማነትና ተደራሽነት፣ ፍትሃዊነት፣ ምላሽ ሰጭነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት አንጻር የሚገኝበትን ሁኔታ በማጥናት አፈጻጸማቸውን ለማጠናከር የሚረዱ የማሻሻያ ሃሳቦችን ማቅረብ፤
• በሕግ ትምህርት እና ሥልጠና ሥርዓቱ ላይ ጥናት በማካሄድ በእውቀቱ፣ በክህሎቱ፣ በአመለካከቱ፣ እንዲሁም በሥነ ምግባሩ ብቁ የሆነ አመራር እና ባለሞያ ለማፍራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለማጠናከር የሚያግዙ ሃሳቦችን ማመንጨት፤
• የፍትህ ዘርፉ ለኪራይ ሰብሳቢነት ያለውን ተጋላጭነት በጥናት በመገምገም በዘርፉ ኪራይ ሰብሳቢነትን ለመከላከል የሚያግዙ የመፍትሄ ሃሳቦችን መጠቆም፤
• በባህላዊ የፍትህ ተቋማት እና በአሰራራቸው ላይ ጥናት በማካሄድ ከመደበኛው የፍትህ ሥርዓት ጋር ተጣጥመው ስራ ላይ እንዲውሉ ለማድረግ የሚረዱ ምክረ ሃሳቦችን ማቅረብ፤
• የፍትህ ሥርአቱን በሚመለከት የማማከር አገልግሎት መስጠት፣
• የፍትህ አካላትን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር የሚረዱ ስልቶች መለየት፤
• አስፈላጊ የሆኑ ጥናትና ምርምር ውጤቶችን እንዲታተሙና እንዲሰራጩ ውሳኔ ይሠጣል፣
• በሥሩ የሚገኙ የጥናትና ምርምር የስራ ክፍሎችን ጥረት ለማስተባበር፣ጥንካሬና ድክመቶቻቸውን ለመገምገምና በጋራም መፍትሄ ለመስጠት የስራ ክፍሎችን ስብሰባ ይመራል፣
• በስሩ ያሉ ዲፓርትመንቶችን ባለሙያዎች የሙያ ብቃታቸውን ለማዳበርና ከአዳዲስ ጽንሰ ሐሳቦች ጋር እንዲተዋወቁ አስፈላጊውን ሥልጠና እንዲያገኙ ያደርጋል፣
• የዲፓርትመንቶችን ውጤት ተኮር የዕቅድ አፈጻጸም ምዘና ያከናውናል፣
• በየዲፓርትመንቶቹ ያሉትን ሰራተኞች በ1 ለ 5 ማደራጀት ፣የውይይታቸውን ሪፖርት መከታተል እና በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄች በአሰራር መፍትሔ መስጠት፣
• ከየዲፓርትመንቶቹ የሚቀርቡትን የሕግ ጥናት እና ምርምሮች የሚገመግም የቴክኒክ ኮሚቴ ያዋቅራል ፣በበላይነት ስራውን ይቆጣጠራል፣
• ከየዲፓርትመንቶቹ የሚቀርቡትን የሕግ ጥናት እና ምርምሮች በአቻላቻ ግምገማ ፣በቴክኒክ ኮሚቴ እንዲገመገሙ ያደርጋል ፣ሂደቱ ይከታተላል፣
• በስሩ ያሉትን ዲፓርትመንቶች ሥራቸውን ስለሚያስተባብሩበት፣ስለሚያቀናጁበትና ስለሚያቀላጥፉበት መንገድ እያጠና ሃሣብ ያቀርባል፣
• አግባብ ካለቸው መሥሪያ ቤቶች(ባለድርሻ አካላት) ጋር በመገናኘት በጋራ ሲለሚሰሩ ጥናት እና ምርምሮች እንዲሁም የሥራ ልምድና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋል፣
የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ የተሰጠዉን ተግባራት ለማከናወን የሚከተለዉን መዋቅር ዘርግቷል፡-