Category Archives: የኢፌዴሪ ህገመንግስት

From the day Prime Minister Abiy Ahmed came to power, the slogan, politics or patriotism that Ethiopia has been saying will not fall apart?


From the day Prime Minister Abiy Ahmed came to power, the slogan, politics or patriotism that Ethiopia has been saying will not fall apart? Who said Ethiopia will be destroyed or Ethiopia will be destroyed? Why did Prime Minister Abiy Ahmed, with his tribute to Isaias Afewerki, repeatedly use slogans unless he himself had the intention of destroying Ethiopia? Apart from Eritrean President Isaias Afewerki, who wants Ethiopia to fall apart? In the absence of a party that wants to overthrow it, Prime Minister Abiy Ahmed. Why do they always shout “Ethiopia will not fall apart”? The Prime Minister says Ethiopia will not fall apart. It is not a scientific political analysis, but a mediation that tells us that Ethiopia will not fall apart like any other country because God protects it. Once the egg yolk is shed, it is useless. God, who created in His image and sacrificed His only begotten Son, killed innocent people who raped women with their soldiers and massacred innocent people, and killed innocent people on TV and radio. They are pretending to be believers and trying to deceive people. The fact that Ethiopia did not fall under the Italian invasion does not mean that Ethiopia will not fall apart. The slogan “Ethiopia will not fall” is determined by the hammer of the destroyer. There is no reason why Ethiopia should not fall apart, as the current negative and unhappy government is a corrupt government and a group of very fast-moving genocides. Ethiopia will collapse like any other country. This means that it cannot continue to be a country until it is in the hands of a murderous and murderous government. ጠ/ም አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡበት ቀን ጀምሮ ኢትዮጵያ አትፈርስም እያሉ የሚያሰሙን መፈክር፣ ፖለትካ ወይስ ሀገር ወዳድነት? ማንስ ኢትዮጵያ ትፍረስ ወይም ኢትዮጵያን እናፈርሳለን ብሎ ተናገረ? ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከግብራቸው ኢሳያስ አፈወርቅ ጋር ሆኖ እራሳቸው ኢትዮጵያን የማፍረስ አላማ ይኖሯቸው ካልሆነ በስተቀር ለምን ደጋግሞ መፈክር ማሰማታቸው ተፈለገ? ከኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ውጪ ማንስ ኢትዮጵያ እንዲትፈርስ ፈላጎት አለው? እንድትፈርስ ፍላጎት ያለው ተከራካሪ ወገን በሌለበት ሁኔታ፣ ጠቅላይ ሚንስቴር አብይ አህመድ። ሁልጊዜም ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚል መፈክር የሚያሰሙን ለምንድነው? እንግዲህ ጠቅላይ ሚንስቴሩ ኢትዮጵያ አትፈርስም  የኢትዮጵያ አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃታል፣ የሚሉት የኢትዮጵያ አምላክ ከሌሎች የተለየ ነው? የሚሉና እግዚአብሔር አብዝቶ ህዝቧንና ራሷን እንዲባርክ የሚማልዱላት ኢትዮጵያ ከሌሎች ሃገራት ሁሉ ተለይታ የማትፈርሰው እግዚአብሔር ስለሚጠብቃት እንደሆነ የሚነግሩን ሽምገላ እንጂ ሳይንሳዊ የፖለቲካ ትንተና አይደለም። አንድ እንቁላል አስኳሉ ከፈሰሰ በኋላ ጥቅም አይሰጥም። እግዚአብሔር በአምሳሉ የፈጠረውን እና አንድ ልጁን የሰዋለትን የሰው ልጅ እንዲገደል ትዕዛዝ እየሰጡ፣ በወታደሮቻቸው ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍሩ ንጹሃንን በእሳት የሚያቃጥሉና ህዝብን በቁም የምረሽን መንግሥት፣ ከዚያም አልፎ የንጹሃን ህይዎት ቀርጥፈው ገደልነው፣ ብሎም በቴሌቪዥን እና በራዲዮ ገደልናቸውገደልናቸው፣ ተደመሰሱ ብሎም ለህዝብ የሚነግሩ ሰዎች ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ይጠብቃል ኢትዮጵያ አትፈርስም ወዘተ፣ የሚሉት አማኝ መስሎ ህዝብን ለማታለል ነው። በጣልያንም ወረራ ኢትዮጵያ አልፈረሰችም ማለት ኢትዮጵያ አሁንም አትፈርስም ማለት አይደለም። ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚል መፈክርን ውሳኔ የሚወስነው አፍራሹ የያዘው መዶሻ ነው። የአሁኑ አፍራሽ ደግሞም የሰው ልጆች በህይወት መኖር ደስታ የማይሰጠው አፍራሽ መንግሥትና በጣም ፈጣን ሃገር አጥፊዎች ስብስብ ሹማምንት ስለሆነ ኢትዮጵያ የማትፈርስበት ምክንያት የለም። ኢትዮጵያ እንደማንኛውም ሃገር ትፈርሳለች። ይህ ማለትም ጨፍጫፊና ገዳይ መንግስት እጅ ውስጥ አስከካለች ድረስ ሃገር ሆና መቀጠል አትችልም።

Ibu lewat!** Ada hari-hari yang sepertinya berlalu! Tapi kami telah melihat mereka lulus! Kita mengira ada malam dan siang, tetapi tidak ada siang dan malam yang tidak datang. Tapi ada prosesnya! Hal Ethiopia adalah tangisan ibu-ibu ini: Air mata akan mengalir! Hari ini berakhir untuk Ethiopia! Tidak diingat tapi hanya tertawa! **Luka dan bekas luka tidak sama sakitnya! Bekas Luka Bisa Mengingatkan Anda! Tapi lukanya masih sakit! Tapi bekas luka yang ditinggalkan oleh luka ini menyakitkan, tapi masih ada. Mari kita berpikir seperti manusia hari ini! Sebagai manusia, mari kita menangis untuk orang Etiopia! Mari kita singkirkan luka ini hari ini agar tidak menjadi bekas luka!.*Tesfish from Toronto!


From the day Prime Minister Abiy Ahmed came to power, the slogan, politics or patriotism that Ethiopia has been saying will not fall apart?


From the day Prime Minister Abiy Ahmed came to power, the slogan, politics or patriotism that Ethiopia has been saying will not fall apart? Who said Ethiopia will be destroyed or Ethiopia will be destroyed? Why did Prime Minister Abiy Ahmed, with his tribute to Isaias Afewerki, repeatedly use slogans unless he himself had the intention of destroying Ethiopia? Apart from Eritrean President Isaias Afewerki, who wants Ethiopia to fall apart? In the absence of a party that wants to overthrow it, Prime Minister Abiy Ahmed. Why do they always shout “Ethiopia will not fall apart”? The Prime Minister says Ethiopia will not fall apart. It is not a scientific political analysis, but a mediation that tells us that Ethiopia will not fall apart like any other country because God protects it. Once the egg yolk is shed, it is useless. God, who created in His image and sacrificed His only begotten Son, killed innocent people who raped women with their soldiers and massacred innocent people, and killed innocent people on TV and radio. They are pretending to be believers and trying to deceive people. The fact that Ethiopia did not fall under the Italian invasion does not mean that Ethiopia will not fall apart. The slogan “Ethiopia will not fall” is determined by the hammer of the destroyer. There is no reason why Ethiopia should not fall apart, as the current negative and unhappy government is a corrupt government and a group of very fast-moving genocides. Ethiopia will collapse like any other country. This means that it cannot continue to be a country until it is in the hands of a murderous and murderous government. ጠ/ም አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡበት ቀን ጀምሮ ኢትዮጵያ አትፈርስም እያሉ የሚያሰሙን መፈክር፣ ፖለትካ ወይስ ሀገር ወዳድነት? ማንስ ኢትዮጵያ ትፍረስ ወይም ኢትዮጵያን እናፈርሳለን ብሎ ተናገረ? ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከግብራቸው ኢሳያስ አፈወርቅ ጋር ሆኖ እራሳቸው ኢትዮጵያን የማፍረስ አላማ ይኖሯቸው ካልሆነ በስተቀር ለምን ደጋግሞ መፈክር ማሰማታቸው ተፈለገ? ከኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ውጪ ማንስ ኢትዮጵያ እንዲትፈርስ ፈላጎት አለው? እንድትፈርስ ፍላጎት ያለው ተከራካሪ ወገን በሌለበት ሁኔታ፣ ጠቅላይ ሚንስቴር አብይ አህመድ። ሁልጊዜም ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚል መፈክር የሚያሰሙን ለምንድነው? እንግዲህ ጠቅላይ ሚንስቴሩ ኢትዮጵያ አትፈርስም  የኢትዮጵያ አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃታል፣ የሚሉት የኢትዮጵያ አምላክ ከሌሎች የተለየ ነው? የሚሉና እግዚአብሔር አብዝቶ ህዝቧንና ራሷን እንዲባርክ የሚማልዱላት ኢትዮጵያ ከሌሎች ሃገራት ሁሉ ተለይታ የማትፈርሰው እግዚአብሔር ስለሚጠብቃት እንደሆነ የሚነግሩን ሽምገላ እንጂ ሳይንሳዊ የፖለቲካ ትንተና አይደለም። አንድ እንቁላል አስኳሉ ከፈሰሰ በኋላ ጥቅም አይሰጥም። እግዚአብሔር በአምሳሉ የፈጠረውን እና አንድ ልጁን የሰዋለትን የሰው ልጅ እንዲገደል ትዕዛዝ እየሰጡ፣ በወታደሮቻቸው ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍሩ ንጹሃንን በእሳት የሚያቃጥሉና ህዝብን በቁም የምረሽን መንግሥት፣ ከዚያም አልፎ የንጹሃን ህይዎት ቀርጥፈው ገደልነው፣ ብሎም በቴሌቪዥን እና በራዲዮ ገደልናቸውገደልናቸው፣ ተደመሰሱ ብሎም ለህዝብ የሚነግሩ ሰዎች ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ይጠብቃል ኢትዮጵያ አትፈርስም ወዘተ፣ የሚሉት አማኝ መስሎ ህዝብን ለማታለል ነው። በጣልያንም ወረራ ኢትዮጵያ አልፈረሰችም ማለት ኢትዮጵያ አሁንም አትፈርስም ማለት አይደለም። ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚል መፈክርን ውሳኔ የሚወስነው አፍራሹ የያዘው መዶሻ ነው። የአሁኑ አፍራሽ ደግሞም የሰው ልጆች በህይወት መኖር ደስታ የማይሰጠው አፍራሽ መንግሥትና በጣም ፈጣን ሃገር አጥፊዎች ስብስብ ሹማምንት ስለሆነ ኢትዮጵያ የማትፈርስበት ምክንያት የለም። ኢትዮጵያ እንደማንኛውም ሃገር ትፈርሳለች። ይህ ማለትም ጨፍጫፊና ገዳይ መንግስት እጅ ውስጥ አስከካለች ድረስ ሃገር ሆና መቀጠል አትችልም።

በሀረሪ ሕዝብ ክልል መንግስት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ እና በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ መካከል የምርጫ ጉዳይን አስመልክቶ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 207036 የሰጠው ውሳኔየሀረሪ ሕዝብ ክልል መንግሥት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ከክልሉ ውጭ የሚኖር የሐረሪ ሕዝብ ከዚህ ቀደም እንደነበሩት አምስት አገራዊ ምርጫዎች በ6ኛው አገራዊ ምርጫም ከክልሉ ዉጭ ያሉ የብሔረሰቡ አባላት ለሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ሊመርጡ ይገባል በሚል ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አቤቱታ ያቀረበ ቢሆንም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ጉዳዩን ማስተናገድ እንደማይቻል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡የሀረሪ ሕዝብ ክልል መንግሥት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ምርጫ ቦርዱ የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም የይግባኝ ቅሬታውን ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቅርቧል፡፡ የፍርድ ቤቱ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 205809 ሚያዚያ 19 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት የምርጫ ቦርድ በጉዳዩ ላይ የሰጠውን ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ቦርዱ ከክልሉ ውጪ ያሉ ሐረሪዎች የመምረጥ መብትን አስቀድሞ በተዘረጋው ስርዓት መሰረት ተግባራዊ እንዲያደርግ ወስኗል፡፡በዚህ ውሳኔ ቅር የተሰኘው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይግባኝ ችሎቱ የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ጉዳዩን ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበ ቢሆንም የሰበር አቤቱታውን የተመለከተው የፍርድ ቤቱ ሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 207036 ግንቦት 19 ቀን 2013 ዓ.ም ጉዳዩን በጥልቀት ከመረመረ በኋላ በሰጠው ውሳኔ የይግባኝ ሰሚ ችሎቱ የሰጠውን ወሳኔ አጽንቷል፡፡


Supreme Court Cassation Hearing Case No. 207036 on Election Issue between the Harari National Regional State Government and the Electoral Board of Ethiopia

Harari National Regional State Harari National Assembly The Ethiopian Electoral Board of Ethiopia (NEBE) has ruled that the Harari National Assembly, which has been living outside the region, has appealed to the Electoral Board of Ethiopia (NEBE).
The Harari People’s State Government has appealed to the Federal Supreme Court against the decision of the Harari National Assembly. The Court of Appeals rejected the decision of the Electoral Board in the case number 205809 on April 19, 2013 and decided that the Board should exercise the right to vote for Hararis outside the region in accordance with the established system.
Dissatisfied with this decision, the National Electoral Board of Ethiopia (NBE) appealed to the Federal Supreme Court, citing a fundamental error of law. The appellate court upheld the decision.

በሀረሪ ሕዝብ ክልል መንግስት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ እና በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ መካከል የምርጫ ጉዳይን አስመልክቶ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 207036 የሰጠው ውሳኔ
*************************
የሀረሪ ሕዝብ ክልል መንግሥት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ከክልሉ ውጭ የሚኖር የሐረሪ ሕዝብ ከዚህ ቀደም እንደነበሩት አምስት አገራዊ ምርጫዎች በ6ኛው አገራዊ ምርጫም ከክልሉ ዉጭ ያሉ የብሔረሰቡ አባላት ለሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ሊመርጡ ይገባል በሚል ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አቤቱታ ያቀረበ ቢሆንም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ጉዳዩን ማስተናገድ እንደማይቻል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

የሀረሪ ሕዝብ ክልል መንግሥት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ምርጫ ቦርዱ የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም የይግባኝ ቅሬታውን ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቅርቧል፡፡ የፍርድ ቤቱ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 205809 ሚያዚያ 19 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት የምርጫ ቦርድ በጉዳዩ ላይ የሰጠውን ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ቦርዱ ከክልሉ ውጪ ያሉ ሐረሪዎች የመምረጥ መብትን አስቀድሞ በተዘረጋው ስርዓት መሰረት ተግባራዊ እንዲያደርግ ወስኗል፡፡
 
በዚህ ውሳኔ ቅር የተሰኘው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይግባኝ ችሎቱ የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት ጉዳዩን ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበ ቢሆንም የሰበር አቤቱታውን የተመለከተው የፍርድ ቤቱ ሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 207036 ግንቦት 19 ቀን 2013 ዓ.ም ጉዳዩን በጥልቀት ከመረመረ በኋላ በሰጠው ውሳኔ የይግባኝ ሰሚ ችሎቱ የሰጠውን ወሳኔ አጽንቷል፡፡

Supreme Court Cassation Hearing Case No. 207036 on Election Issue between the Harari National Regional State Government and the Electoral Board of Ethiopia

Harari National Regional State Harari National Assembly The Ethiopian Electoral Board of Ethiopia (NEBE) has ruled that the Harari National Assembly, which has been living outside the region, has appealed to the Electoral Board of Ethiopia (NEBE).
The Harari People’s State Government has appealed to the Federal Supreme Court against the decision of the Harari National Assembly. The Court of Appeals rejected the decision of the Electoral Board in the case number 205809 on April 19, 2013 and decided that the Board should exercise the right to vote for Hararis outside the region in accordance with the established system.
Dissatisfied with this decision, the National Electoral Board of Ethiopia (NBE) appealed to the Federal Supreme Court, citing a fundamental error of law. The appellate court upheld the decision.

The solution is to face the bitter truth!………………………………………….. ..It is the historic responsibility of this generation to abandon the “generation” that claims to be dead if we do not burn the American flag. To do this, we must first evict all forces that violated Ethiopia’s sovereignty and ensure that we do not need any interference. Next you need to look inside and close your home in a polite manner. The world is solving the problem through dialogue, negotiation, and acceptance, not by making excuses and by fighting.Failure to do so is a second death, especially for my generation!


The solution is to face the bitter truth!
………………………………………….. ..
It is the historic responsibility of this generation to abandon the “generation” that claims to be dead if we do not burn the American flag. To do this, we must first evict all forces that violated Ethiopia’s sovereignty and ensure that we do not need any interference. Next you need to look inside and close your home in a polite manner. The world is solving the problem through dialogue, negotiation, and acceptance, not by making excuses and by fighting.
Failure to do so is a second death, especially for my generation!

Basic Rules of International Humanitarian Law in Armed ConflictsThe seven fundamental rules which are the basis of the Geneva Conventions and the Additional Protocols:


Basic Rules of International Humanitarian Law in Armed Conflicts
The seven fundamental rules which are the basis of the Geneva Conventions and the Additional Protocols:
1 – Persons hors de combat and those who do not take a direct part in hostilities are entitled to respect for their lives and their moral and physical integrity. They shall in all circumstances be protected and treated humanely without any adverse distinction.
2 – It is forbidden to kill or injure an enemy who surrenders or who is hors de combat.
3 – The wounded and sick shall be collected and cared for by the party to the conflict which has them in its power. Protection also covers medical personnel, establishments, transports and equipment. The emblem of the red
cross or the red crescent is the sign of such protection and must be respected.
4 – Captured combatants and civilians under the authority of an adverse party are entitled to respect for their lives, dignity, personal rights and convictions. They shall be protected against all acts of violence and reprisals. They shall have the right to correspond with their families and to receive relief.
5 – Everyone shall be entitled to benefit from fundamental judicial guarantees. No one shall be held responsible for an act he has not committed. No one shall be subjected to physical or mental torture, corporal punishment or cruel or degrading treatment.
6 – Parties to a conflict and members of their armed forces do not have an unlimited choice of methods and means of warfare. It is prohibited to employ weapons or methods of warfare of a nature to cause unnecessary losses or excessive suffering.
7 – Parties to a conflict shall at all times distinguish between the civilian population and combatants in order to spare civilian population and property. Neither the civilian population as such nor civilian persons shall be the object of attack. Attacks shall be directed solely against military objectives.

የተባበሩት መንግስት


የተዋሃዱ ግዛቶች ሴናት
ዋርጎ ኦ.ሲ 2610
29 ኤፕሪል 2021

አምባሳደር ጄፍሪ ፌልማን
አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 2201 C St NW
ዋሽንግተን ዲሲ 20520
አምባሳደር ፌልማን


ለአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ የስፔስ መልዕክተኛ ሆነው በመሾምዎ እንኳን ደስ አላችሁ ፡፡ ብዙ ውስብስብ ችግሮች ያጋጠሙት ወሳኝ ወሳኝ ክልል ነው ፡፡ የእርስዎ ተሞክሮ እና አመራር ዩናይትድ ስቴትስ በስትራቴጂክ ፣ በተቀናጀ ሁኔታ ምላሽ እንድትሰጥ ያስችላታል ፡፡
ወደ አከባቢው ለመጓዝ ሲዘጋጁ ግምት ውስጥ ያስገባሉ ብለን የምንጠብቃቸውን በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ባሉና እርስ በርሳቸው በሚተሳሰሩ ቀውሶች ላይ ያለንን አመለካከት ለማካፈል እንፅፋለን ፡፡ ከኖቬምበር 2020 ጀምሮ በትግራይ ክልል በተፈጠረው ግጭት በሰብአዊ እና በሰብአዊ መብቶች ማጎሳቆሎች ሁላችንም የተረበሸን ነን ፣ በግምት ወደ 1.7 ሚሊዮን ከሚሆኑት የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተጨማሪ 62,000 ሰዎች እንደ መጠለያ ለመሸሽ ተገደዋል ፣ እና 4.5 ሚሊዮን አስቸኳይ ምግብ ያስፈልጋቸዋል በጾታ እና በጾታ ላይ የተመሠረተ ጥቃት በስፋት ጥቅም ላይ መዋልን ጨምሮ በፀጥታ ኃይሎች በሰላማዊ ዜጎች ላይ በፈጸሙት ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እርዳታ በርካታ ተዓማኒ ሪፖርቶች ተገኝተዋል ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ / ር) የኤርትራ እና የክልል ያልሆኑ ወታደሮች ከትግራይ እንዲወጡ ደህንነቱ ያልተጠበቀ የሰብአዊ አቅርቦትን ወደ ክልሉ ለማቅረብ የገቡትን ቃል እንዲፈጽሙ ሁሉንም የዲፕሎማቲክ መሳሪያዎች እንዲጠቀሙ እናበረታታዎታለን ፡፡ በሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ ገለልተኛ ምርመራዎችን ለመፍቀድ እና አጥቂዎችን ተጠያቂ ለማድረግ ፡፡ እነዚህ አስቸኳይ እርምጃዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የርሃብ አደጋ ለመግታት እና በመላው አገሪቱ በሲቪል ዜጎች ላይ የሚደርሰውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ለማስቆም ወሳኝ ናቸው ፡፡
በተመሳሳይ ጊዜ እኛ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚከሰቱ የጎሳ ጥቃቶች መበራከትንም በተመለከተ በጣም ተቀናጅተናል ፡፡ ለካምፕል እ.ኤ.አ. በታህሳስ 2020 በቤኒሻንጉል-ግሩሙዝ ክልል በምስራቅ 200 አማራ ፣ ኦሮሞ ፣ ሺናሳ ፣ አገው እና ሌሎች አናሳ አናሳዎች በአጥቂዎች ተገደሉ ፡፡ ተመሳሳይ ጥቃቶች በኦሮምያ ክልል ውስጥ ከተነሱበት ጊዜ አንስቶም እንዲሁ ፡፡ it ts cstimatcd ነው
ቤሽር ኤም (2021, ኤፕሪል 15). የተባበሩት መንግስታት በኤክስሂያ ትግራዋይ ውስጥ ረሃብ እና አስገድዶ መድፈር እየጨመረ መጥቷል ፡፡ የአሜሪካ አይጥ ተሰርvedል ከ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበር. (2021. ኤፕሪል 27) ፣ ኢትዮጵያ-ታይጋይ ክልል
ሂሚኒታንሳን Updatc. የተወሰደ ትሮም ሊቲንኮርቲ.ኑናታ.ኢግ ncuntcthaopia
ክላርክ ፣ ኤች እና ኪቴ ፣ አር (2021. ኤፕሪል 27) ፡፡ በቲጅጊ ፣ ወሲባዊ ጥቃት l የጦር መሣሪያ ሆነ ፡፡ የፋርኪንግ ፖሊሲ.
ዳግም የተሰጠው ትሮም bttpsorsignpolicy.soma0REDHAZmeluray-exual-slikncelas-becencH -0ENar
የታጠቀ ቡድን በምዕራብ ምዕራብ ኢትዮጵያ አውራጃን ተቆጣጠረ – የመብቶች ኮሚሽን (202l ፣ ኤፕሪል 23) ሮይተርስ ፡፡ የተወሰደ trom ittpsAWISMcrs.com.waratoca.cbiopta-tightassonnssR-S-arncd-team-lasetakcn-controlscounty
አምነስቲ ኢንቴማዊ (እ.ኤ.አ. 2020 ፣ ኖቬምበር 2) ፡፡ የታጠቁ ቡድን ጎሳ አማራዎችን በመግደል መንደሮች ላይ ጥቃት ሰነዘረባቸው ፣ ቤቶችን አጥፍቷል ተሰርስሮ የተወሰደ tID htpsww.IDcsty.onun.latcs.ncSO0LL12cthopsasoxcEM-chnksnhata: killkd-in attackoon: Slagcetraclgloa

United States ሴኔት የመንግሥት ተዋንያን በመላ አገሪቱ እና በእውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ምርጫዎች መሠረት ለመጣል ፡፡
በረጅም ጊዜ ውስጥ በኦሮሚያ ፣ በአማራ ፣ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ፣ በትግራይና በሌሎችም ክልሎች የተፈጸሙ የሰብአዊ ንቅናቄዎች በደሎችን በተመለከተ ገለልተኛ ምርመራን እንደሚደግፉ ተስፋ እናደርጋለን ፡፡ እንዲሁም ለኢትዮጵያ የተረጋጋ ፣ የተስማማ እና ሁሉን አቀፍ አካታችነት ለመቅረጽ ሁሉንም የአገሪቱን ብሄረሰቦች እና የፖለቲካ ቡድኖችን የሚያሰባስብ ብሔራዊ ውይይት ሂደት እንዲያስተዋውቁ እናበረታታዎታለን ፡፡
ኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ ለአሜሪካ አስፈላጊ አጋር ሆና በሰፊ ምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ውስጥ ጉልህ ሚና ትጫወታለች ፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ የሚከሰቱ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን መፍታት ለኢትዮጵያ ፣ ለአሜሪካ እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፍላጎት ነው ፡፡
እንደ ሪያልታን የኢትዮ Ethiopiaያ ሬናስንስን አሠራር በመሳሰሉ በኢትዮጵያ እና በጎረቤቶ between መካከል እየጨመረ ላለው ውጥረት ነጥቦች በሰላማዊ ፣ በድርድር መፍትሄዎችን ማበረታታት አለብን ፡፡
ግድብ ከእነዚህ ተፈታታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አንዳቸውም በተናጥል ሊስተናገዱ አይችሉም ፣ የእነዚህን ቀውሶች እርስ በእርስ የመተያየት ተፈጥሮን ወደኋላ የምንመልስ አጠቃላይ ስትራቴጂዎችን እንቀጥላለን ፡፡ እነዚያን ስትራቴጂዎች እንዲያዳብሩ እና እንዲያስፈጽሙ ለመርዳት ዝግጁ ነን ፣ እናም የሰውን ልጅ ንፅህናን ፣ ዲሞክራሲን እና ብልጽግናን በኢትዮ andያ እና በመላው አፍሪካ ሆርሞን ለማራመድ ከእርስዎ ጋር አብሮ ለመስራት በጉጉት እንጠብቃለን ፡፡
ከሠላምታ ጋር
ቤንጃንት ኤል ካርዲን
የዩናይትድ ስቴትስ ሴናተር
ቲም ካይንክ
የዩናይትድ ስቴትስ ሴናተር
ጃኪ ሮዜ
የዩናይትድ ስቴትስ ሴናተር
ኮሪ ኤ ቡከር
የዩናይትድ ስቴትስ ሴናተር
ኤድዋርድ J. Markčy
የዩናይትድ ስቴትስ ሴናተር

አቶ ልደቱ አያሌውን ከሃገር ወጥቶ እንዲታከሙ የመፍቀድ ግዴታ አለበት። የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ አራዳ የጸረ ሽብር ወንጀል ችሎት በዛሬው እለት የሰጠው ውሳኔ ተፈጻሚ ሆኖ አቶ ልደቱ አያሌውን ይቅርታ በመጠየቅ የችሎቱን ትዕዛዝ እንዲፈጽሙ እንመኛለን።


መንግስት ፖለቲከኞችን ባልፈጸሙት ወንጀል አሸባሪ ነው ሃገርን አውኳል , ወይም አተራምሷል በማለት በየግዜው ዜጎች በሆኑት ፖለቲከኞች ላይ በሀሰተኛ ክስ የማስተጓገል,የማደናቀፍ,እንዲሁም በፖለቲከኞች ላይ የስነልቦና ጫና መፍጠር በዚህ በቅርብ ዘመናት ዋንኛው የመንግሥት ተግባር መሆኑ ይታወቃል። እደግመዋለሁ አዎን የትግራይን ጦርነት የንጹሃንን ትግራይን የህዝብ እልቂት, የሴቶችን መደፈር,ትክክል አይደለም ብሎ መቃወም ወንጀለኛ አያስብልም። የዜጎችን መብት መጣስ/የዜጎችን መብት መንፈግ ዋንኛው የመንግሥት መደበኛ የስራ አፈጻጸም ሆኗል። መንግስት የዜጎችን መብት እየነፈገ ወንጀለኛ ሆኖስአለ ምንም አይነት ህግን የማስከበር ፍላጎትም ሞራልም እንደሌለው እራሱን ልያውቅ ይገባል። አሁንም በአስቸኳይ
#አቶ ልደቱ አያሌውን ከሃገር ወጥቶ እንዲታከሙ የመፍቀድ ግዴታ አለበት። የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ አራዳ የጸረ ሽብር ወንጀል ችሎት በዛሬው እለት የሰጠው ውሳኔ ተፈጻሚ ሆኖ አቶ ልደቱ አያሌውን ይቅርታ በመጠየቅ የችሎቱን ትዕዛዝ እንዲፈጽሙ እንመኛለን።

In recent years, the government has been known to harass, intimidate, and exert political pressure on politicians by claiming that the government is a terrorist who has disturbed the country, or that it has disturbed the country.  I repeat, yes, the war in Tigray is not a crime to oppose the massacre of innocent Tigray, the rape of women.  Violation of civil rights / denial of civil rights has become a major function of government.  The government should be aware that it has no interest in enforcing the law and has no interest in enforcing the law.  Still urgently
# Mr. Lidetu is obliged to allow Ayale to leave the country for treatment.  We apologize to Lidetu Ayalew for complying with the decision of the Federal Court of First Instance’s Arada Anti-Terrorism Tribunal today.

YE ABESHA MEDHANIT Facebook page. I listened to a woman who is an activist and she is an amazing woman. I couldn’t help but admire her. This brilliant, beautiful and good activist is brilliant and her thinking as a girl is amazing. The sincerity of her heart is evident. This beautiful, decent woman is sharing all her thoughts and knowledge with us in a very balanced and unbiased way. It is incumbent upon all of us to encourage and support such courageous and positive women as role models for other women.


YE ABESHA MEDHANIT Facebook page. I listened to a woman who is an activist and she is an amazing woman. I couldn’t help but admire her. This brilliant, beautiful and good activist is brilliant and her thinking as a girl is amazing. The sincerity of her heart is evident. This beautiful, decent woman is sharing all her thoughts and knowledge with us in a very balanced and unbiased way. It is incumbent upon all of us to encourage and support such courageous and positive women as role models for other women.

Basic Rules of International Humanitarian Law in Armed Conflicts


Basic Rules of International Humanitarian Law in Armed Conflicts

The seven fundamental rules which are the basis of the Geneva Conventions and the Additional Protocols:

1 – Persons hors de combat and those who do not take a direct part in hostilities are entitled to respect for their lives and their moral and physical integrity. They shall in all circumstances be protected and treated humanely without any adverse distinction.

2 – It is forbidden to kill or injure an enemy who surrenders or who is hors de combat.

3 – The wounded and sick shall be collected and cared for by the party to the conflict which has them in its power. Protection also covers medical personnel, establishments, transports and equipment. The emblem of the red
cross or the red crescent is the sign of such protection and must be respected.

4 – Captured combatants and civilians under the authority of an adverse party are entitled to respect for their lives, dignity, personal rights and convictions. They shall be protected against all acts of violence and reprisals. They shall have the right to correspond with their families and to receive relief.

5 – Everyone shall be entitled to benefit from fundamental judicial guarantees. No one shall be held responsible for an act he has not committed. No one shall be subjected to physical or mental torture, corporal punishment or cruel or degrading treatment.

6 – Parties to a conflict and members of their armed forces do not have an unlimited choice of methods and means of warfare. It is prohibited to employ weapons or methods of warfare of a nature to cause unnecessary losses or excessive suffering.

7 – Parties to a conflict shall at all times distinguish between the civilian population and combatants in order to spare civilian population and property. Neither the civilian population as such nor civilian persons shall be the object of attack. Attacks shall be directed solely against military objectives.

What are the 3 types of dictatorships?


What are the 3 types of dictatorships?

Between the two world wars, three types of dictatorships have been described: constitutional, counterrevolutionary and fascist. Since World War II, a broader range of dictatorships has been recognized, including Third World dictatorships, theocratic or religious dictatorships and dynastic or family-based dictatorships.

Characteristics. Authoritarianism is characterized by highly concentrated and centralized government power maintained by political repression and the exclusion of potential challengers. It uses political parties and mass organizations to mobilize people around the goals of the regime.

Dictatorships are often characterised by some of the following: suspension of elections and civil liberties; proclamation of a state of emergency; rule by decree; repression of political opponents; not abiding by the rule of law procedures, and cult of personality.

የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ


የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ

የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል የጥናትና ምርምር ስራ አንዱና ዋንኛው ነው፡፡ በመሆኑም ተቋማችን በፍትህ ሥርዓቱ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመለየት የህብረተሰቡን ወቅታዊ የፍትህ ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዱ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን በጥራትና በስፋት እያከናወነ ይገኛል፡፡፡
የፍትሕና የሕግ ሥርዓት ጥናትና ምርምር ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር የጥናትና ምርምር ስራዎችን ለመስራት የተደራጀ ሲሆን፣ በስሩ ሶስት ዳይሬክቶሬቶች የያዘና ተጠሪነቱም ለኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ሲሆን የሚከተሉት ተግባራት ያከናዉናል፡-
• ዳይሬክተሩ በሚሰጠው ውክልና መሠረት ዳይሬክተሩ ሳይኖር የሱን ሥራ ተክቶ ይሠራል፣
• የሕግና ፍትህ ምርምሩን የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅድ መርሃ ግብርና በጀት አዘጋጅቶ ለዳሬክተሩ ያቀርባል፣ሲፈቅድም በሥራ ላይ ያውላል፣
• የቢሮውን ተግባር ያቅዳል ፣በሥሩ የተደረጁትን ዲፓርትመንቶች ሥራ በበላይነት ይመራል፣ያስተባብራል፣ይቆጣጠራል፣
• የሚካሄደው ምርምርና በአገሪቷ ውስጥ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማትን ለማፋጠን በሚያስችል መልኩ እንዲነደፉ ያደርጋል፣
• የፐብሊክ ሕግ፣ የሲቪልሕግ እና የፍትሕ ሥርዓት ጥናት ጥናትና ምርምር ስራዎችን ማቀድ፣ ማስተባበር፣ መምራት እና መደገፍ፣
• የፍትሃብሄር ፍትህ፣ የወንጀል ፍትህ እና የአስተዳደር ፍትህ ተቋማት አፈጻጸም ከቅልጥፍና፣ ውጤታማነትና ተደራሽነት፣ ፍትሃዊነት፣ ምላሽ ሰጭነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት አንጻር የሚገኝበትን ሁኔታ በማጥናት አፈጻጸማቸውን ለማጠናከር የሚረዱ የማሻሻያ ሃሳቦችን ማቅረብ፤
• በሕግ ትምህርት እና ሥልጠና ሥርዓቱ ላይ ጥናት በማካሄድ በእውቀቱ፣ በክህሎቱ፣ በአመለካከቱ፣ እንዲሁም በሥነ ምግባሩ ብቁ የሆነ አመራር እና ባለሞያ ለማፍራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለማጠናከር የሚያግዙ ሃሳቦችን ማመንጨት፤
• የፍትህ ዘርፉ ለኪራይ ሰብሳቢነት ያለውን ተጋላጭነት በጥናት በመገምገም በዘርፉ ኪራይ ሰብሳቢነትን ለመከላከል የሚያግዙ የመፍትሄ ሃሳቦችን መጠቆም፤
• በባህላዊ የፍትህ ተቋማት እና በአሰራራቸው ላይ ጥናት በማካሄድ ከመደበኛው የፍትህ ሥርዓት ጋር ተጣጥመው ስራ ላይ እንዲውሉ ለማድረግ የሚረዱ ምክረ ሃሳቦችን ማቅረብ፤
• የፍትህ ሥርአቱን በሚመለከት የማማከር አገልግሎት መስጠት፣
• የፍትህ አካላትን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር የሚረዱ ስልቶች መለየት፤
• አስፈላጊ የሆኑ ጥናትና ምርምር ውጤቶችን እንዲታተሙና እንዲሰራጩ ውሳኔ ይሠጣል፣
• በሥሩ የሚገኙ የጥናትና ምርምር የስራ ክፍሎችን ጥረት ለማስተባበር፣ጥንካሬና ድክመቶቻቸውን ለመገምገምና በጋራም መፍትሄ ለመስጠት የስራ ክፍሎችን ስብሰባ ይመራል፣
• በስሩ ያሉ ዲፓርትመንቶችን ባለሙያዎች የሙያ ብቃታቸውን ለማዳበርና ከአዳዲስ ጽንሰ ሐሳቦች ጋር እንዲተዋወቁ አስፈላጊውን ሥልጠና እንዲያገኙ ያደርጋል፣
• የዲፓርትመንቶችን ውጤት ተኮር የዕቅድ አፈጻጸም ምዘና ያከናውናል፣
• በየዲፓርትመንቶቹ ያሉትን ሰራተኞች በ1 ለ 5 ማደራጀት ፣የውይይታቸውን ሪፖርት መከታተል እና በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄች በአሰራር መፍትሔ መስጠት፣
• ከየዲፓርትመንቶቹ የሚቀርቡትን የሕግ ጥናት እና ምርምሮች የሚገመግም የቴክኒክ ኮሚቴ ያዋቅራል ፣በበላይነት ስራውን ይቆጣጠራል፣
• ከየዲፓርትመንቶቹ የሚቀርቡትን የሕግ ጥናት እና ምርምሮች በአቻላቻ ግምገማ ፣በቴክኒክ ኮሚቴ እንዲገመገሙ ያደርጋል ፣ሂደቱ ይከታተላል፣
• በስሩ ያሉትን ዲፓርትመንቶች ሥራቸውን ስለሚያስተባብሩበት፣ስለሚያቀናጁበትና ስለሚያቀላጥፉበት መንገድ እያጠና ሃሣብ ያቀርባል፣
• አግባብ ካለቸው መሥሪያ ቤቶች(ባለድርሻ አካላት) ጋር በመገናኘት በጋራ ሲለሚሰሩ ጥናት እና ምርምሮች እንዲሁም የሥራ ልምድና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋል፣
የፍትህና የህግ ጥናትና ምርምር ዘርፍ የተሰጠዉን ተግባራት ለማከናወን የሚከተለዉን መዋቅር ዘርግቷል፡-

የአስተዳደር ህግ ምንነት፣


የአስተዳደር ህግ ምንነት።
 
ለአስተዳደር ህግ ብያኔ በማበጀት ረገድ የመስኩ ባለሙያዎች በከፊልም ቢሆን የተለያየ እይታ አላቸው፡፡ በእርግጥ የአስተዳደር ህግ የጥናት ወሰኑን አስመልክቶ የሚከሰት ልዩነት ካልሆነ በቀር በመሰረታዊ እሳቤው ላይ የተራራቀ አቋም የለም፡፡ እንደ ህንዳዊው የአስተዳደር ህግ ምሁር አይ.ፒ. ማሴይ አገላለጽ በአስተዳደር ህግ ትርጓሜ ላይ ያለው ልዩነት ምንጩ በየጊዜው እያደገና እየተወሳሰበ የመጣው አስተዳደራዊ ሂደት ሲሆን ይህም ሂደቱን በሙሉ አጠቃሎ የያዘ ወጥ ትርጉም ለመስጠት አስቸጋሪ አድርጐታል፡፡

ያም ሆኖ የአስተዳደር ህግ ትርጓሜ ቢያንስ ሁለት መሰረታዊ አላባውያንን ማካተት ይጠበቅበታል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የአስተዳደር ህግ ከይዘት ይልቅ ስነ ስርዓት ላይ የሚያተኩር ህግ ስለመሆኑ ግልጽ መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም የአስተዳደር ውሳኔው እንዴት ተሰጠ? እንጂ ይዘቱ ትክክል ይሁን አይሁን ፍርድ ቤቶች ሆነ የአስተዳደር ህግ ጣልቃ የሚገባበት ጉዳይ አይደለም፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ማንኛውም የአስተዳደር ህግ ትርጓሜ የህጉን ዓላማ ግምት ውስጥ ያስገባ ተግባራዊ አቀራረብ እንዲያቅፍ ይጠበቅበታል፡፡ የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ዓላማ ወይም ተግባር ስልጣንን መቆጣጠር ነው፡፡h ያ ሲባል ግን የአስተዳደር አካላት ስራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩና እንዳይላወሱ ማነቆ ሆኖ ያግዳቸዋል ማለት አይደለም፡፡ የስልጣን ቁጥጥር ሲባል ማንኛውም ባለስልጣን ሆነ መስሪያ ቤት በህግ ተለይቶ ከተቀመጠለት የስልጣን ገደብ እንዳያልፍና ስልጣን ቢኖረውም እንኳን ስልጣኑን ፍትሐዊና አግባብ በሆነ መንገድ እንዲወጣ ያደርጋል ለማለት ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ዓላማና ተግባር ስልጣንን በተግባር መቆጣጠር እንደመሆኑ ይህን ባህርዩን ግምት ውስጥ ያላስገባ ብያኔ የተሟላ ተብሎ ሊወሰድ ሆነ ሊወደስ አይችልም፡፡

ለንጽጽር እንዲረዳን በመስኩ ባለሙያዎች ለአስተዳደር ህግ የተሰጡ ትርጓሜዎችን እንደሚከተለው እንጠቅሳለን፡፡
ቤርናርድ ሺዋሬዝ (Bernard Schwartz) የአስተዳደር ህግን ‘በውክልና ህግ የማውጣትና አስተዳደራዊ ዳኝነት የመስጠት ስልጣን ባላቸው የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ህግ’ በማለት ይገልፀዋል፡፡i ይህ ብያኔ ጠባብ ከመሆኑ በቀር ስለ ህጉ ይዘት ገላጭ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ በውክልና ስልጣን ህግ ከማውጣትና ከአስተዳራዊ የዳኝነት ስልጣን በተጨማሪ ይህ ስልጣን በፍርድ የሚታረምበትን የአጣሪ ዳኝነት (judicial review) ስነ-ስርዓት እንዲሁም በፖርላማና በተለያዩ ተቋማት የሚደረግ ቁጥጥርንም ያካትታል፡፡
ጄኒንግስ በበኩሉ የአስተዳደር ህግ ማለት ‘አስተዳደርን የሚመለከት ህግ ነው፡፡ ይህ ህግ የአስተዳደር መስሪያ ቤቶችን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ግዴታ ይወስናል፡፡’ በማለት ይገልጸዋል፡፡j እንደ አይ.ፒ ማሴይ አስተያየት ይህ ትርጓሜ የአስተዳደር ህግን ከህገ መንግስት በግልጽ አይለይም፡፡ አስተዳደር ወይም ማስተዳደር ማለት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስልጣንን በመጠቀም የህብረተሰቡን ጉዳይ መምራት ማለት ነው፡፡k ለዚህም በዋነኛነት አደራ የተጣለባቸው አካላት የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ናቸው፡፡ ምንም እንኳን የእነዚህ ተቋማት ስልጣንና ግዴታ በዝርዝር ህግ ተለይቶ ቢወሰንም የስራ አስፈፃሚው አካል ስልጣን በጠቅላላው የሚቀመጠው በህገ መንግስት ላይ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ሆነ ህገ መንግስት ሁለቱም የመንግስት አስተዳደርን ወይም የግለሰብና የመንግስትን ግንኙነት የሚመሩ ህጐች እንደመሆናቸው በመካከላቸው ያለው መለያ ክር በጄኒንግ ትርጓሜ ላይ በግልጽ ነጥሮ አልወጣም፡፡

ታዋቂው የህገ መንግስት ሊቅ ኤ. ቪ. ዲሴይ የአስተዳደር ህግን በሶስት ደረጃዎች ከፋፍሎ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡l
የአስተዳደር ህግ የመንግስት ባለስልጣናትን የህግ ስልጣንና ተጠያቂነት የሚወስኑትን የአንድ አገር የህግ ስርዓት የሚመለከት የህግ ክፍል ነው፡፡
ግለሰቦች ከመንግስት አካላት ጋር በሚኖራቸው ግንኙነት ያላቸውን መብትና ግዴታ ለይቶ ይወስናል፡፡
እነዚህ መብቶችና ግዴታዎች ተፈጻሚ የሚሆኑበትን ስርዓት ይዘረጋል፡፡
እንደ ማሴይ ትችት ይህ ትርጓሜ የአስተዳደር ህግ አንድ አካል የሆነውን አጣሪ ዳኝነት (judicial review) ብቻ የሚመለከት እንደመሆኑ በይዘቱ ጠባብ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ከአጣሪ ዳኝነት በተጨማሪ በህግ አውጭውና በተቋማት (ለምሳሌ በእንባ ጠባቂ ተቋምና ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን) አማካይነት የሚደረግ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችንም ያካትታል፡፡ ህጉ ከመንግስት ባለስልጣናትና ከአስተዳደር መስሪያ ቤቶች በተጨማሪ ከፊል የአስተዳደር አካላት ተብለው የሚፈረጁትን መንግስታዊ ኮርፖሬሽኖች፤ ዩኒቨርሲቲዎች እና በከፊል መንግስታዊ ነክ ስልጣን ያላቸውን ማህበራትm በተመለከተም ተፈጻሚነት አለው፡፡
በመጨረሻም ታዋቂው የህንድ ምሁር አይ.ፒ. ማሴይ ከላይ ከተሰጡት ሰፋ ያለና የህጉን ባህሪያትና ተግባራት ጠቅልሎ የያዘ ብያኔ እንደሚከተው ያስቀምጣል፡፡
የአስተዳደር ህግ የህዝብ አስተዳደር ህግ አካል ሲሆን የአስተዳደርና ከፊል አስተዳደር መስሪያ ቤቶችን አደረጃጀትና ስልጣን የሚደነግግ፣ አስተዳደራዊ ውሳኔ የሚሰጥበትን ደንብና መርህ የሚያስቀምጥ፣ እንዲሁም ከግለሰቦች መብትና ነፃነት ውሳኔው የሚታረምበትን ስርዓት የሚወስን የህግ ክፍል ነው፡፡n
ይህ ትርጓሜ ከሞላ ጐደል ሁሉንም የአስተዳደር ህግ ባህርያት አጠቃሎ የያዘ በመሆኑ ተመራጭነት አለው፡፡ ከላይ ከቀረቡት የተለያዩ ትርጓሜዎች የሚከተሉት የጋራ ነጥቦች ይመዘዛሉ::

አንደኛ፤ የአስተዳደር ህግ የአስተዳደር እና ከፊል የአስተዳደር አካላት ያላቸውን ስልጣን፣ ተግባርና ኃላፊነት ያጠናል፡፡o የማንኛውም የአስተዳደር አካል የስልጣን ምንጭ የሚገኘው ከማቋቋሚያ አዋጁ (Enabling Act) ሲሆን አልፎ አልፎ በሌላ ዝርዝር ህግ ይወሰናል፡፡ በአስተዳደር ህግ የመጀመሪያው ጥያቄ ውሳኔ ወይም እርምጃ የወሰደው አካል በህግ የተሰጠው ስልጣን አለው? የሚል ነው፡፡ ከሌለ ድርጊቱ ከስልጣን በላይ ስለሆነ ዋጋ አልባ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ከድርጊቱ በስተጀርባ የህግ ስልጣን ካለ ውሳኔ ሰጪው ስልጣኑን በአግባቡና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንደተገለገለ ይጣራል፡፡ ካልሆነ ስልጣኑን ያለ አግባብ በሚገለገለው አካል ላይ ህጉ ቁጥጥር ያደርግበታል፡፡

ሁለተኛ፤ ህጉ ስልጣንን በመገልገል ሂደት ተፈጻሚ የሚሆኑ መሪ ደንቦችን፤ ስነ ስርዓቶችንና መርሆዎችን ያስቀምጣል፡፡ ህግ አውጭው ለአስተዳደር አካላት ስልጣን ሲሰጥ ስልጣኑ ተግባር ላይ በሚውልበት ጊዜ ህጋዊነቱንና ፍትሐዊነቱን የሚያረጋግጥ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታ አብሮ እንዲደነግግ ይጠበቃል፡፡ ለምሳሌ ያህል ደንብና መመሪያ በማውጣት ረገድ ከሚመለከተው አካል ጋር የመመካከርና የህትመት ቅድመ ሁኔታዎች፣ አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሰጥ የመሰማት መብትና የኢ- አድሎአዊነት መርሆዎችን በአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ወይም በዝርዝር ህግ ማውጣት ይኖርበታል፡፡ እነዚህም በአስተዳደር ሂደቱ ውስጥ ፍትሐዊነትን በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ስፍራ አላቸው፡፡ ስልጣን በዘፈቀደ ሳይሆን በአግባቡ ስራ ላይ ዋለ ለማለት የሚቻለውም ያኔ ነው፡፡

ሶስተኛ፤ የአስተዳደር ህግ የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችን በተመለከተ የሚያጠና ህግ ነው፡፡p ልጓም የሌለው ስልጣን ለዜጎች መብትና ነፃነት ፀር ነው፡፡ የተጠያቂነት መርሕ እውን እንዲሆን የስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቶችም በግልጽ ተለይተው መቀመጥ ይኖርባቸዋል፡፡ ስለሆነም የአስተዳደር ህግ በፍርድ ቤት፤ በአስተዳደር ፍርድ ቤት፤ በህግ አውጭው እና በተቋማት የሚደረጉ የስልጣን መቆጣጠሪያ መንገዶችን በተግባር እየፈተነ ያጠናል፡፡

አራተኛ፤ ህጉ በአስተዳደር አካላት ወይም በመንግስት ባለስልጣናት በተወሰዱ እርምጃዎች መብታቸው ለተጣሰና ነፃነታቸው ለተገፋ ዜጎች መፍትሔ ይሰጣል፡፡q መብት ያለ መፍትሔ ‘ላም አለኝ በሰማይ’ ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ መብቱ የተጓደለበት ሰው አቤቱታ አቅርቦ መፍትሔ የሚጠይቅበትና የሚያገኝበት የህግ ክፍል ነው፡፡
 
የአስተዳደር ህግ ግብና ተግባራት፣

የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ዓላማና ተግባር ስልጣንን መቆጣጠር ስለመሆኑ በመስኩ ምሁራን ስምምነት የተደረሰበት ጉዳይ ሆኗል፡፡ ሆኖም በዚህ ብቻ ሳይወሰን ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትንም ያከናውናል፡፡ እንደ ብዙዎች የአስተዳደር ህግ ሊቃውንት የአስተዳደር ህግ ዋነኛ ግብ አስተዳደራዊ ፍትህን ማስፈን ሲሆን የሚከተሉት ተግባራት ይኖሩታል፡፡

ስልጣን መቆጣጠር (Control Function)፣

የአስተዳደር ህግ ስራ አስፈፃሚው የመንግስት አካልና የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች፣ ሚኒስትሮች፣ ባለስልጣናትና ሌሎች ሹመኞች በህግ ተለይቶ የተሰጣቸውን ስልጣን አልፈው እንዳይሄዱና ህጋዊ ስልጣናቸውንም አለአግባብ እንዳይገለገሉበት ለመቆጣጠር የሚያስችለን የህግ ክፍል ነው፡፡ በመሆኑም ስልጣን በህገ ወጥ መንገድ አለአግባብ ጥቅም ላይ እንዳይውል በመከላከል እንደ መገደቢያ መሳሪያነት ያገለግላል፡፡r

ግዴታ ማስፈፀም (Command Function)፣

በአስተዳደሩ በሚፈፀም ድርጊት የዜጋው መብት ከሚጣስበት ሁኔታ ባልተናነስ ህጋዊ ግዴታን አለመወጣት በግል መብትና ጥቅም ላይ የከፋ ጉዳት ያስከትላል፡፡ የአስተዳደር ህግ ስልጣን በልኩና በአግባቡ ተግባር ላይ እንዲውል ከመቆጣጠር ባሻገር የአስተዳደር አካላት በህግ ተለይቶ የተጣለባቸውን ግዴታ እንዲወጡ አስገዳጅ የስነ ስርዓትና ተቋሟዊ ስልቶችን ይቀይሳል፡፡s አስገዳጅ የህግ ማዕቀፍ ከሌለ ግዴታ በፈቃድ ላይ የተመሰረተ ውዴታ ብቻ ሆኖ ይቀራል፡፡

የአስተዳደር ፍትህ ማስፈን፣

በየትኛውም ህግን ለማስፈፀም ስልጣን በተሰጠው የመንግስት አካል የሚወሰዱ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችና እርምጃዎች የህዝብ አመኔታና ተቀባይነት እንዲያገኙ ፍትሐዊነታቸው በተጨባጭ ሊታይ ይገባል፡፡ የአስተዳደር ህግ አይነተኛ ተልዕኮ የአስተዳደር ፍትህን ማስፈን ነው፡፡

ግልጽነት ተጠያቂነትና የህዝብ ተሳትፎ፣

የአስተዳደር ህግ በመንግስት አስተዳደር ስራ ውስጥ ግልፅነት፣
ተጠያቂነትና የህዝብ ተሳትፎ እንዲረጋገጥ ተግባራዊ መሳሪያ በመሆን ያገለግላል፡፡ የስልጣን ልኩ ሳይታወቅና ከልክ በላይ የሆነ ስልጣን መቆጣጠሪያ ስልቱ ሳይቀየስ ስለተጠያቂነት ማውራት የማይመስል ነገር ነው፡፡ የአስተዳደር ህግ ዜጎች መረጃ የማግኘት መብታቸውን በህግ የሚያረጋግጥ ከመሆኑም በላይ በህዝብ አስተዳደር ውስጥ በንቃት እንዲሳተፉ የሚያስችሉ የስነ- ስርዓት ደንቦችን ይዘረጋል፡፡

ለተበደለ ወገን መፍትሔ መስጠት፣

የአስተዳደር ህግ ዜጎች ለደረሰባቸው በደል በፍርድ ቤት ወይም ከፍርድ ቤት ውጭ ባሉ መንገዶች አቤቱታ አቅርበው በአነስተኛ ወጪ እና በቀላሉ መፍትሔ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል፡፡ ስለ አስተዳደር ህግ በተደጋጋሚ ቢወራ ‘አንጀት ጠብ’ የሚል፣ የሚጨበጥ፣ የሚዳሰስ፣ መፍትሔ እስከሌለ ድረስ ረብ የለሽነቱን ያጎላው እንደሆነ እንጂ የሚፈይደው ነገር የለም፡፡

ባለስልጣናት በህዝብ ላይ ለሚፈፅሟቸው አስተዳደራዊ በደሎች በዝርዝር የተቀመጡ የመፍትሔ መንገዶች አሏቸው፡፡
በአንድ አገር ውስጥ የአስተዳደር ህግ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራቱን ውጤታማ በሆነ መንገድ ተወጥቷል ለማለት ከአገሪቱ የመንግስት አወቃቀር ስርዓት፤ ህገ መንግስታዊና ዲሞክራሲያዊ ዕድገትና የአስተዳደር ህግ ተቋማት መዳበር ከግምት ውስጥ በማስገባት አንፃራዊ በሆነ መልኩ የሚለካ ጉዳይ ነው፡፡ በአጠቃላይ ግን በአንድ አገር ውስጥ ሁሉን አቀፍ ውጤታማና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰ የአስተዳደር ህግ ስርዓት አለ ለማለት ከሚከተሉት ሶስት ዋነኛ መርሆዎች አንጻር እየተመነዘረ መገምገም አለበት፡፡

የአስተዳደር ፍትህ፤

የአስተዳደር በደል በፍርድ የሚታረምበትና አስተዳደራዊ ፍትሕ የሚገኝበት የፍርድ ሂደትና መንገድ እንዲሁም ተሞክሮ በአገራችን ውስጥ በግልጽ የሚታወቅ አይደለም፡፡ የአስተዳደር ፍትሕ የአስተዳደር ህግ ‘ልቡ’ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አስተዳደራዊ በደል አለቅጥ በተንሰራፋበት አገር ውስጥ የአስተዳደር ህግ ትንፋሽ ያጠረው ህላዌነቱ የሚያጠራጥር ህግ ነው፡፡ የከለላው መጠን የአስተዳደር ፍትህ ደረጃ አንጻራዊ መለኪያ ነው፡፡

የስራ አስፈፃሚው ተጠያቂነት፤

የዚህ መርህ ዋና አላማ ህግ የማስፈፀም ስልጣን ያለው አካል ለሚፈፅመው ድርጊት እና ለሚወስደው እርምጃ በህዝብ ፊት ተጠርቶ እንዲጠየቅና ማብራሪያ እንዲሰጥ ለማስገደድ ነው፡፡ ማንኛውም የመንግስት ባለስልጣንን የተቀበለ አካል ወይም ባለስልጣን የሚፈፅመው ድርጊት የህዝቡን ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆን ይኖርበታል፡፡ ውሳኔ ሰጭው ለድርጊቱ ትክክለኛነትና ፖለቲካዊ ተገቢነት ህግ አውጭው ፊት ተጠርቶ በመቅረብ ለማብራሪያ የሚገደድበት ስርዓት ከሌለ በቀር ተጠያቂነት አለ ማለት አይቻልም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አስተዳደሩ በዜጎች መብት ለሚያደርሰው ጉዳት በፍርድ ሂደት ለድርጊቱ ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፡፡

መልካም አስተዳደር፣

በዚህ መርህ መሰረት አስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ሁሉን አቀፍ ተቀባይነት ላገኙ መሪ ደንቦች መገዛት አለበት፡፡ እነዚህም የፍትሀዊነት፣ ምክንያታዊነት፣ ሚዛናዊነትና የግልፅነት መርሆዎችን ያጠቃልላሉ፡፡ አስተዳደራዊ ውሳኔ በህጉ መሰረት መወሰዱ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ የውሳኔው መሰረት ከቅን ልቦና የመነጨ፣ ለባለጉዳዩ ግልፅ በሆነ አሰራርና መንገድ ያልተወሰደ ካልሆነ በስተቀር የመንግስት አስተዳደር ወደ መልካምነት ደረጃ ለመድረስ ገና ብዙ ይቀረዋል፡፡ የአስተዳደር ህግ እነዚህን መርሆዎች እንዲዳብሩ ከማድረግ አንፃር አይነተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ ስለሆነም የህጉ የእድገት ደረጃ የአንድ አገር የመልካም አስተዳደር ሁኔታ ጠቋሚ መለኪያ ነው ማለት እንችላለን፡፡

በወንጀል የዳኝነት ስልጣን።


በወንጀል የዳኝነት ስልጣን፡-

1. በፌደራል መንግስቱ የቀረጥና የግብር ገቢዎች በጠቅላላ የገንዘብ ጥቅሞች ላበሚፈጸም ወንጀል

2. የሀሰት ገንዘብን በሚመለከቱ ወንጀሎች

3. በፌደራል መንግስቱ ሰነዶች ላይ የሐሰት ሰራ በመስራት በሚፈጸሙ ወንጀሎች

4. ከአንድ ክልል በላይ ውይም በአለም አቀፍ ደረጃ አገልግሎት በሚሰጡ መገናኛዎች ፀጥታና ነጻነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች

5. የውጭ ሀገር ዜጎችን የሚመለከቱ ወንጀሎች

6. በአዲስ አበባና በድሬደዋ ውስጥ በሚነሱ በስራ ላይ ባሉ ሌሎች ሕጎች ለአውራጃና ለወረዳ ፍርድ ቤቶች በተሰጡ በሌሎች የወንጀል ጉዳዮች

ጋብቻ በንብረት በኩል ስለሚኖረው ውጤት


ጋብቻ በንብረት በኩል ስለሚኖረው ውጤት

አንቀጽ ፶፯ የባልና ሚስት የግል ሀብት (፩) ያለግብይት የተገኙ ንብረቶች

 

ባልና ሚስት ጋብቻቸውን በሚፈጽሙበት ጊዜ በየግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ ወይም በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንብረቶቻቸው ሆነው ይቀራሉ፡፡

 

አንቀጽ ፶፰ (፪) በግብይት የተገኙ ንብረቶች

 

፩. ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ አንዱ የግል ሀብቱ በሆነ ንብረት ለውጥ ያገኘው ወይም በግል ገንዘቡ የገዛቸው ወይም የግል ንብረቱን ሸጦ የሚያገኘው ገንዘብ የግል ሀብቱ ይሆናል፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተመለከተው ድንጋጌ ተፈፃሚ የሚሆነው በግብይት የተገኘው ንብረት የግል ይባልልኝ ብሎ አንደኛው ወገን ጥያቄ ሲያቀርብ እና ፍርድ ቤት ሲያፀድቀው ብቻ ነው፡፡

 

አንቀጽ ፶፱ የግል ሀብትን ስለማስተዳደር (፩) መሠረቱ

 

፩. እያንዳንዱ ተጋቢ የግል ሀብቱን ራሱ ለማስተዳደርና ገቢውንም ለመቀበል ይችላል፡፡

፪. እያንዳንዱ ተጋቢ የግል ሀብቱን ራሱ ሊያዝበት ነፃነት አለው፡፡

 

አንቀጽ ፷ (፪) የግል ሀብት አስተዳደርን በጋብቻ ውል ስለመወሰን

 

፩. ባልና ሚስት አንደኛው የሌላውን ተጋቢ የግል ሀብት በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድርለት እና እንደአስፈላጊነቱ እንዲያዝበት በጋብቻ ውላቸው ሊወስኑ ይችላሉ፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) በተመለከተው አኳኋን ንብረት የማስተዳደር ሥልጣን የተሰጠው ተጋቢ በሌላኛው ተጋቢ ሲጠየቅ ስለንብረቱ አስተዳደር ዓመታዊ የሂሳብ መግለጫ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡

 

አንቀጽ ፷፩ (፫) ስለውክልና ሥልጣን

 

ከተጋቢዎች አንዱ የግል ሀብቱን በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድርለት ለሌላኛው ተጋቢ ውክልና መስጠት ይችላል፡፡

 

አንቀጽ ፷፪ የባልና ሚስት የጋራ ሀብት

 

፩. ባልና ሚስት ከግል ጥረታቸውና ከግል ወይም ከጋራ ንብረታቸው የሚያገኟቸው ገቢዎች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው ይሆናሉ፡፡

፪. በዚህ ሕግ በአንቀጽ ፶፰ ንዑስ አንቀጽ (፪) መሠረት የአንደኛው ተጋቢ የግል ሀብት ነው ካልተባለ በስተቀር፣ ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኙት ንብረት ሁሉ የጋራ ሀብታቸው ይሆናል፡፡

፫. በስጦታው ውል ወይም በኑዛዜው ቃል በሌላ አኳኋን ካልተመለከተ በስተቀር፣ በስጦታ ወይም በኑዛዜ ለተጋቢዎቹ የተሰጧቸው ንብረቶች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው ይሆናሉ፡፡

 

አንቀጽ ፷፫ የሕግ ግምት

 

፩. አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር ማንኛውም ንብረት በአንደኛው ተጋቢ ስም ብቻ የተመዘገበ ቢሆንም እንኳን የጋራ ሀብት እንደሆነ ይቆጠራል፡፡

፪. የግል ንብረት መሆኑን ሦስተኛ ወገኖች የሚያውቁት ወይም ሊያውቁት የሚገባ ካልሆነ በስተቀር፣ ባልና ሚስቱ ወይም ከሁለቱ አንዱ ይኸው ንብረት የግል ነው በማለት በሦስተኛ ወገን ላይ መቃወሚያ አድርገው ሊያቀርቡት አይችሉም፡፡

 

አንቀጽ ፷፬ ስለባልና ሚስት ገቢ (፩) መደበኛ የገቢ አስተዳደር

 

፩. ባልና ሚስት እያንዳንዳቸው ገቢያቸውን በየራሳቸው ይቀበላሉ፡፡

፪. ባልና ሚስት በየግላቸው የሚያገኙትን ገቢ የግል ወይም የጋራ የባንክ ሂሳብ በመክፈት ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡

፫. ከባልና ከሚስት አንደኛው ሲጠይቅ፣ ሌላኛው ተጋቢ ያገኘውን የገቢ መጠን የማስታወቅ ግዴታ አለበት፡፡

 

አንቀጽ ፷፭ (፪) ልዩ ሁኔታ

 

፩. ከባልና ከሚስት አንዱ፣ ገቢውን ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልለት ሥልጣን ለመስጠት ሙሉ ነፃነት አለው፡፡

፪. ከባልና ከሚስት በአንደኛው ጠያቂነት የአንደኛውን ገቢ ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልና ለመቀበሉም ደረሰኝ እንዲሰጥ ፍርድ ቤት ሊወስን ይችላል፡፡

፫. በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር፣ ከባልና ከሚስት የአንደኛው ገቢ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲከበር በፍርድ ቤት ሊታዘዝ ይችላል፡፡

 

አንቀጽ ፷፮ የጋራ ሀብትን ስለማስተዳደር

 

፩. ከባልና ከሚስት አንዱ፣ የጋራ ሀብታቸውን በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያስተዳድር ግልጽ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ባልና ሚስቱ የጋራ ሀብታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ፡፡

፪. ከባልና ከሚስት አንዱ ችሎታ የለውም ተብሎ ሲወሰን ወይም ንብረት የማስተዳደር መብቱን ሲገፈፍ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት የጋራ ሀብታቸውን ለማስተዳደር የማይችል ሆኖ ሲገኝ ሌላኛው ተጋቢ የጋራ ሀብቱን የማስተዳደሩን ተግባር ያከናውናል፡፡

 

አንቀጽ ፷፯ የማስታወቅ ግዴታ

 

ከተጋቢዎች አንዱ ብቻ የጋራ ሀብታቸውን በሚያስተዳድርበት ጊዜ የሀብቱን አስተዳደር በተመለከተ ለሌላኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡

 

አንቀጽ ፷፰ (፩) የተጋቢዎች ስምምነት አስፈላጊ ስለመሆኑ

 

በሌላ ሕግ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር፣ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ የተጋቢዎቹ ስምምነት አስፈላጊ ነው፤

 

ሀ) የጋራ የሆነውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ፣ ለመለወጥ፣ ለማከራየት በመያዣ ወይም በዋስትና ለመስጠት ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ በዚሁ ንብረት ላይ ሌሎች ሰዎች መብት እንዲያገኙ ለማድረግ፤

ለ) ዋጋቸው ከብር ፭፻ (አምስት መቶ) በላይ የሆኑ የሚንቀሳቀሱ የጋራ ንብረቶችን ወይም የገንዘብ ሰነዶችን፣ ለመሸጥ፣ ለመለወጥ በመያዣ ወይም በዋስትና ለመስጠት ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ለማስተላለፍ፤

ሐ) ከብር ፻ (አንድ መቶ) በላይ ዋጋ ያለውን የጋራ ንብረት ወይም ገንዘብ ለሌላ ሰው በስጦታ ለማስተላለፍ፤

መ) ከብር ፭፻ (አምስት መቶ) በላይ ለመበደር ወይም ለማበደር ወይም ለሌላ ሰው ዋስ ለመሆን፡፡

 

አንቀጽ ፷ (፪) የስምምነት አለመኖር ስለሚያስከትለው ውጤት

 

፩. አንደኛው ተጋቢ ከዚህ በላይ የተመለከተውን ድንጋጌ ባለማክበር የውል ግዴታ ገብቶ የተገኘ እንደሆነ፣ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው ሊፈርስ ይችላል፡፡

፪. ግዴታው እንዲፈርስ የሚቀርበው ጥያቄ ጠያቂው ወገን ግዴታው መገባቱን ከአወቀበት ቀን ጀምሮ ከስድስት ወር በኋላ ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ግዴታው ከተገባ ከሁለት ዓመት በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡

 

አንቀጽ ፸ የባልና ሚስት ዕዳ

 

፩. ከባል ወይም ከሚስት በግል የሚጠየቅ ዕዳ፣ ከባለዕዳው ተጋቢ የግል ሀብት፣ የግል ሀብቱ ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከጋራ ሀብታቸው ይከፈላል፡፡

፪. ዕዳው የመጣው ለትዳራቸው ጥቅም ከሆነ ከጋራ ሀብታቸው የጋራ ሀብታቸው፣ ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከባል ወይም ከሚስት የግል ሀብት ይከፈላል፡፡

 

አንቀጽ ፸፩ ለትዳር ጥቅም እንደተደረገ የሚቆጠር ዕዳ

 

የሚከተሉት ዕዳዎች ለትዳር ጥቅም እንደተደረጉ የሚቆጠሩ ናቸው፡፡

ሀ) ለባልና ለሚስት እንዲሁም ለልጆቻቸው የዕለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ለማሟላት የተገቡ ዕዳዎች፤

ለ) ባል ወይም ሚስት ቀለብ ለመስጠት ያለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተደረጉ ወጪዎች፤

ሐ) ከባልና ከሚስት በአንደኛው ወይም በዕዳ ጠያቂው አለመልካችነት ለትዳር ጥቅም ስለመሆኑ ፍርድ ቤት የተቀበለው ሌላ ዕዳ፡፡

 

አንቀጽ ፸፪ የትዳር ወጪዎችን ስለመሸፈን

 

ተጋቢዎች የትዳራቸውን ወጪ ለመሸፈን እያንዳንዳቸው እንደየአቅማቸውና ችሎታቸው አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው፡፡

 

አንቀጽ ፸፫ በተጋቢዎች መካከል ስለሚደረጉ ውሎች

 

ባልና ሚስቱ ተጋብተው በሚኖሩበት ጊዜ በመካከላቸው የሚያደርጓቸው ውሎች፣ ፍርድ ቤት ካላፀደቃቸው በስተቀር ውጤት አይኖራቸውም፡፡

የጋብቻ ሁኔታዎች አለመሟላት የሚያስከትለው ውጤት


የጋብቻ ሁኔታዎች አለመሟላት የሚያስከትለው ውጤት

አንቀጽ ፴፩ የዕድሜ ሁኔታ

 

፩. በዚህ ሕግ አንቀጽ ፯ ንዑስ አንቀጽ (፪) የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ዕድሜአቸው ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች በሆኑ ሰዎች መካከል የተፈፀመ ጋብቻ በማንኛውም ባለጉዳይ ወይም በዐቃቤ ሕግ ጥያቄ እንዲፈርስ ይደረጋል፡፡

፪. ሕጉ የሚጠይቀው የጋብቻ ዕድሜ ከተሟላ በኋላ ጋብቻው እንዲፈርስ ጥያቄ ማቅረብም ሆነ መወሰን አይቻልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፪ የሥጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና

በሥጋ ወይም በጋብቻ ዝምድና ምክንያት ጋብቻ እንዳይፈጸም የተደነገገውን ክልከላ በመተላለፍ የተፈጸመ ጋብቻ በማንኛውም ባለጉዳይ ወይም በዐቃቤ ሕግ ጥያቄ እንዲፈርስ ይደረጋል፡፡

 

አንቀጽ ፴፫ በጋብቻ ላይ ጋብቻ

 

፩. በጋብቻ ላይ ሌላ ጋብቻ ተፈጽሞ የተገኘ እንደሆነ በመጀመሪያው ወይም በሁለተኛው ተጋቢ ወይም በዐቃቤ ሕግ ጥያቄ የኋለኛው ጋብቻ እንዲፈርስ ይደረጋል፡፡

፪. ሆኖም የመጀመሪያው ተጋቢ የሞተ እንደሆነ የኋለኛው ጋብቻ እንዲፈርስ መጠየቅ አይቻልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፬ በፍርድ ክልከላ ምክንያት ጋብቻን ስለማፍረስ

 

፩. በፍርድ የተከለከለ ሰው ፍርድ ቤት ሳይፈቅድ ጋብቻ ፈጽሞ የተገኘ እንደሆነ፣ የተከለከለው ሰው ራሱ ወይም አሳዳሪው ጋብቻው እንዲፈርስ ጥያቄውን ለፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል፡፡

፪. የተከለከለው ሰው ጋብቻው እንዲፈርስ የሚያቀርበው ጥያቄ ክልከላው ከቀረበት ቀን ጀምሮ ስድስት ወር ካለፈ በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡

፫. ጋብቻው እንዲፈርስ በአሳዳሪው የሚቀርበው ጥያቄ ጋብቻው መፈፀሙን ከአወቀበት ቀን ጀምሮ ከስድስት ወር በኋላ ወይም በማናቸውም ምክንያት ቢሆን ክልከላው ከቀረ በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፭ በኃይል ተግባር የተፈፀመ ጋብቻን ስለማፍረስ

 

፩. ማንኛውም ሰው ተገዶ ጋብቻ የፈጸመ እንደሆነ ጋብቻው እንዲፈርስ ጥያቄውን ለፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል፡፡

፪. ስለዚህ ጉዳይ የሚቀርበው ጥያቄ የኃይል ሥራው ከቀረበት ከስድስት ወር በኋላ እና በማናቸውም ምክንያት ቢሆን ጋብቻው ከተፈፀመ ከሁለት ዓመት በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፮ በስህተት ምክንያት የተፈጸመ ጋብቻን ስለማፍረስ

 

፩. ማንኛውም ሰው ከመሠረታዊ ስህተት በመነሳት ጋብቻ የፈፀመ እንደሆነ ጋብቻው እንዲፈርስ ጥያቄውን ለፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል፡፡

፪. ስለዚህ ጉዳይ የሚቀርበው ጥያቄ መሳሳቱን ከአወቀበት ቀን ጀምሮ ከስድስት ወር በኋላ እና በማናቸውም ምክንያት ቢሆን ጋብቻው ከተፈፀመ ከሁለት ዓመት በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፯ በብቸኝነት ለመኖር የተወሰነውን ጊዜ ስላለመጠበቅ

 

በዚህ ሕግ አንቀጽ ፲፮ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተመለከተው በብቸኝነት ለመኖር የተወሰነው ጊዜ አልተከበረም በሚል ምክንያት ብቻ ጋብቻ እንዲፈርስ ጥያቄ ሊቀርብ አይችልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፰ የክብር መዝገብ ሹም ሥልጣን የሌለው ስለመሆኑ

 

ጋብቻው ያስፈጸመው የክብር መዝገብ ሹም በአንቀጽ ፳፪ መሠረት ሥልጣን አልነበረውም በማለት ብቻ ጋብቻው እንዲፈርስ ለመወሰን አይቻልም፡፡

 

አንቀጽ ፴፱ የሥነ ሥርዓት አለመጠበቅ

 

በዚህ ሕግ አንቀጽ ፳፭ ንዑስ አንቀጽ (፫) እና (፮) የተመለከቱት ሥርዓቶች አልተጠበቁም በማለት ብቻ ጋብቻ እንዲፈርስ ሊወሰን አይችልም፡፡

የጋብቻ ውጤት


የጋብቻ ውጤት



አንቀጽ ፵ ሁሉም የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓቶች ተመሳሳይ ውጤት ያላቸው ስለመሆኑ

 

፩. በማናቸውም ዓይነት የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓት መሠረት የተፈፀመ ጋብቻ ተመሳሳይ ሕጋዊ ውጤት ይኖረዋል፡፡

፪. በዚህ ረገድ ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት ወይም በሃይማኖት ወይም በባህል በታዘዙት ሥርዓቶች መሠረት የተፈፀመም ቢሆን ልዩነት አይደረግበትም፡፡

 

አንቀጽ ፵፩ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈፀም

 

የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት በዕውነት መፈፀሙ ወይም ተፈጽሟል ተብሎ መገመቱ፣ ጋብቻው ለሚያስከትለው ውጤት አስፈላጊ አይደለም፡፡

 

አንቀጽ ፵፪ (፩) የጋብቻ ውል

 

፩. ተጋቢዎቹ ጋብቻቸው ንብረታቸውን በተመለከተ ስለሚያስከትለው ውጤት ጋብቻቸውን ከመፈፀማቸው በፊት ወይም እጅግ ቢዘገይ ጋብቻቸው በሚፈፀምበት ዕለት በውል መወሰን ይችላሉ፡፡

፪. እንዲሁም ግላዊ ግንኙነታቸውን በሚመለከት የሚኖሯቸውን መብቶችና ግዴታዎች በዚህ ውል መወሰን ይችላሉ፡፡

፫. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) እና (፪) መሠረት ተጋቢዎቹ የሚያደርጓቸው ውሎች አስገዳጅ የሕግ ድንጋጌዎችን የሚቃረኑ ሊሆኑ አይችሉም፡፡

 

አንቀጽ ፵፫ (፪) የተጋቢዎቹ ችሎታ ማጣት

 

፩. በፍርድ የተከለከለ ሰው የሚያደርገውን የጋብቻ ውል እርሱ ራሱ ካልፈፀመውና ፍርድ ቤት ካላፀደቀው በስተቀር ውጤት አይኖረውም፡፡

፪. በሕግ የተከለከለ ሰው፣ የጋብቻ ውል መዋዋልን በተመለከተ ችሎታ እንዳለው ይቆጠራል፡፡

 

አንቀጽ ፵፬ (፫) የውሉ ፎርም

የጋብቻ ውል በጽሑፍ ካልተደረገና አራት ምስክሮች፣ ሁለት በባል ወገን፣ ሁለት በሚስት ወገን፣ የፈረሙበት ካልሆነ በስተቀር ውጤት አይኖረውም፡፡

 

አንቀጽ ፵፭ (፬) የውሉ ሰነድ ስለሚቀመጥበት ቦታ

 

፩. የጋብቻ ውሉ አንድ ቅጅ በፍርድ ቤት ወይም በክብር መዝገብ ሹም ዘንድ ይቀመጣል፡፡

፪. ተጋቢዎች ወይም ከተጋቢዎች አንዱ ለማየት በፈለጉ ጊዜ እንዲሁም በፍርድ ቤት ወይም ከተጋቢዎቹ በአንዱ የተፈቀደላቸው ሰዎች የውሉን ሰነድ ለማየት ይችላሉ፡፡

 

አንቀጽ ፵፮ (፭) ውል ለመዋዋል ስላለው የነፃነት ወሰን

 

፩. ተጋቢዎች በጋብቻቸው ውል ውስጥ በሌሎች ሦስተኛ ወገኖች ላይ ግዴታን የሚያስከትሉ ስምምነቶችን ማድረግ አይችሉም፡፡

፪. እንዲሁም ተጋቢዎቹ ባሕልን ወይም ሃይማኖትን ወይም የአንድን አገር ሕግ በጥቅሉ በመጥቀስ ብቻ ተስማምተናል በማለት የሚያደርጉት የጋብቻ ውል ውጤት አይኖረውም፡፡

 

አንቀጽ ፵፯ (፮) የጋብቻ ውልን ስለማሻሻል

 

፩. የጋብቻ ውል እንዲሻሻል የቤተሰቡ ጥቅም የሚጠይቅ ሲሆንና ተጋቢዎቹ ሲስማሙ ውሉን በማሻሻል ፍርድ ቤት እንዲፀድቅላቸው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

፪. ፍርድ ቤት በተጋቢዎቹ ተሻሽሎ የቀረበው የጋብቻ ውል የቤተሰቡን ጥቅም የማይጎዳ መሆኑን ሲያረጋግጥ የተሻሻለውን ውል ተቀብሎ ያፀድቃል፡፡

፫. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፪) በተመለከተው ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ውሉን ያፀደቀው እንደሆነ፣ የተሻሻለው ውል በፍርድ ቤት ወይም በክብር መዝገብ ሹም ዘንድ ይቀመጣል፡፡

 

አንቀጽ ፵፰ (፯) የሕግ ተፈፃሚነት

 

የጋብቻ ውል በሌለ ጊዜ ወይም የጋብቻ ውል ቢኖርም በሕግ ሳይፀና የቀረ እንደሆነ፣ ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡

 

ለሎች የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች


ሌሎች የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓቶች

አንቀጽ ፳፮ በሃይማኖት ሥርዓት የሚፈፀም ጋብቻ

 

፩. በሃይማኖት ሥርዓት መሠረት ጋብቻ ሊፈፀም የሚችልበትና የአፈፃፀሙ ሥርዓት እንደየሃይማኖቱ ይወሰናል፡፡

፪. በዚህ ሕግ ለማንኛውም የጋብቻ አፈፃፀም መሟላት አለባቸው የተባሉት ሁኔታዎች በሃይማኖት ሥርዓት መሠረት ለሚፈፀም ጋብቻም መሟላት አለባቸው፡፡

 

አንቀጽ ፳፯ በባህል ሥርዓት ስለሚፈፀም ጋብቻ

 

፩. በባሕል ሥርዓት መሠረት ጋብቻ ሊፈፀም የሚችልበትና የአፈፃፀሙ ሥርዓት በአካባቢው ባሕል ይወሰናል፡፡

፪. በዚህ ሕግ ለጋብቻ አፈፃፀም መሟላት አለባቸው የተባሉት ሁኔታዎች በባህል ሥርዓት መሠረት ለሚፈፀም ጋብቻም መሟላት አለባቸው፡፡

የፋይል እና የፒዲኤፍ ሰነዶች/FILE ADN PDF DOCUMENTS


የጋብቻ ምዝገባ


ስለጋብቻ ምዝገባ

 

አንቀጽ ፳፰ ጋብቻን ስለማስመዝገብ

 

፩. ጋብቻው የተፈፀመው በማንኛውም የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓት ቢሆንም፣ አግባብ ባለው የክብር መዝገብ ሹም መመዝገብ አለበት፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) መሠረት ምዝገባውን ያከናወነ የክብር መዝገብ ሹም ለተጋቢዎቹ የጋብቻ የምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡

፫. ማንኛውም ጋብቻ ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ ውጤት ይኖረዋል፡፡

 

አንቀጽ ፳፱ የጋብቻ መዝገብ ስለማደራጀት

 

፩. በዚህ ሕግ አንቀጽ ፳፰ ንዑስ አንቀጽ (፩) መሠረት ተጋቢዎች ጋብቻውን ያላስመዘገቡ ቢሆንም እንኳን፣ የክብር መዝገብ ሹሙ ጋብቻ መፈፀሙን ያወቀ እንደሆነ የጋብቻ መዝገብ በሥልጣኑ ያደራጃል፡፡

፪. ይህ በሚሆንበት ጊዜ የክብር መዝገብ ሹሙ ተጋቢዎቹና እንደ ነገሩ ሁኔታ ምስክሮች ቀርበው በጋብቻው መዝገብ ላይ እንዲፈርሙ ያደርጋል፡፡

 

አንቀጽ ፴ የጋብቻ መዝገብ ይዘት

 

የጋብቻ መዝገብ የሚያመለክተው፣

 

ሀ) የተጋቢዎችን ሙሉ ስም፣ የተወለዱበትን ቀንና ቦታ፣ የመኖሪያ አድራሻቸውን፣

ለ) የምስክሮችን ሙሉ ስም፣ የተወለዱበትን ቀንና ቦታ፣ የመኖሪያ አድራሻቸውን፣

ሐ) ጋብቻው የተፈፀመበትን ሥርዓት፣ ቀንና ቦታ እንዲሁም የተመዘገበበትን ቀን ይሆናል፡፡

Variation of Orders Contained in Sentences.


Variation of Orders Contained in Sentences  Art.216. – Principle.

(1) Where any order as defined in sub-art. (2) requires to be made, such order shall be made by the court having passed the sentence in relation to which such order is to be made.(2) The provisions of sub-art. (1) shall apply in cases of:(a) enforcement of internment (Art. 132 Penal Code); and(b) revision of orders made in respect of offenders not fully responsible (Art. 136 and 137 Penal Code); and(c) extension of detention (Art. 140 (2) Penal Code); and(d) revocation of probation or variation of rules of conduct (Art. 198, 202 (3) and 204 Penal Code); and(e) conditional release (Art. 131, 207, 209 – 112 Penal Code); and(f) orders under Art. 124(2) and 156 Penal Code.(3) Orders made in respect of young persons may be varied in accordance with the provisions of Art. 180 of this Code. Art.217. – Procedure and decision. (1) The court shall not make an order under this Chapter unless an application to this effect is made by the convicted person or his legal representative, the public prosecutor or any person or authority charged with executing or supervising the execution of the sentence.(2) Prior to making its decision, the court shall summon the person in respect of whom the order is to be made and such other person as is likely to give information to assist the court. The court may, where appropriate, order such inquiries to be made as appear necessary.(3) The court shall make its decision after having heard all the persons summoned and obtained the required information. Where the person in respect of whom the decision is to be made fails to appear, the court shall make its decision in his absence.(4) Any statement made and the decision of the court shall be recorded.(5) No appeal shall lie from a decision under this Article and such decision shall be carried out in accordance with the provisions of Chapter I of this Book.

Prosecution and Inquiry:Setting in Motion Prosecution and Inquiry Setting justice in motion


 Police Investigation

Art. 22 Principle.


(1) Whenever the police know or suspect that an offence has been committed, they shall proceed to investigate in accordance with the provisions of this Chapter.
(2) Investigation into offences committed by young persons shall be carried out in accordance with instructions given by the court under Art. 172 (2) .

Art. 23. __ Duty of police to investigate.

Investigating police officers shall carry out their duties under this Chapter not withstanding that they are of opinion that the accusation, complaint or information they may have received is open to doubt.

Art. 24. __ recording of statement.

After having recorded an accusation or complaint in the manner laid down in Art. 14, the investigating police officer shall elicit from the person making the accusation or complaint all relevant facts and dates, the name or description of the offender, the names and addresses of principal witnesses and all other evidence which may be available and shall record them.

Art.25.___ Summoning of accused or suspected person.

Where the investigating police officer has reason to believe that a person has committed an offence, he may be written summons require such person to appear before him.

Art 26. __ Arrest

(1) Where the accused or the suspect has not been arrested and the offence is such as to justify arrest or where the person summoned under Art. 25 fails to appear, the investigating police officer shall take such steps as are necessary to effect his arrest.
(2) Where the arrest cannot be made without warrant, the investigating police officer shall apply to the court for a warrant of arrest in accordance with the provisions of Art. 53.

Art. 27.__ Interrogation.

(1) Any person summoned under Art. 25 or arrested under Art. 26,50 or 51 shall, after his identity and address have been established. Be asked to answer the accusation or complaint made against him.
(2) He shall not be compelled to answer and shall be informed that he has the right not to answer and that any statement he may make may be used in evidence.
(3) Any statement which may be made shall be recorded.
(4) Where the arrested person is unable properly to understand the language in which his answers are to be recorded, he shall be supplied with a competent interpreter, who shall certify the correctness of all questions and answers.

Art. 28. __ Release on bond.

(1) Where the offence committed or complained of is not punishable with rigorous imprisonment as a sole or alternative punishment; or where it is doubtful that an offence has been committed or that the summoned or arrested person has committed the offence complained of, the investigating police officer may in his discretion release such person on his executing a bond with or without sureties that he will appear at such place, on such day and at such time as may be fixed by the police.
(2) Where the accused is not released on bond under this article, he may apply to the court to be released on bail in accordance with the provisions of Art. 64.

Art. 29__ Procedure after arrest

(1) Where the accused has been arrested by the police or a private person and handed over to the police (Art. 58) the police shall bring him before the nearest court within forty eight hours of his arrest or so soon thereafter as local circumstances and communications permit. The time taken in the journey to the court shall not be included.
(2) The court before which the accused is brought may make any order it thinks fit in accordance with the provisions of Art. 59.

Art. 30__ Examination of witnesses by the police.

(1) The investigating police officer may, where necessary, summon and examine any person likely to give information on any matter relating to the offence or the offender.
(2) Any person so examined shall be bound to answer truthfully all questions put to him. He may refuse to answer any question the answer to which would have a tendency to expose him to a criminal charge.
(3) Any statement which may be made shall be recorded.

Art. 31.___ No inducement to be offered.

(1) No police officer or person in authority shall offer or use or make or cause to be offered, made or used any inducement, threat, promise or any other improper method to any person examined by the police.
(2) No police officer or other person shall prevent or discourage by whatever means any person from making or from requiring to be recorded in the course of the police investigation any statement relating to such investigation which he may be disposed to make of his own free will.

Art. 32. __ Searches and seizures.

Any investigation police officer or member of the police may make searches or seizures in accordance with the provisions which follow;
(1) No arrested person shall be searched except where it is reasonably suspected that he has about his person any articles which may be material as evidence in respect of the offence with which he is accused or in suspected to have committed. A search shall be made by a person of the same sex as the arrested person.
(2) No premises may be searched unless the police officer or member of the police is in possession of a search warrant in the form prescribed in the third schedule to this code except where;
(a) An offender is followed in hot pursuit and enters premises or disposes of articles the subject matter of an offence in premises;
(b) Information is given to an investigating police officer or member of the police that there is reasonable cause for suspecting that articles which may be material as evidence in respect of an offence in respect of which an accusation or complaint had been made under art. Of this Code and the offence is punishable with more than three years imprisonment, are concealed or lodged in any place and he has good grounds for believing that by reason of the delay in obtaining a search warrant such articles are likely to be removed.

Art. 33.__ Issue of search warrant.

(1) A search warrant may be issued by any court. No search warrant shall be issued unless the court is satisfied that the purposes of justice or of any inquiry, trial or other proceedings under this code will be served by the issue of such warrant.
(2) Every search warrant issued shall specify the property to be searched for and seized and no investigating police officer or member of the police may seize any property other than that specified in such warrant.
(3) On seizing any property such investigating police officer or member of the police shall make a list of the property seized and where possible shall have the list checked and signed by an independent person. Any property seized which is required for the trial shall be preserved in a safe place until handed over to the court as an exhibit. Any property not so required may be returned to the person from whom it was taken and a receipt shall be taken
(4) In effecting a search the investigating police officer or member of the police may use such force as is necessary and may where access to premises is denied use reasonable force to affect entry.
(5) Unless otherwise expressly ordered by the court, searches shall be carried out only between the hours of 6 A.M. and 6 P.M.
Art. 34.__ Physical examination
(1) Notwithstanding the provisions of Art. 20 Civil Code where an investigating police officer considers it necessary, having regard to the offence with which the accused is charged, that a physical examination of the accused should be made, he may require a registered medical practitioner to make such examination and require him to record in writing the results of such examination. Examination under this Article shall include the taking of a blood test.
(2) An investigating police officer may, with the agreement of the victim of an offence or, where he is incapable with the consent of the parent or guardian, require a registered medical practitioner to make such physical examination as the offence being inquired into would appear to require. He shall require the registered medical practitioner to record in writing the results of such examination.
Art.35. Power of court to record statements and confessions
(1) Any court may record any statement or confession made to it at any time before the opening of a preliminary inquiry or trial.
(2) No court shall record any such statement or confession unless, upon questioning the person making it, it ascertains that such person voluntarily makes such statement or confession. A note to this effect shall be made on the record.
(3) Such statement or confession shall be recorded in writing and in full by the court and shall thereafter be read over to the person making the statement or confession, which shall sign and date it. The statement shall then be signed by the president of the court.
(4) A copy of the record shall then be sent to the court before which the case is to be inquired into or tried, and to the public prosecutor.
Art. 36 __ Diary of investigation
(1) Every police officer making a police investigation under this Chapter shall day by day enter his proceedings in the investigation in a diary setting forth:
(a) The day on which he started and closed his investigation and
(b) All the steps taken in the course of the investigation; and
(c) The circumstances which the investigation disclosed; and
(d) All the means of evidence which may have been collected.
(2) He shall enter in the diary any order which he may have received from a court or the public prosecutor in the course of the investigation.
Art. 37 Repot of police investigation.
(1) Every police investigation under this Chapter shall be completed without unnecessary delay.
(2) As soon as the investigation is completed, the investigation police officer shall forward to the public prosecutor a report setting forth;
(a) The name of the parties; and
(b) The nature of the information and the names of all persons who appear to be acquainted with the circumstances of the case; and
(c) All the means of evidence which have been collected.
(3) The report shall specify all the steps which may have been taken with a view to preservation or otherwise.
Art. 38. – Action by public prosecutor on receiving report.
On receiving the report under Art. 37 the public prosecutor may:
A) Prosecute the accused on a charge drawn up by him under Art.109-122; or
B) Order that a preliminary inquiry be held under Art.80-93;or
C) Order further investigations; or
D) Refuse to institute proceedings under Art. 42
Art. 39. Closure of police investigation file
(1) The public prosecutor shall close the police investigation file where the accused:
(a) Has died ;or
(b) Is under nine years of age or
(c) Cannot be prosecuted under any special law or under public international law (diplomatic immunity)
(2) The provisions of art. 43-45 shall not apply where the case file is closed under this article.
(3) On closing the case file. The public prosecutor shall send a copy of his decision to the Advocate General. The private complainant, if any and the investigating police officer.
Chapter 3. Institution of Proceedings

Art. 40 Duty to institute proceedings

(1) Subject to the provisions of Art. 42 the public prosecutor shall institute proceedings accordance with the provisions of this Chapter whenever he is of opinion that there are sufficient grounds for prosecution the accused.
(2) The public prosecutor shall not institute proceedings against a young person unless instructed so to do by the court under Art. 172.

Art. 41 Doubtful cases.

Where it is not clear whether proceedings should be instituted, the public prosecutor shall refer the matter for instructions to the Advocate General.
Art 42. Cases where proceedings shall not be instituted
(1) No proceedings shall be instituted where:
(a) The public prosecutor is of opinion that there is not sufficient evidence to justify a conviction; or
(b) There is no possibility of finding the accused and the case is one which may not be tried in his absence; or
(c) The prosecution is barred by limitation or the offence is made the subject of a pardon or amnesty: or
(d) The public prosecutor is instructed not to institute proceedings in the public interest by the Minister by order under his hand.
(2) On no other grounds may the public prosecutor refuse to institute proceedings.
(3) The public prosecutor shall institute proceedings in cases affecting the Government when so instructed by the Minister.
Art. 44 Effect of refusal.
(1) Where the public prosecutor refuses to institute proceedings under Art. 42 (1)(a) in relation to an offence punishable on complaint only, he shall authorize in writing the appropriate person mentioned in Art.47 to conduct a private prosecution. A copy of such authorization shall be sent to the court having jurisdiction.
(2) Where the public prosecutor refuses to institute proceedings under Art. 42 (1) (a) in relation to an offence which is not punishable on complaint only, the appropriate person mentioned in art, 47 may, within thirty days from having received the decision of the public prosecutor apply for an order that the public prosecutor institute proceedings.
Art. 45 form of and decision an application
(1) An application under Art. 44(2) shall be made to the court to which an appeal lies from decisions of the court which would have had jurisdiction, had proceedings been instituted.
(2) The court shall, after considering the refusal of the public prosecutor to institute proceedings under Art.42(1) and the reasons therefor either confirm the decision of the public prosecutor or order him to institute proceedings ;
Art. 46 Liability of private prosecutor.
The private prosecutor authorized to conduct a private prosecution under art. 44(1) shall conduct the private prosecution at his peril and at his own expense.
Art. 47 Persons entitled to conduct private prosecutions.
No person other than:
(a) The injured party or his legal representative; or
(b) The husband or wife on behalf of the spouse; or
(c) The legal representative of an incapable person; or
(d) The attorney or a body corporate;
May conduct a private prosecution.
Art. 48 Stay of proceedings in private prosecution pending institution of proceedings by public prosecutor.
Where the evidence in a private prosecution discloses that a more serious offence has resulted than has been charged in a private prosecution, the public prosecutor may apply to the court to stay the proceedings pending the institution of fresh proceedings by the public prosecutor and the court shall thereon stay the proceedings

Execution of Sentences


Execution of Sentences .

– General Provisions Art.203. – Principle.
 
(1) Any court having passed a sentence in a criminal case shall issue the necessary warrants or orders requiring the appropriate authorities to carry out or supervise the carrying out of the sentence in accordance with the provisions of this Book.(2) Nothing in this Article shall affect the provisions of Art. 188. Art.204. – Warrant in respect of person sentenced to death. (1) Where any person is sentenced to death, the presiding judge shall by warrant under his hand in the form prescribed in the Third Schedule to this Code order such person to be detained until the pleasure of His Imperial Majesty shall be made known.(2) Where the sentence is confirmed, it shall be carried out in accordance with the conditions laid down in the order of confirmation.(3) Where the sentence is commuted, the order of commutation shall be sufficient authority for carrying into effect the terms of such order. Art.205. – Warrant in respect of person sentenced to loss of liberty. (1) Where any person is sentenced to arrest, imprisonment of internment, the presiding judge shall by warrant under his hand in the form prescribed in the Third Schedule to this Code order the sentence to be carried out.(2) Such warrant shall be sufficient authority for the officer in charge of the prison and all other persons to carry out the sentence described in the warrant. Art.206. – Execution may be postponed in certain cases. Where a person who has been sentenced to arrest or simple imprisonment not exceeding one year is:(a) a pregnant woman; or(b) the sole support of his family,and such person is not likely to be a danger to public security, the court may postpone the execution of the sentence for a period not exceeding six months on production of guarantors for his good behaviour. Art.207. – Warrant in respect of person sentenced to flogging. Where any person is sentenced to be flogged for an offence under Art. 635 (3) or 637 (1) Penal Code, the presiding judge shall by warrant under his hand in the sixteenth form prescribed by the Third Schedule to this Code order that the sentence be carried out in accordance with Art. 120A Penal Code by such person and at such place as shall be specified in the warrant. Art.208. – Warrant in respect of irresponsible persons. Where any person is found to be not fully responsible for his acts and the court decides that he be confined or treated in accordance with the provisions of Art. 134 or 135 Penal Code, the presiding judge shall by warrant under his hand in the fifteenth form prescribed in the Third Schedule to this code order that the accused be remanded to a suitable institution for confinement or treatment. Art.209. – Recovery of fines. (1) Fines shall be recovered on the order of the court by the execution officer in accordance with the provisions of Art. 91,171, (1), 703 and 710 Penal Code.(2) Where a fine or any part thereof has not been recovered, the execution officer shall refer the matter to the court and thereupon the court shall make the appropriate orders for execution or for the fine to be converted into labour, arrest or simple imprisonment in accordance with the provisions of Art. 92, 94, 96, 171 (2) and 709 Penal Code.(3) Where a person has been sentenced in his absence to pay a fine, the provisions of sub-art. (1) shall not apply and the court shall forthwith order that execution be levied on the convicted person’s property. Art.210. – Payment of costs and compensation. Where a judgment given by a criminal court contains provisions for the payment of legal costs or compensation, such part of the judgment as contains such provisions shall be executed in the same manner as a civil judgment. Art.211. – Confiscation of property. (1) Where an order for confiscation of property has been made under Art. 272 Penal Code, the court shall make an order requiring the execution officer to seize such property as is seizable under the provisions of Art. 97 Penal Code and shall specify in such order the property to be seized.(2) On seizing such property, the execution officer shall hold it until he receives an order from the competent authority requiring him to hand over such property to a person or persons named in such order and on so handing such property, the execution officer shall be given a detailed receipt by such person or persons.(3) The family of the convicted person may apply to the court for the release of any property wrongly confiscated. Art.212. – Sequestration of property. (1) Where a person is sentenced in his absence to have his property sequestrated for an offence as defined in Art. 272 Penal Code, the court shall make an order:(a) requiring the execution officer to attach such property as may be attached under Art. 98 Penal Code and shall specify in such order the property to be attached; and(b) appointing a trustee to manage the property and on such appointment the execution officer shall hand over the property to such trustee against a detailed receipt.(2) The execution officer shall be responsible for ensuring that none of the property mentioned in Art. 97 (3) Penal Code be attached. The family of the convicted person may apply to the trustee for the release of any property wrongly attached.(3) An order or attachment made under sub-art. (1) shall remain in force until an application for its removal is made to the court by the competent authority and thereupon the court shall order the attachment to be removed and the trustee discharged on submitting proper accounts. Art.213. – Orders in respect of young persons. (1) Where an order is made in respect of a young person under Art. 162, 165, 166, 173 or 703 Penal Code, the presiding judge shall sign and send an order to the responsible official, headmaster, director or officer in charge, as the case may be, and such order shall be sufficient authority to deal with young person on the conditions laid down in the order.(2) Where an order is made in respect of a young person under Art. 163 Penal Code, the presiding judge shall sign and send an order to one of the persons mentioned in Art. 163 Penal Code and such order shall be sufficient authority to deal with the young person on the conditions laid down in the order.(3) Where a young person is sentenced to caning under Art. 72 Penal Code, the presiding judge shall cause the young person to be medically examined as to his fitness to undergo corporal punishment and, where he has been found fit, he shall cause the caning to be carried out in a private place by a family elder or such other suitable person as the presiding judge shall appoint, in the presence of himself, the person who has examined the young person and the young person’s parents, relatives or guardian, if any. Art.214. – Compulsory labour, secondary penalties and measures. Where an order is made under Art. 102, 103, 122, 144, 146, 147, 149-154-158-160, 178, 179, 715, 716, or 718-720 Penal Code, the court shall cause a copy of the operative part of the judgment to be served on the appropriate authorities and require them to carry the order into effect. Art.215. – Recording of orders for execution. The court shall record any order it may have made with a view to the sentence being executed. A note shall be made of the day on which such order was executed and, where appropriate, of the reasons why such order could not be executed.

የአስተዳደር ውሳኔ ምንድነው?


አስተዳደራዊ ውሳኔ ምንድነው?

‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ በአስተዳር ህግ ውስጥ ከቃል አጠቃቀም፣ ከይዘትና ከወሰን አንጻር ቁርጥ ያለ መደብ ከሌላቸው ፅንሰ ሀሳቦች መካከል ጎልቶ ይወጣል፡፡ ውስብስብነቱ ከፅንሰ ሀሳቡ ወካይ ስያሜ ይጀምራል፡፡ ‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ በሚል እዚህ ላይ መጠቀሱም በአገራችን የአስተዳደር ህግ ውስጥ መደበኛ መጠሪያው ቢሆን ይበጃል በሚል ብቻ ነው፡፡ ጀርመኖች እንኳን የራሳቸውን ወካይ ቃል መፍጠር ተስኗቸው አሁን ላይ በአስተዳደር ህጋቸው ዐቢይ ስፍራ ይዞ የሚገኘውን ‘Administrative act’ (Verwaltungsakt) በሚል የሚጠሩትን ፅንሰ ሀሳብ ለማዳበር ከፈረንሳዮች acte administrative ለመዋስ ተገደዋል፡፡

‘Administrative act’ (Verwaltungsakt) is a core concept of the German administrative law. It covers most of the actions of the administrative authorities through which they affect the legal interests of an individual. The origin of this concept is traced from the French concept of acte administratif from which it was borrowed by the German jurists and developed into a German concept since 1826 onwards.a

በእንግሊዝኛው ፍቺ ከወሰድነው Administrative Decision በይዘቱ Administrative Act ውስጥ የሚጠቃለል ሲሆን ዘርፈ ብዙ መልክ ካላቸው አስተዳደራዊ ተግባራት መካከል አንድ ነጠላ ተግባርን ብቻ ይወክላል፡፡ ሆኖም ለአገራችን የአስተዳደር ህግ ‘አስተዳደራዊ ተግባር’ ወይም ‘አስተዳደራዊ ድርጊት’ የሚለውን ቃል ብንጠቀም ገላጭነቱ አይጎላም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አስተዳደራዊ ድንጋጌ ማውጣት እንዲሁም ምርመራ፣ ቁጥጥርና ክትትል ሁሉም የአስተዳደር ተግባራት እንደመሆናቸው ዳኝነታዊ ባህርይ ያላቸውን ተግባራት ለይቶ ለማመልከት ውስን ይዘት ያለውን ቃል መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንጻር በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ‘የአስተዳደር ውሳኔ’ ወይም ‘አስተዳደራዊ’ ውሳኔ የሚለው ቃል ዳኝነታዊ ባህርይ ያላቸውን ተግባራት ለመግለጽ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ሆኖም በመደበኛ ትርጓሜው አደናጋሪ መልዕክት ስለሚፈጥር ይዘቱንና ፍቺውን በቅድሚያ መወሰን ያስፈልጋል፡፡

እ.ኤ.አ. በ1976 ዓ.ም. በወጣው የጀርመን የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ የአስተዳደር ተግባር (Administrative act) የሚከተለው ፍቺ ተሰጥቶታል፡፡

Administrative act is every order, decision or other sovereign measure taken by an authority for the regulation of a particular case in the sphere of public law and directed at immediate external legal consequences.b

ወደ አማርኛ ስንመልሰው፤

የአስተዳደር ተግባር ማለት ቅርብና ውጫዊ የህግ ውጤት የሚያስከትል በህዝብ አስተዳደር ህግ ማዕቀፍ ውስጥ አንድን ልዩ ሁኔታ ለመቆጣጠር ሲባል ስልጣን ያለው አካል የሚሰጠው ትዕዛዝ፣ ውሳኔ ወይም ሌላ ማናቸውም ሌላ ሉዓላዊ እርምጃ ነው፡፡

በትርጓሜው ውስጥ ተጨማሪ ሰፊ ማብራሪያ የሚሹ ንዑስ ሀሳቦች ታጭቀዋል፡፡ ሆኖም በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል በጀርመን የአስተዳደር ህግ የአስተዳደር ተግባር ማለት ህግ ለማስፈጸምና የአስተዳደር ስራ ለማከናወን ስልጣን የተሰጣቸው ተቋማት ይህን ህዝባዊ ስልጣናቸውን (public functions) በመገልገል የሚሰጡትን ትዕዛዝ፣ ውሳኔ ወይም ማናቸውም በማድረግ፣ ባለማድረግ የሚገለጽ እርምጃ ሁሉ ያጠቃልላል፡፡ ይህም ማለት በውል ወይም ከውል ውጪ ኃላፊነት ህጎች ስር የሚሸፈኑ ግላዊ ድርጊቶች፣ ውሳኔዎች፣ እርምጃዎች ወዘተ…በአስተዳደር ተግባር ስር አይሸፈኑም፡፡

በትርጓሜው ላይ ‘ልዩ ሁኔታ ለመቆጣጠር’ ሲባል ተግባሩ ህጋዊ ውጤት እንደሚያስከትል ወሰኑም በአንድ ልዩ ሁኔታ ላይ ያነጣጠረ እንጂ ጠቅላላ ተፈጻሚነት እንደሌለው ያመለክታል፡፡ ስለሆነም የበታች ሠራተኛ ለበላይ ኃላፊ የሚያቀርበው የውሳኔ ሀሳብ፣ ሪፖርት ወይም የምርመራ ውጤት ራሱን ችሎ ህጋዊ ውጤት የማይከተለው በመሆኑ እንደ አስተዳደራዊ ተግባር አይቆጠርም፡፡ በአንድ ዘርፍ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ የተወሰደ እርምጃ (ለምሳሌ ስጋ ሻጮች ማሟላት ያለባቸው የጥራት ደረጃ) ከላይ በተቀመጠው ትርጓሜ ውስጥ አይወድቅም፡፡ ምክንያቱም ተፈጻሚነቱ ሁሉንም የዘርፍ ነጋዴዎች ስለሚያቅፍ ጠቅላላነት ይታይበታል፡፡ በመጨረሻም ህጋዊ ውጤቱ በአስተዳደሩ ውስጣዊ መዋቅር ተወስኖ የሚቀር (ለምሳሌ በአንድ ነጋዴ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የበላይ ኃላፊው ለበታች ሠራተኛ የሚያስተላልፈው ማሳሰቢያ) ከሆነ በአስተዳደራዊ ተግባር ውስጥ አይመደብም፡፡

የአሜሪካው የፌደራል አስተዳር ስነ ስርዓት ህግ ተፈጻሚነቱ አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (rule making) እና አስተዳደራዊ ዳኝነት (adjudication) የመስጠት ሂደቶች ላይ ነው፡፡ በህጉ ላይ በተሰጠው ፍቺ አስተዳደራዊ ዳኝነት ማለት በውጤቱ ‘ትዕዛዝ’ የሚያቋቁም የአስተዳደር ሂደት (agency process for the formulation of an order) ነው፡፡ ትዕዛዝ የሚለው ቃል በአስተዳደር ስነ ስርዓት ህጉ ላይ ፍቺ የተሰጠው ሲሆን ይዘቱ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡

order means the whole or a part of a final disposition, whether affirmative, negative, injunctive, or declaratory in form, of an agency in a matter other than rule making but including licensing.c

‘ትዕዛዝ’ ከጀርመኑ ‘የአስተዳደር ተግባር’ ጋር ሲነጻጸር መሰረታዊ ልዩነት አይታይበትም፡፡ ጉዳዩን የሚቋጭ የመጨረሻ መሆኑ ህጋዊ ውጤት እንደሚከተለው ይጠቁመናል፡፡ በይዘቱ አንድ ድርጊት እንዳይፈጸም፣ እንዲፈጸም ወይም የአንድ ሁኔታ (መብት) መኖር/አለመኖር የሚያረጋግጥ መግለጫ ወይም ከአስተዳደራዊ ድንጋጌ ማውጣት ውጪ ያለ ማንኛውም የመጨረሻ እልባት የሚሰጥ ነው፡፡

በመቀጠል የአገራችን የፌደራል ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ (1993) የተጠቀመውን ቃል እና አፈታቱን እናያለን፡፡ በረቂቅ አዋጁ የትርጓሜ ክፍል አንቀጽ 2 /2/ እንደተመለከተው አስተዳደራዊ ውሳኔ ማለት፤

ማናቸውም አስተዳደራዊ ባህርይ ያለውን ተግባር ወይም ነገር ከመፈጸም ጋር የተያያዘ ውሳኔ ወይም ውሳኔ አለመስጠትን ጨምሮ ቅጣትን ለመጣል፣ ወይም መፍትሔ ለመስጠት ወይም የመከላከል ዓላማ ወይም ውጤት ያለው በአስተዳደር ተቋማት የሚሰጥ ማናቸውም ውሳኔ፣ ትዕዛዝ ወይም ብይን [ነው፡፡]

የትርጓሜውን ይዘት ይበልጥ ለመረዳት የእንግሊዝኛውን ቅጂ መመልከቱ ጠቃሚ ነው፡፡

Administrative Decision means any decision, order or award of an agency having as its object or effect the imposition of a sanction or the grant or refusal of relief, including a decision relating to doing or refusing to do any other act or thing of an administrative nature, or failure to take a decision

በቀጣይ በ2001 ዓ.ም. በተዘጋጀው ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ አዋጅ አርቃቂዎቹ የተለየ አገላለጽ መጠቀም መርጠዋል፡፡ በረቂቁ አንቀጽ 2/2/ ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንደሚከተለው ተተርጉሟል፡፡

አስተዳደራዊ ውሳኔ ማለት ተጨባጭ ሕጋዊ ግንኙነቶችን ለመመስረት፣ ለማሻሻል፣ በምርመራ ለማረጋገጥ ወይም የተሟላ ለማድረግ ለአንድ ጉዳይ የተወሰነ መፍትሔ የመስጠት ዓላማ ያለውና በግለሰብ ወይም በተወሰኑ ሰዎች ላይ ተፈጻሚነት ያለው በተቋሙ የሚሰጥ ሕጋዊ ውሳኔ ሲሆን፣ አስተዳደራዊ ባህርይ ባለው ተግባር ወይም ጉዳይ ላይ ውሳኔ አለመስጠትንም ይጨምራል፡፡

በሁለቱም ረቂቆች ላይ የሚታየው ገላጭነት የጎደለው የቋንቋ አጠቃቀም አብዛኛው ሰው በቀላሉ አይረዳውም፡፡ ከዚህም አልፎ የህግ ባለሞያዎች፣ ዳኞች እና አስተዳዳሪዎች በጋራ የሚያግባባ አገላለጽ አልያዘም፡፡ ለምሳሌ በተለምዶ ሰርኩላር በሚል ስያሜ ጠቅላላ ተፈጻሚነት ኖሯቸው የሚተላፉ ትዕዛዞች የአስተዳደራዊ ውሳኔና የአስተዳደራዊ ድንጋጌ ከፊል ባህርያት ይጋራሉ፡፡ ሆኖም በአንደኛው ስር ለመፈረጅ ሁለቱም ትርጓሜዎች ግልጽ መለያ መስፈርት አላካተቱም፡፡ ለአስተዳደራዊ ውሳኔ ትርጓሜ ለማበጀት ጥሩ መነሻ የሚሆነው የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው፡፡ ሁለቱን የሚያመሳስላቸው ብዙ ነጥቦች አሉ፡፡ አስተዳደራዊ ሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሁለቱም ምንጫቸው ዳኝነታዊ ስልጣን ነው፡፡ በዳኝነት ፍሬ ነገሩን የማረጋገጥና በተረጋገጠው ፍሬ ነገር ላይ ህጉን ተፈጻሚ የማድረግ ተግባራት ይከናወናሉ፡፡ ዓላማው አከራካሪ የሆነ አንድ ተለይቶ የታወቀ ጉዳይ (particular case) መቋጨት ነው፡፡ ጉዳዩን በመቋጨት የሚነገረው ትዕዛዝ፣ ብይን ወይም ውሳኔ በባለጉዳዮች ወይም ሶስተኛ ወገኖች ላይ ህጋዊ ውጤት ያስከትላል፡፡ እነዚህ ወሳኝ ባህርያት በጀርመኑ እና የአሜሪካው የአስተዳደር ህጎች ላይ በግልጽ ተለይተዋል፡፡

በአንድ የአስተዳደር መ/ቤት የተፈጸመ ተግባር የአስተዳደር ውሳኔ ነው ወይስ አይደለም? የሚለው ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ውስጥ መሰረታዊ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ጥያቄው ተቋሙ ካሉት ጠቅላላ የማስተዳደር (ህግ ማስፈጸም)፣ ከፊል የህግ አውጭነት እና ከፊል የዳኝነት ስልጣናት መካከል የትኛውን እየተገለገለ እንደሆነ የሚለይበት ነው፡፡ የጥያቄው ሌላ መልክ ሲታይ ተቋሙ የፈጸመው ተግባር በባህርዩ ዳኝነታዊ ነው ወይስ አይደለም? የሚለውን ጥያቄ ይመልሳል፡፡ የውሳኔ ሰጭውን የስልጣን እና የተግባር ዓይነት መለየት በህጉ የአፈጻጸም ወሰን ላይ የራሱ ጉልህ እንደምታዎች አሉት፡፡ ጠቅለል ባለ አነጋገር የአስተዳደር መ/ቤቶች ዳኝነታዊ ወይም የህግ አውጭነት ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ጊዜ ካልሆነ በስተቀር ሙሉ በሙሉ በአስተዳደር ስልጣን ውስጥ የሚወድቁት ድርጊቶች በመደበኛ ፍ/ቤቶች ቁጥጥር ሊደረግባቸው አይችልም፡፡ በሌላ አነጋገር አስተዳደራዊ ውሳኔ ወይም ድንጋጌ ባልሆነ ጉዳይ ላይ የአጣሪ ዳኝነት ስልጣን አይኖራቸውም፡፡ የአስተዳደር መ/ቤቶች ዳኝነታዊ ስልጣናቸውን ተጠቅመው አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሰጡ መሰረታዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎች ተፈጻሚ መሆን ይጀምራሉ፡፡

ባህርያትና የስልጣን ምንጭ፣


⚖️ ባህርያትና የስልጣን ምንጭ   

አስተዳደራዊ ድንጋጌ ማለት ከህግ አውጭው በተሰጠ የውክልና ስልጣን ገደብ ውስጥ በስራ አስፈፃሚውና የአስተዳደር መ/ቤቶች የሚወጣ የበታች ህግ (subordinate legislation) ነው፡፡ በውክልና ህግ ማውጣት የአስተዳደር ህግ አይነተኛ መገለጫ ነው፡፡ የስራ አስፈፃሚው አካል ህግ የማውጣት ስልጣን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣት የነፃ ገበያ ክስተትን ተከትሎ የመጣው ዘመናው የማህበራዊ ደህንነት መንግስት (welfare state) ካስመዘገባቸው እድገቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡

በውክልና ህግ ለማውጣት ዋናው የስልጣን ምንጭ ህግ አውጭው እንደመሆኑ የተወካዮች ም/ቤት በማያወላውልና ግልጽ በሆነ መልኩ ስልጣኑን በከፊል ቆርሶ ለሚኒስትሮች ም/ቤት ወይም ለአስተዳደር መ/ቤቶች ካልሰጠ እነዚህ አካላት ከህገ መንግስት የመነጨ የህግ አውጭነት ስልጣን የላቸውም፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የሚኒስትሮች ም/ቤት ሆነ የአስተዳደር መ/ቤቶች ደንብና መመሪያ እንዲያወጡ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ስልጣን አይሰጣቸውም፡፡ በፌደራል ደረጃ ህግ የማውጣት ስልጣን የተወካዮች ም/ቤት ሲሆን በክልል ደረጃ ደግሞ የክልሉ ምክር ቤት ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ህግ የማውጣት ስልጣን የተሰጠው አካል በህገ-መንግስቱ ላይ የለም፡፡

የውክልና ስልጣን በሌለበት ሁኔታ የሚወጣ ማንኛውም ደንብ ሆነ መመሪያ ከስልጣን በላይ እንደመሆኑ የህጋዊነት መስፈርትን አያሟላም፡፡ በእርግጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፓርላማው ፀድቆ ከታወጀ የሚኒስትሮች ም/ቤት ውስን ለሆነ ጊዜ ሲቪል እና ፖለቲካዊ መብቶችን ደንብ በማውጣት ሊገድብ ይችላል፡፡ ከዚህ ውጭ የሚኒስትሮች ም/ቤት በቀጥታ ደንብ ለማውጣት የሚችልበት ህገ መንግስታዊ ስልጣን የለውም፡፡

የስልጣኑ ምንጩ የተወካዮች ም/ቤት ብቻ ነው ከተባለ ይህ አካል ስልጣኑን በከፊል ቆርሶ በውክልና ማስተላለፍ ይችላል? የሚለውን ጥያቄ መመርመሩ ተገቢ ሆናል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ላይ ይህን የሚፈቅድለት ግልጽ ድንጋጌ የለም፡፡ ብዙዎች የመስኩ ምሁራን እንደሚስማሙበት ግን ህግ አውጭው ስልጣኑን በከፊል በውክልና ለማስተላለፍ ከህግ አውጭነቱ የሚመነጭ ስልጣን (inherent power) አለው፡፡ እንዲያም ሆኖ ያለገደብ ከህዝብ የተሰጠውን ስልጣን በውክልና ስም ሊያስተላልፍ አይችልም፡፡

በመሰረቱ በውክልና ስልጣን የሚወጣ ህግ ከመንግስት አስተዳደር እየተለጠጠ መምጣት ጋር ተያያዥ የሆኑ አስገዳጅ ሁኔታዎች ያመጡት ክስተት ነው፡፡ ስለሆነም እንደ ልዩ ሁኔታ እንጂ በመርህ ደረጃ ተቀባይነት የለውም፡፡ ህግ አውጭው ምንም እንኳን በከፊል ስልጣኑን ማስተላለፍ ቢኖርበትም የፖሊሲ ጥያቄዎችን የሚነኩ መሰረታዊ ጉዳዮች በደንብ ወይም በመመሪያ እንዲወሰኑ ውክልና መስጠት የለበትም፡፡ የተፈጻሚነቱ ወሰኑ በህግ አውጪው በሚወጣው ህግ ላይ የሚታዩ ቀዳዳዎችን ለመድፈን ብሎም የፖሊሲ ጥያቄዎችን በማይነኩ ዝርዝርና ጥቃቅን ቴክኒካል ጉዳዮች መገደብ አለበት፡፡ ከዚህ አንጻር አፈጻጸሙ በጠባቡ ሊሆን ይገባዋል፡፡


አስፈላጊነት

ብቁና ውጤታማ አስተዳደር እንዲሰፍን የአስተዳደር መ/ቤቶች በህግ የተሰጣቸውን ስልጣን፣ ተግባርና ግዴታ በተጨባጭ ማሳካት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ስኬት እንዲኖር ደግሞ የማስፈፀም ስልጣን ብቻውን በቂ አይሆንም፡፡ ጠቅለል ያለ ይዘት ያላቸው በፓርላማ የሚወጡ ህጐች የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ከመጠቆም ባለፈ ቴክኒካልና ዝርዝር ጉዳዮችን ስለማይዳስሱ በየጊዜው ለሚነሱ ችግሮች ወቅታዊና ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት ይሳናቸዋል፡፡ ስለሆነም አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት ስልጣን አስፈላጊነት ከሁለት አቅጣጫዎች ማለትም ከአስተዳደር ስራ ውጤታማነት እና ከህግ አውጭው ውስንነት አንፃር ሊቃኝ ይችላል፡፡

አስፈላጊነቱ ጎልቶ ቢታይም በመስኩ ሊቃውንት ጠንካራ ተቃውሞ ሳይገጥመው አልቀረም፡፡ እንደ ብዙዎች እምነት የአስተዳደር መ/ቤቶች ህግ የማውጣት ስልጣን በዜጐች መብት ላይ በሩን ዘግቶ ወደ አምባገነናዊነት የሚያመራ አደገኛ አካሄድ ነው፡፡ ተቃውሞው መሰረቱ ንድፈ ሀሳባዊ ሲሆን የስልጣን ኢ-ተወካይነት ንድፈ ሀሳብ (theory of non delegability of power) አንዱ ነው፡፡ በላቲን potestas delegari non potest delegare ተብሎ ሲጠራ በእንግሲዝኛው power once delegated should not be re-delegated የሚል ይዘት አለው፡፡ ይህም ወደ አማርኛ ሲመለስ ‘በውክልና የተሰጠ ስልጣን እንደገና በውክልና ሊተላለፍ አይችልም’ እንደ ማለት ነው፡፡ በአጭር አገላለፅ ህግ አውጭው ህግ የማውጣት ስልጣኑን የሚያገኘው ከመራጩ ህዝብ እንደመሆኑ ይህን በአደራ የተቀበለውን ስልጣን እንደገና (በድጋሚ) በውክልና ማስተላለፍ የለበትም ማለት ነው፡፡a

የህግ አውጭነት የስልጣን ምንጩ ህዝብ ነው፡፡ የአንድ አገር ህዝብ ተወካዮቹን ሲመርጥ ችሎታና ብቃታቸውን መሰረት አድርጐ ‘ያስተዳድሩኛል፤ ለእኔ ይሰሩልኛል፣ ትክክለኛውን ህግ ያወጡልኛል’ በሚል እምነት ጥሎባቸው ነው፡፡ ህግ አውጭው በውክልና በአደራ ከህዝቡ የተቀበለውን ስልጣን በአግባቡ በመገልገል ልማት፤ እድገት፤ ፍትህ፣ መልካም ስርዓትና ሰላም የሚያሰፍኑ ህጐችን ማውጣት አለበት፡፡ ህዝቡ ድምፁን ሰጥቶ ተወካዮቹን ሲመርጥና ስልጣን ሲሰጥ ይህን የህግ አውጭነት ስልጣን ላልተመረጡ ግን ለተሾሙ ስራ አስፈፃሚዎች በውክልና እንዲያስተላልፉት አይደለም፡፡ ከዚህ ሀሳብ በተቃራኒ ስልጣን በውክልና ከተላለፈ ህዝቡ ድምፅ ሰጥቶ ባልመረጣቸው ስራ አስፈፃሚዎች እየተገዛ ነው፡፡

ሁለተኛው የውክልና ህግ ንድፈ ሀሳባዊ ተቃውሞ ከስልጣን ክፍፍል መርህ (separation of powers) የሚነሳ ሲሆን ዞሮ ዞሮ መሰረቱ የአስተዳደር በደል እንዲንሰራፋ ያደርጋል የሚል ነው፡፡ በስልጣን ክፍፍል መርህ መሰረት ህግ ማውጣት ለህግ አውጭው፤ ህግ መተርጐም ለፍርድ ሰጭው፤ ህግ ማስፈፀም ለአስፈፃሚ ተብሎ የእያንዳንዱ የመንግስት አካል ስልጣኑ ተመድቦና ተለይቶ ተሰጥቷል፡፡ አንድ የመንግስት አካል በተደራራቢነት ከአንድ በላይ ስልጣን የያዘ እንደሆነ ከራሱ በላይ ተቆጣጣሪ የሌለው ስልጣኑን እንዳሻው የሚጠቀም አምባገነን ይሆናል፡፡ ስለሆነም ስራ አስፈፃሚው ከተመደበለት ህግ የማስፈፀም ተግባር በተጨማሪ በደንብና መመሪያ ስም ህግ የሚያወጣ ከሆነ ሁለት የመንግስት ስልጣናትን ደርቦ ስለመያዙ ያም የስልጣን ክፍፍል መርህን መጣሱ ግልጽነቱ ጐልቶ የሚታይ ሀቅ ነው፡፡

ከላይ በተጠቀሱት ሁለት ንድፈ ሀሳብ ተቃውሞዎች መሰረት በውክልና የሚወጣ ህግ አስተዳደራዊ አምባገነናዊነት፤ የአስተዳደር ብልሹነት እና በስልጣን አለአግባብ መገልገል እንዲሰራፋ ያደርጋል በሚል ከመስኩ ባለሙያዎች የሰላ ሂስና ትችት ሲገጥመው ቆይቷል፡፡ ለምሳሌ እንግሊዝ አገር ውስጥ ሎርድ ሄዋርት የተባሉ የተከበሩ ዳኛና ምሁር በአገራቸው በየጊዜው በፍጥነት እያደገ የመጣውን የአስተዳደር መ/ቤቶች በውክልና ህግ የማውጣት ስልጣን ‘The New Despotism’ በሚለው መጽሐፋቸው እ.ኤ.አ. በ1931 ዓ.ም. ያቀረቡት ጠንካራ ተቃውሞ የእንግሊዝ ፓርላማ ስለጉዳዩ የሚያጠና አጣሪ እንዲሾምና ምርመራ እንዲያደርግ ምክንያት ሆኗል፡፡b ይሁን እንጂ ከምርመራው በኋላ የቀረበው የምርመራ ሪፖርት (Committee on Ministers’ Powers Report) የደረሰበት ድምዳሜ የውክልና ህግ እንግሊዝ ውስጥ በፍጥነት እያደገ መሆኑን ይህም በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ ተቀባይነት እንደሌለው ካተተ በኋላ በተግባር ግን የግድ አስፈላጊና መቅረት የሌለበት አሰራር መሆኑን በአጽንኦት ገልጿል፡፡c

ከላይ የቀረቡት ንድፍ ንድፈ ሀሳባዊ ተቃውሞዎች አሳማኝ የመሆናቸውን ያህል እየተወሳሰበ ከመጣው የመንግስት አስተዳደር ጋር ተያይዘው የሚነሱ ተግባራዊ ምክንያቶች አስፈላጊነቱን አይቀሬና የበለጠ አሳማኝ አድርገውታል፡፡ የአስተዳደር መ/ቤቶች በህግ አውጭው በሚወጡት አዋጆች ላይ ብቻ ተንተርሰው ውጤታማ አስተዳደር ማስፈን አይቻላቸውም፡፡ በተለያዩ አገራት እንደታየው ህግ አውጭው ከሚያወጣቸው ህጐች በበለጠ የአስተዳደር መ/ቤቶች የሚያወጧቸው መመሪያዎች በፍጥነት እየበዙ መጥተዋል፡፡d በየጊዜው እያደገና እየተወሳሰበ የመጣው የመንግስት አስተዳደር ስራና የህግ አውጭው ለዚህ ስራ ውጤታማነት የሚያግዙ ህጐችን በአይነትና በጥራት ለማቅረብ አለመቻል በውክልና ስልጣን የሚወጣ ህግ አማራጭ ሳይሆን የግድ መሆኑን ያሳየናል፡፡

ለዚህም ይመስላል ታዋቂው የአስተዳደር ህግ ምሁር ደብሊው ኤች. አር. ዌድ በውክልና የሚወጣ ህግን “መጥፎ ግን አስፈላጊ” (necessary evil) ሲል የሚገልፀው፡፡e ከህግ አውጭው በሚሰጥ ውክልና ህግ የማውጣት ስልጣንን በተግባር አስፈላጊ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የሚከተሉት በዋነኛነት ይጠቀሳሉ፡፡

የግዜ እጥረት፣

ህግ አውጭው ስልጣኑን በከፊል ቆርሶ በውክልና ለማስተላፍ ከሚገደ`ድባቸው ምክንያቶች አንዱ ከራሱ ከህግ አውጭነቱ የሚመነጭ ችግር ነው፡፡ አንድን አዋጅ ለመደንገግ ከሚወስደው ረጅም ጊዜና ተፈጻሚ ከሚሆነው የጠበቀ የስነ-ስርዓት አካሄድ አንጻር ውስብስብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ህጐችን በብዛትና በጥራት ለማውጣት አስቸጋሪ ነው፡፡f የተወካዮች ም/ቤትን ያየን እንደሆነ ከሁለት ወራት የክረምት የእረፍት ጊዜ በኋላ በመካከል ለአንድ ወር ለእረፍት ሲበተን ጠቅላላ የስራ ጊዜው ከዘጠኝ ወራት አይበልጥም፡፡g ከዘጠኙ ወራት ውስጥ ቅዳሜና እሁድ ተቀንሰው በሚቀሩት የስራ ቀናት ባሉት አጭር የስራ ሰዓታት ለአገሪቱ አስፈላጊ አዋጆችን ማውጣት አዳጋች ነው፡፡ የመስኩ ምሁራን እንደሚስማሙበት የአንድ አገር ፓርላማ ለተከታታይ 365 ቀናት ድፍን 24 ሰዓታት በስራ ላይ ቢቆይ እንኳን በብዛትና በጥራት ለአገሪቱ አስፈላጊ የሆኑ ህጐችን ማቅረብ ይሳነዋል፡፡h

በተወሰኑ ዘርፎች የተወካዮች ምክር ቤት ያወጣቸው አዋጆች እና በውክልና የወጡ መመሪያዎች ቁጥር ብናነጻጽር ከጊዜ እጥረት ጋር በተያያዘ ያለውን ችግር በተግባራዊ ምልከታ ለመመዘን ያስችለናል፡፡ ምክር ቤቱ ከ1987 ዓ.ም. ጀምሮ ቀረጥና ታክስ በሚመለከት (ማሻሻያዎችን ጨምሮ) ያወጣቸው አዋጆች በቁጥር ከ25 አይበልጡም፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ እነዚህን ህጎች ለማስፈጸም በተለያየ ቅርጽና ስያሜ ተዋቅረው በነበሩትና በኋላም ከሐምሌ 2000 ዓ.ም. ጀምሮ ስልጣናቸውን አዋህዶ በተረከበው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣንi በውክልና ስልጣኑ 129j መመሪያዎች ወጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲሁ የባንክ፣ የመድን፣ የአነስተኛ ፋይናንስ እና የካፒታል ዕቃ ኪራይ ስራዎችን ለመቆጣጠር ከወጡ ወደ ሰባት የሚጠጉ አዋጆችና በሌሎች ልዩ ህጎች በተሰጠው ስልጣን ከ110 በላይ መመሪያዎችን አውጥቷል፡፡k ሌሎች የአስተዳደር መ/ቤቶች እያንዳንዳቸው በቁጥር ወደ 100 የሚጠጉ መመሪያዎች ባይኖራቸውም ከብዛታቸው አንጻር ጠቅላላ ድምሩ ከ1000 ያልፋል፡፡ በዚህ ላይ የሚኒስትሮች ምክር ቤት እስከ ጥር 2008 ዓ.ም. ድረስ ያወጣቸውን 371 ደንቦች ስንጨምርበት በውክልና ስልጣን የሚወጡ አስተዳደራዊ ድንጋጌዎች ቁጥር ወደ ላይ በጣም ያሻቅባል፡፡

የተወካዮች ምክር ቤት እስከ ነሀሴ 2008 ዓ.ም. ድረስ ካወጣቸው አዋጆች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በአጭር ጊዜ የሚወጡ ዓለም ዓቀፍና የሁለትዮሽ ስምምነቶችና የብድር ማፅደቂያ አዋጆች ናቸው፡፡ ስለሆነም ም/ቤቱ ሁሉንም ደንቦችና መመሪያዎች ራሱ ለመደንገግ ቢወስን በተግባር ሊወጣው አይችልም፡፡

የእውቀት እጥረት፣

የህዝብ ተመራጮች ለመመረጣቸው ምክንያት እውቀት ወይም ብቃት አንዱ መለኪያ ቢሆንም ዋናው መስፈርት ግን በህዝብ ዘንድ ያላቸው አመኔታና ተቀባይነት ነው፡፡ በጠቅላላ ጉዳዮች ጠቅላላ እውቀት ይኖራቸዋል ብለን ብንገምት እንኳን ከመንግስት አስተዳደር ውስብስብነት አንፃር ቴክኒካል በሆኑ ጉዳዮች ላይ የበለጠ እውቀትና ችሎታ ያለው በአስተዳደር መ/ቤቶች ዘንድ ነው፡፡l ስለሆነም ፓርላማው ትኩረቱን በፖሊሲ ጉዳዮች ላይ በማነጣጠር ዝርዝር የአፈፃፀም ስልት የሚጠይቁ ቴክኒካል 

የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርህ እና ስርዓትአስተዳደራዊ ውሳኔ ምንድነው?


የአስተዳደራዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርህ እና ስርዓት
አስተዳደራዊ ውሳኔ ምንድነው?

‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ በአስተዳር ህግ ውስጥ ከቃል አጠቃቀም፣ ከይዘትና ከወሰን አንጻር ቁርጥ ያለ መደብ ከሌላቸው ፅንሰ ሀሳቦች መካከል ጎልቶ ይወጣል። ውስብስብነቱ ከፅንሰ ሀሳቡ ወካይ ስያሜ ይጀምራል። ‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ በሚል እዚህ ላይ መጠቀሱም በአገራችን የአስተዳደር ህግ ውስጥ መደበኛ መጠሪያው ቢሆን ይበጃል በሚል ብቻ ነው። ጀርመኖች እንኳን የራሳቸውን ወካይ ቃል መፍጠር ተስኗቸው አሁን ላይ በአስተዳደር ህጋቸው ዐቢይ ስፍራ ይዞ የሚገኘውን ‘Administrative act’ (Verwaltungsakt) በሚል የሚጠሩትን ፅንሰ ሀሳብ ለማዳበር ከፈረንሳዮች acte administrative ለመዋስ ተገደዋል።
‘Administrative act’ (Verwaltungsakt) is a core concept of the German administrative law. It covers most of the actions of the administrative authorities through which they affect the legal interests of an individual. The origin of this concept is traced from the French concept of acte administratif from which it was borrowed by the German jurists and developed into a German concept since 1826 onwards.a
በእንግሊዝኛው ፍቺ ከወሰድነው Administrative Decision በይዘቱ Administrative Act ውስጥ የሚጠቃለል ሲሆን ዘርፈ ብዙ መልክ ካላቸው አስተዳደራዊ ተግባራት መካከል አንድ ነጠላ ተግባርን ብቻ ይወክላል። ሆኖም ለአገራችን የአስተዳደር ህግ ‘አስተዳደራዊ ተግባር’ ወይም ‘አስተዳደራዊ ድርጊት’ የሚለውን ቃል ብንጠቀም ገላጭነቱ አይጎላም። ከዚህ በተጨማሪ አስተዳደራዊ ድንጋጌ ማውጣት እንዲሁም ምርመራ፣ ቁጥጥርና ክትትል ሁሉም የአስተዳደር ተግባራት እንደመሆናቸው ዳኝነታዊ ባህርይ ያላቸውን ተግባራት ለይቶ ለማመልከት ውስን ይዘት ያለውን ቃል መጠቀም ያስፈልጋል።

ከዚህ አንጻር በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ‘የአስተዳደር ውሳኔ’ ወይም ‘አስተዳደራዊ ውሳኔ’ የሚለው ቃል ዳኝነታዊ ባህርይ ያላቸውን ተግባራት ለመግለጽ ጥቅም ላይ ውሏል። ሆኖም በመደበኛ ትርጓሜው አደናጋሪ መልዕክት ስለሚፈጥር ይዘቱንና ፍቺውን በቅድሚያ መወሰን ያስፈልጋል።
እ.ኤ.አ. በ1976 ዓ.ም. በወጣው የጀርመን የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ የአስተዳደር ተግባር (Administrative act) የሚከተለው ፍቺ ተሰጥቶታል።
Administrative act is every order, decision or other sovereign measure taken by an authority for the regulation of a particular case in the sphere of public law and directed at immediate external legal consequences.b
ወደ አማርኛ ስንመልሰው፤
የአስተዳደር ተግባር ማለት ቅርብና ውጫዊ የህግ ውጤት የሚያስከትል በህዝብ አስተዳደር ህግ ማዕቀፍ ውስጥ አንድን ልዩ ሁኔታ ለመቆጣጠር ሲባል ስልጣን ያለው አካል የሚሰጠው ትዕዛዝ፣ ውሳኔ ወይም ሌላ ማናቸውም ሌላ ሉዓላዊ እርምጃ ነው።
በትርጓሜው ውስጥ ተጨማሪ ሰፊ ማብራሪያ የሚሹ ንዑስ ሀሳቦች ታጭቀዋል። ሆኖም በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል በጀርመን የአስተዳደር ህግ የአስተዳደር ተግባር ማለት ህግ ለማስፈጸምና የአስተዳደር ስራ ለማከናወን ስልጣን የተሰጣቸው ተቋማት ይህን ህዝባዊ ስልጣናቸውን (public functions) በመገልገል የሚሰጡትን ትዕዛዝ፣ ውሳኔ ወይም ማናቸውም በማድረግ፣ ባለማድረግ የሚገለጽ እርምጃ ሁሉ ያጠቃልላል። ይህም ማለት በውል ወይም ከውል ውጪ ኃላፊነት ህጎች ስር የሚሸፈኑ ግላዊ ድርጊቶች፣ ውሳኔዎች፣ እርምጃዎች ወዘተ…በአስተዳደር ተግባር ስር አይሸፈኑም።
በትርጓሜው ላይ ‘ልዩ ሁኔታ ለመቆጣጠር’ ሲባል ተግባሩ ህጋዊ ውጤት እንደሚያስከትል ወሰኑም በአንድ ልዩ ሁኔታ ላይ ያነጣጠረ እንጂ ጠቅላላ ተፈጻሚነት እንደሌለው ያመለክታል። ስለሆነም የበታች ሠራተኛ ለበላይ ኃላፊ የሚያቀርበው የውሳኔ ሀሳብ፣ ሪፖርት ወይም የምርመራ ውጤት ራሱን ችሎ ህጋዊ ውጤት የማይከተለው በመሆኑ እንደ አስተዳደራዊ ተግባር አይቆጠርም። በአንድ ዘርፍ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ የተወሰደ እርምጃ (ለምሳሌ ስጋ ሻጮች ማሟላት ያለባቸው የጥራት ደረጃ) ከላይ በተቀመጠው ትርጓሜ ውስጥ አይወድቅም። ምክንያቱም ተፈጻሚነቱ ሁሉንም የዘርፍ ነጋዴዎች ስለሚያቅፍ ጠቅላላነት ይታይበታል። በመጨረሻም ህጋዊ ውጤቱ በአስተዳደሩ ውስጣዊ መዋቅር ተወስኖ የሚቀር (ለምሳሌ በአንድ ነጋዴ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የበላይ ኃላፊው ለበታች ሠራተኛ የሚያስተላልፈው ማሳሰቢያ) ከሆነ በአስተዳደራዊ ተግባር ውስጥ አይመደብም።
የአሜሪካው የፌደራል አስተዳር ስነ ስርዓት ህግ ተፈጻሚነቱ አስተዳደራዊ ድንጋጌ የማውጣት (rule making) እና አስተዳደራዊ ዳኝነት (adjudication) የመስጠት ሂደቶች ላይ ነው። በህጉ ላይ በተሰጠው ፍቺ አስተዳደራዊ ዳኝነት ማለት በውጤቱ ‘ትዕዛዝ’ የሚያቋቁም የአስተዳደር ሂደት (agency process for the formulation of an order) ነው። ትዕዛዝ የሚለው ቃል በአስተዳደር ስነ ስርዓት ህጉ ላይ ፍቺ የተሰጠው ሲሆን ይዘቱ እንደሚከተለው ይነበባል።
order means the whole or a part of a final disposition, whether affirmative, negative, injunctive, or declaratory in form, of an agency in a matter other than rule making but including licensing.c
‘ትዕዛዝ’ ከጀርመኑ ‘የአስተዳደር ተግባር’ ጋር ሲነጻጸር መሰረታዊ ልዩነት አይታይበትም። ጉዳዩን የሚቋጭ የመጨረሻ መሆኑ ህጋዊ ውጤት እንደሚከተለው ይጠቁመናል። በይዘቱ አንድ ድርጊት እንዳይፈጸም፣ እንዲፈጸም ወይም የአንድ ሁኔታ (መብት) መኖር/አለመኖር የሚያረጋግጥ መግለጫ ወይም ከአስተዳደራዊ ድንጋጌ ማውጣት ውጪ ያለ ማንኛውም የመጨረሻ እልባት የሚሰጥ ነው።
በመቀጠል የአገራችን የፌደራል ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ (1993) የተጠቀመውን ቃል እና አፈታቱን እናያለን። በረቂቅ አዋጁ የትርጓሜ ክፍል አንቀጽ 2 /2/ እንደተመለከተው አስተዳደራዊ ውሳኔ ማለት፤
ማናቸውም አስተዳደራዊ ባህርይ ያለውን ተግባር ወይም ነገር ከመፈጸም ጋር የተያያዘ ውሳኔ ወይም ውሳኔ አለመስጠትን ጨምሮ ቅጣትን ለመጣል፣ ወይም መፍትሔ ለመስጠት ወይም የመከላከል ዓላማ ወይም ውጤት ያለው በአስተዳደር ተቋማት የሚሰጥ ማናቸውም ውሳኔ፣ ትዕዛዝ ወይም ብይን [ነው።]
የትርጓሜውን ይዘት ይበልጥ ለመረዳት የእንግሊዝኛውን ቅጂ መመልከቱ ጠቃሚ ነው።
Administrative Decision means any decision, order or award of an agency having as its object or effect the imposition of a sanction or the grant or refusal of relief, including a decision relating to doing or refusing to do any other act or thing of an administrative nature, or failure to take a decision
በቀጣይ በ2001 ዓ.ም. በተዘጋጀው ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ አዋጅ አርቃቂዎቹ የተለየ አገላለጽ መጠቀም መርጠዋል። በረቂቁ አንቀጽ 2/2/ ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንደሚከተለው ተተርጉሟል።
አስተዳደራዊ ውሳኔ ማለት ተጨባጭ ሕጋዊ ግንኙነቶችን ለመመስረት፣ ለማሻሻል፣ በምርመራ ለማረጋገጥ ወይም የተሟላ ለማድረግ ለአንድ ጉዳይ የተወሰነ መፍትሔ የመስጠት ዓላማ ያለውና በግለሰብ ወይም በተወሰኑ ሰዎች ላይ ተፈጻሚነት ያለው በተቋሙ የሚሰጥ ሕጋዊ ውሳኔ ሲሆን፣ አስተዳደራዊ ባህርይ ባለው ተግባር ወይም ጉዳይ ላይ ውሳኔ አለመስጠትንም ይጨምራል።
በሁለቱም ረቂቆች ላይ የሚታየው ገላጭነት የጎደለው የቋንቋ አጠቃቀም አብዛኛው ሰው በቀላሉ አይረዳውም። ከዚህም አልፎ የህግ ባለሞያዎች፣ ዳኞች እና አስተዳዳሪዎች በጋራ የሚያግባባ አገላለጽ አልያዘም። ለምሳሌ በተለምዶ ሰርኩላር በሚል ስያሜ ጠቅላላ ተፈጻሚነት ኖሯቸው የሚተላፉ ትዕዛዞች የአስተዳደራዊ ውሳኔና የአስተዳደራዊ ድንጋጌ ከፊል ባህርያት ይጋራሉ። ሆኖም በአንደኛው ስር ለመፈረጅ ሁለቱም ትርጓሜዎች ግልጽ መለያ መስፈርት አላካተቱም። ለአስተዳደራዊ ውሳኔ ትርጓሜ ለማበጀት ጥሩ መነሻ የሚሆነው የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው። ሁለቱን የሚያመሳስላቸው ብዙ ነጥቦች አሉ። አስተዳደራዊ ሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሁለቱም ምንጫቸው ዳኝነታዊ ስልጣን ነው። በዳኝነት ፍሬ ነገሩን የማረጋገጥና በተረጋገጠው ፍሬ ነገር ላይ ህጉን ተፈጻሚ የማድረግ ተግባራት ይከናወናሉ። ዓላማው አከራካሪ የሆነ አንድ ተለይቶ የታወቀ ጉዳይ (particular case) መቋጨት ነው። ጉዳዩን በመቋጨት የሚነገረው ትዕዛዝ፣ ብይን ወይም ውሳኔ በባለጉዳዮች ወይም ሶስተኛ ወገኖች ላይ ህጋዊ ውጤት ያስከትላል። እነዚህ ወሳኝ ባህርያት በጀርመኑ እና የአሜሪካው የአስተዳደር ህጎች ላይ በግልጽ ተለይተዋል።
የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ ቁ. 1183/2012 ለአስተዳደር ውሳኔ ፍቺ የሰጠበት መንገድ የቀድሞዎቹን ረቂቆች ችግር ከማስተካከል ይልቅ የባሰ ተጨማሪ ችግሮች ይዞ መጥቷል። በአንቀጽ 2/3/ ላይ ትርጓሜው እንደሚከተለው ይነበባብል።
የአስተዳደር ውሳኔ ማለት መመሪያ ማውጣትን ሳይጨምር የአስተዳደር ተቋም በዕለት ተዕለት ተግባሩ በሰዎች መብት ወይም ጥቅም ላይ የሚሰጠው የአስተዳደር ውሳኔ ነው።
የትርጓሜ አለአግባብ መለጠጥ ከሞላ ጎደል ሁሉንም ከመመሪያ ማውጣት ያሉ የአስተዳደር ተግባራት በትርጓሜው ስር እንዲወድቁ አድርጓቸዋል። ምንም እንኳን በአቀራረቡ የአሜሪካውን የአስተዳደር ስነ-ስርዓት የተከተለ ቢመስልም በአዋጁ ውሳኔዎች አዎንታዊ መልክ ብቻ እንዲኖራቸው ነው የተደረገው። ለምሳሌ ተቋሙ ‘የማይሰጠውን ውሳኔ’ ማለትም ግዴታን አለመወጣት በትርጓሜው ላይ አይነበብም።
በአንድ የአስተዳደር መ/ቤት የተፈጸመ ተግባር የአስተዳደር ውሳኔ ነው ወይስ አይደለም? የሚለው ጥያቄ በአስተዳደር ህግ ውስጥ መሰረታዊ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ነው። ጥያቄው ተቋሙ ካሉት ጠቅላላ የማስተዳደር (ህግ ማስፈጸም)፣ ከፊል የህግ አውጭነት እና ከፊል የዳኝነት ስልጣናት መካከል የትኛውን እየተገለገለ እንደሆነ የሚለይበት ነው። የጥያቄው ሌላ መልክ ሲታይ ተቋሙ የፈጸመው ተግባር በባህርዩ ዳኝነታዊ ነው ወይስ አይደለም? የሚለውን ጥያቄ ይመልሳል። የውሳኔ ሰጭውን የስልጣን እና የተግባር ዓይነት መለየት በህጉ የአፈጻጸም ወሰን ላይ የራሱ ጉልህ እንደምታዎች አሉት። ጠቅለል ባለ አነጋገር የአስተዳደር መ/ቤቶች ዳኝነታዊ ወይም የህግ አውጭነት ስልጣናቸውን በሚገለገሉበት ጊዜ ካልሆነ በስተቀር ሙሉ በሙሉ በአስተዳደር ስልጣን ውስጥ የሚወድቁት ድርጊቶች በመደበኛ ፍ/ቤቶች ቁጥጥር ሊደረግባቸው አይችልም። በሌላ አነጋገር አስተዳደራዊ ውሳኔ ወይም ድንጋጌ ባልሆነ ጉዳይ ላይ የአጣሪ ዳኝነት ስልጣን አይኖራቸውም። የአስተዳደር መ/ቤቶች ዳኝነታዊ ስልጣናቸውን ተጠቅመው አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሰጡ መሰረታዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎች ተፈጻሚ መሆን ይጀምራሉ።
የፍትሐዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎች
ከስነ-ስርዓት አካሄድ አንጻር ውሳኔ ሰጪ የሆነ የመንግስት አካል በቅን ልቦና ተመርቶ አድሎአዊ ያልሆነ ውሳኔ መስጠትና ከሁሉም በላይ በውሳኔው መብቱ ወይም ጥቅሙ ሊነካ ለሚችል ለማንኛውም ግለሰብ ከውሳኔው በፊት የመሰማት መብቱን ሊጠብቅለት ይገባል።
የአስተዳደር ውሳኔ ፍትሐዊነት በዋነኛነት ሁለት መሰረታዊ መርሆዎችን ያቅፋል። አንደኛው የመሰማት መብት ሲሆን (The right to fair hearing) በላቲን audi alteram partem ተብሎ ሲጠራ አንዳንዴ ‘ተቃራኒውን ወገን ሰማው’ ወይም ‘ማንም ሰው መከላከያው ሳይሰማ እርምጃ ሊወሰድበት አይገባም’ (no one should be condemned unheard) በሚል ይገለጻል።d
ሁለተኛው የኢ-አድሎአዊነት መርህ (The rale against bias) ነው። በላቲን nemo judex in causa sua የሚለውን የህግ አባባል / legal maxim/ ይወክላል። ወደ አማርኛው ስንመልሰው ‘አንድ ሰው በራሱ ጉዳይ ራሱ ዳኛ ሊሆን አይገባም’ የሚል መልዕክት አለው።e በእንግሊዝ እነዚህ ሁለት መርሆዎች ‘የተፈጥሮ ፍትሕ’ የሚባለውን በዳኞች የዳበረ ፅንሰ ሀሳብ የሚወክሉ ሲሆን የህጉ የመሰረት ድንጋይ ተደርገው ይቆጠራሉ።
የመሰማት መብት
በተከሰሰበት ጉዳይ መልስ ሳይሰጥ እንዲሁም ማስረጃውን ሳያሰማ የንግድ ፍቃዱ የተሰረዘበት ነጋዴ፣ የቤት ካርታው የመነከበት ግለሰብ፣ ከዩኒቨርሲቲ የተባረረ ተማሪ… ሁሉም የአስተዳደር በደል ሰለባዎች ናቸው። የአንድን ግለሰብ መብትና ጥቅም ሊጐዳ የሚችል ማንኛውም አስተዳደራዊ እርምጃ ከመወሰዱ በፊት ግለሰቡ የመሰማት ዕድል ሊያገኝ ይገባል። የመሰማት መብት በዘፈቀደ በሚወሰድ አስተዳደራዊ እርምጃ የተነሳ ዜጎች ህይወታቸውና ንብረታቸው ለአደጋ እንዳይጋለጥ ይከላከላል።
መሰማት ሲባል ከክስ እስከ ውሳኔ ድረስ ያሉ ዝርዝር የክርክር ሂደቶችን ያቅፋል። እያንዳንዱ ሂደት በራሱ ካልተሟላ በቂ የመሰማት ዕድል እንዳልተሰጠ ይቆጠራል። በአስተዳደር ዳኝነት ውስጥ የዚህ መብት ዝርዝር ሂደቶችና አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች በዋነኛነት የሚከተሉትን ያካትታል።

ቅድመ-ክስ ማስታወቂያ

የክስ መሰማት ውሳኔ ሰጭው ባለስልጣን ለባለጉዳዩ /ለተከሳሹ/ በሚሰጠው የክስ ማስታወቂያ ይጀመራል። ማስታወቂያ ተከራካሪው እንዲቀርብ የሚሰጥ መጥሪያ ነው። በይዘቱ ባለጉዳዩ የቀረበበትን ክስ በሚገባ ተረድቶ መልሱን አዘጋጅቶ እንዲያቀርብ የሚያስችለው በቂ ማስታወቂያ መሆን አለበት። ተከራካሪው ራሱን ለመከላከል የሚችለው የተከሰሰበትን ጉዳይ በማያሻማ ሁኔታ የተገለጸለት እንደሆነ ነው።f ከዚህ አንጻር የክሱ ዓይነትና ምክንያት ቀጥተኛና ግልጽ በሆነ መንገድ በማስታወቂያው ላይ መስፈር ይኖርበታል። ለምሳሌ እንዲቀርብ የተጠራው ባለጉዳይ የመንግስት ሰራተኛ ወይም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆነ በደፈናው ‘የዲሲፕሊን ክስ ስለቀረበብህ እንድትቀርብ!’ የሚል መጥሪያ ግልጽነት ይጐድለዋል። በተጨማሪም ከአንድ በላይ ክስ በቀረበ ጊዜ እያንዳንዱ ክስ በዝርዝር ሊገለጽ ይገባል። በሌላ መልኩ በክስ ማስታወቂያው ላይ የቀረበው የክስ አይነት ክሱ በሚሰማበት ቀን የተቀየረ እንደሆነ ክሱ እንዳልተገለጸ ወይም በቂ ማስታወቂያ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል። በስርቆት ተከሶ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ፊት እንዲቀርብ የተጠራ ተማሪ ክሱ በሚሰማበት ቀን የመጀመሪያው ክስ ተቀይሮ ‘በፈተና ማጭበርበር’ ተከሶ ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ ተማሪው የተቀጣው በቂ ማስታወቂያ ሳይሰጠው እንደመሆኑ ቅጣቱ መሰረታዊ የሆነውን የመሰማት መብት ይጻረራል።
ክሱ የሚሰማበት ጊዜና ቦታ
‘በቂ’ ሊባል የሚችል የክስ ማስታወቂያ መለኪያ ባለጉዳዩ ራሱን በሚገባ እንዲከላከል በሚያስችል መልኩ በቂ መረጃና ጊዜ የሰጠ እንደሆነ ነው። ክርክሩን ለማካሄድ ስልጣን የተሰጠው አካል ተከራካሪዎች የሚመቻቸውን ጊዜ በመወሰን ክሱ ስለሚሰማበት ቦታ ትክክለኛ መረጃ እንዲኖራቸው በሚያስችል መልኩ መጥሪያውን መላክ ይጠበቅበታል። ጊዜው ሲገለጽ ትክክለኛው ሰዓት ጭምር መገለጽ አለበት። ቦታውም እንዲሁ ትክክለኛ መለያ አድራሻውን በመጥቀስ ለባለጉዳዩ/ለተከሳሹ በግልጽ ማሳወቅ ያስፈልጋል።
ከጊዜ ጋር በተያያዘ መልስ ለማቅረብ የሚሰጠው የዝግጅት ጊዜ እንደክሱ ክብደትና ውስብስብነት ሚዛናዊ የጊዜ መጠን መሆን ይኖርበታል። ዛሬ ክሱ ተሰጥቶት ለነገ መልስ መጠበቅ በተዘዋዋሪ የመሰማት መብትን እንደመንፈግ ይቆጠራል። በመጨረሻም ክሱን የሚሰማው አካል ትክክለኛ ማንነት በማስታወቂያው ላይ መመልከት ይኖርበታል።
የክስ ማስታወቂያ በአካል ስለመስጠት
የጥሪ ማስታወቂያው በይዘቱ በቂ ሊባል የሚችል ቢሆንም ለባለጉዳዩ በአግባቡ እስካልዳረሰው ድረስ የመሰማት መብቱ ተጓድሏል። ባለጉዳዩ በቅርብ የሚገኝ ከሆነ በተቻለ መጠን መጥሪያው ለራሱ በአካል ሊሰጠው ይገባል። ከተገቢ ጥረት በኋላ ለማግኘት የማይቻል ከሆነ ማስታወቂያውን ቅርብ በሆነ ቦታ ላይ መለጠፍና ለተወሰነ ጊዜ በተለጠፈበት ቦታ እንዲቆይ ማድረግ ያስፈልጋል። ጉዳዩ በሚሰማበት ቀን አለመቅረብ ክርክሩ በሌለበት እንዲቀጥል የሚያደረግ በመሆኑ የመጥሪያ በአግባቡ መድረስ የመስማት መብት አካል ተደርጐ መቆጠር ይኖርበታል።ክርክርና ማስረጃ የማቅረብ መብት
ክስ የቀረበበት (ባለጉዳይ) ጉዳዩ በተቀጠረበት ቀን በአካል ወይም በወኪሉ ተገኝቶ ክርክሩን የመከታተል፤ መልስ፣ ክርክርና ማስረጃ የማቅረብ ዕድል ሊያገኝ ይገባል። ይህ መፈጸሙን ማረጋገጥ ክርክሩን የሚሰማው አካል ግዴታ ነው። መልሱ የሚቀርብበት መንገድ እንደየሁኔታው በቃል ወይም በጽሑፍ ሊሆን ይችላል። የሚቀርበው የማስረጃ ዓይነት የቃል (የሰው ምስክር) ወይም የጽሑፍ ማስረጃ ሊሆን ይችላል። ማስረጃው በ3ኛ ወገን እጅ የሚገኝ ከሆነ ባለጉዳዩ እንዲቀርቡለት በጠየቀ ጊዜ ክርክሩን የሚሰማው አካል እንዲቀርቡ ማድረግ አለበት።
መስቀለኛ ጥያቄ የማቅረብ መብት
ባለጉዳዩ የተቃራኒ ወገን ክስና ማስረጃ በአግባብ ሊደርሰውና ሊመለከተው እንደሚችል ከዚህ በፊት ተገልጿል። የዚህ ዓላማ በአንድ በኩል ባለጉዳዩ የራሱን መከራከሪያና ማስረጃ በማቅረብ ክሱን በቀጥታ እንዲከላከል ሲሆን በሌላ በኩል የተቆጠረበትን ማስረጃ ማስተባበል እንዲያስችለው ጭምር ነው።
በፍርድ ቤት በሚካሄድ መደበኛ ክርክር መስቀለኛ ጥያቄ የምስክሮችን ተዓማኒነት ለማሳጣትና በአጠቃላይ እውነትን ለማውጣት ውጤታማ መሳሪያ ነው። ተከሳሹ መስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብ ዕድሉ ተነፍጐት የተሰጠ የምስክርነት ቃል ህጋዊ ብቃቱም አጠያያቂ ነው። ያም ሆኖ ግን የአስተዳደር ክርክር በዓይነቱና በይዘቱ የፍርድ ቤት ክርክር መልክ ከያዘ ውጤታማ አስተዳደርን ወደ ኋላ መጎተቱ አይቀርም። ስለሆነም የመስቀለኛ ጥያቄ መቅረት ባለጉዳዩ ውጤታማ መከላከያ እንዳያቀርብ የሚያግደው ካልሆነ በስተቀር ውሳኔ ሰጭው አካል በመብቱ ላይ ገደብ ሊያደርግ ይችላል።g ይሁን እንጂ ምስክርነቱ በቃለ መሀላ ስር የተሰጠ ከሆነ መስቀለኛ ጥያቄ መከልከል አይገባም። በዚህ ረገድ የ1967ቱ ረቂቅ አዋጅ መስቀለኛ ጥያቄ የማቅርብ መብት ለባለጉዳዩ የሚፈቅድ ግልጽ ድንጋጌ የለውም። በተቃራኒው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ (1993) በአንቀጽ 6 (3)(ሐ) ላይ ይህን መብት በግልፅ አካቷል።
የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁ. 1183/2012 በደፈናው ‘ማስረጃ ስለመመርመር’ ቢናገርም በግልጽ ባለጉዳዩ መስቀለኛ ጥያቄ የመጠቅ መብት ያለው ስለመሆኑ አያመለክትም። ባለጉዳዩ ለተቋሙ የቀረቡ ማስረጃዎችን የመስማትና የመመርመር መብት የአንቀጽ 37/1/ ሐ አነጋገር መብቱ ከጽሑፍ ማስረጃ ጋር ብቻ የተቆራኘ የሚመስል ይዘት አለው። በተጨማሪ ‘ለተቋሙ የቀረቡ’ የሚለው አገላለጽ አደናጋሪ ነው።
በአስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ መስቀለኛ ጥያቄ የማቅረብ መብት ከሞላ ጎደል በሁሉም ህጎችቻን ላይ አልተካተተም። ልዩ ሁኔታ የሚገኘው በፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ 847/2006 ላይ ነው። በአንቀጽ 39/2/ እንደተመለከተው የዲሲፕሊን ክስ የቀረበበት ሰው የከሳሽን ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ መብት ይኖረዋል። የመንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን ክስ በሚሰማበት ወቅት እንዲሁ ግራ ቀኙ መስቀለኛ ጥያቄ ማቅረብ ተፈቅዶላቸዋል። በፌደራል መንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ ስርዓት ደንብ ቁ. 77/1994 አንቀጽ 17/5/ እንደሰፈረው የከሳሽ ምስክሮችን ተከሳሹ፤ የተከሳሽ መከላከያ ምስክሮችን የመንግስት መስሪያ ቤቱ ተወካይ፤ የዲሲፕሊን ኮሚቴው የጠራቸውን ተጨማሪ ምስክሮች ደግሞ ሁለቱም ተከራካሪ ወገኖች መስቀለኛ ጥያቄ መጠየቅ ይችላሉ።
በጠበቃ ተወክሎ የመከራከር መብት
የባለጋራን ክስና ማስረጃ ለማስተባበል የህግ ባለሙያ እገዛ አስፈላጊነቱ አያጠያይቅም። በተለይ ውስብስብ በሆኑ የአስተዳደር ክርክሮች ተካፋይ የሆነ ወገን ካለባለሙያ እገዛ ራሱን በውጤታማ መንገድ ለመከላከል ያለው ዕድል አነስተኛ ነው። ሆኖም በጠበቃ መወከል መሰረታዊ የመሰማት መብት አካል ተደርጐ አይቆጠርም። በመብቱ ላይ የሚጣለው ገደብ የራሱ አሳማኝ ምክንያቶች አሉት።
የአስተዳደራዊ ዳኝነት ክርክር ጥብቅ የሆነ የመደበኛ ፍ/ቤቶች ዓይነት የስነ-ስርዓት አካሄድ ሳይከተል በፍጥነት ጉዳዩን ለመቋጨት ያለመ ነው። የጠበቃ መኖር ክርክሩ የባሰ እንዲወሳሰብና ከተገቢው ጊዜ በላይ እንዲንዛዛ በማድረግ የክርክሩን ኢ-መደበኛ ባህርይ ያጠፋዋል። በአጠቃላይ አነጋገር በጠበቃ ውክልና ከሚታገዝ ይልቅ ባለጉዳዩ ራሱ የሚከራከርበት አስተዳደራዊ ክርክር በአጭር ጊዜ እልባት ያገኛል። ያም ሆኖ ግን ክርክር የሚካሄድበት ጉዳይ በባሉጉዳዩ መብትና ጥቅም ላይ ሊኖረው ከሚችለው አሉታዊ ውጤት አንጻር ማለትም የክርክሩን ክብደትና ውስብስነት መሰረት አድርጐ እንደየሁኔታው በጠበቃ የመወከል ጥያቄን ማስተናገድ ያስፈልጋል።
ምክንያታዊ ውሳኔ
ዜጐች በሰውነታቸውና በንብረታቸው ላይ እርምጃ ሲወሰድ ከመንግስት ምክንያት ይሻሉ። አንዳችም ምክንያት የሌለው ውሳኔ የአስተዳደር በደል መገለጫ ነው። ኢ-ፍትሐዊነት በሁለት መልኩ ይገለጻል፤ የመጀመሪያው ምክንያት ሳይጠቀስ በደፈናው ውሳኔ ሲሰጥ፣ ሁለተኛው ደግሞ ውሳኔው በራሱ ፍርደገምድል፣ ሚዛናዊነት የጐደለውና በአሳማኝ ምክንያት ያልተደገፈ ሲሆን።
ለውሳኔ ምክንያት መስጠት በአስተዳደር ህግ ውስጥ ጉልህ ስፍራ እያያዘና እያደገ የመጣ መሰረተ ሀሳብ ነው። ያም ሆኖ ከአሜሪካው የአስተዳደር ስነስርዓት በስተቀር በእንግሊዝ ሆነ በህንድ ምክንያት እንዲሰጥ የሚያስገድድ በሁሉም የአስተዳደር አካላት ተፈጻሚ የሆነ ጠቅላላ ደንብ የለም። ሆኖም አልፎ አልፎ ማቋቋሚያው አዋጅ ለአስተዳደራዊ ውሳኔ ምክንያት እንዲሰጥ ቅድመ ሁኔታ ያስቀምጣል።
አስተዳደራዊ ውሳኔ ሊኖረው የሚገባውን ይዘትና ቅርጽ በተመለከተ በ1967 ረቂቅ አዋጅ አንቀጽ 13 እንዲሁም በፌደራሉ ረቂቅ አዋጅ (1993 ዓ.ም.) አንቀጽ 32 ላይ ቅድመ ሁኔታዎቹ ተዘርዝረዋል። በዚሁ መሰረት አስተዳደራዊ ውሳኔ በጽሑፍ መሰጠት ያለበት ሲሆን ውሳኔውም የክርክሩን ፍሬ ነገር፣ የማስረጃዎች ፍሬ ጉዳይና ምንጭ፣ የነገሩን ጭብጥ አወሳሰን እንዲሁም በውሳኔው መሰረት ተመስርቶ ሊወሰድ ስለሚገባው እርምጃ የሚያመለክት መሆን ይኖርበታል። ምንም እንኳን በረቂቆቹ ላይ ‘ምክንያት’ የሚለው ቃል በግልጽ ባይጠቀስም የውሳኔ ምክንያትን የሚያያቋቁሙ ሁኔታዎች የተካተቱ እንደመሆኑ ምክንያት መስጠት እንደአስገዳጅ ሁኔታ ተቀምጧል ማለት እንችላለን።
ከረቂቆቹ ጋር ሲነጻጸር የአስተዳደር ስነ- ስርዓት አዋጁ የአስተዳደር ውሳኔ መያዝ ያለበትን ፍሬነግሮች የዘረዘረ ሲሆን ለውሳኔ በቂ ምክንያት መስጠትም እንደ አንድ መሰረታዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርህ አካቶታል። በመሆኑም የአስተዳደር ውሳኔ ሲሰጥ አብሮት በቂ ምክንያት ሊሰጥ ይገባል።h የአስተዳደር ውሳኔ ይዘት በተመለከተ በጽሑፍ ሆነ የሚከተሉትን መያዝ ይኖርበታል።
1-የውሳኔ ቀንና ቁጥር ፤
2-የተቋሙን ስም ፤
3-በክርክሩ ተካፋይ የሆኑ ወገኖችን አድራሻ፤
4-አከራካሪ ፍሬ ነገር፤
5-የማስረጃዎች ትንተና፤
6-የፍሬ ነገር እና የሕግ ትንታኔ፤
7-ውሳኔ
በአንዳንድ አዋጆች ላይ ውሳኔን በምክንያት ማስደገፍ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ ነው። ለአብነት የሚከተሉት ይጠቀሳሉ።
በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁ. 980/2008 አንቀጽ 6/2/ የንግድ ምዝገባ ማመልከቻ ውድቅ ከተደረገ መዝጋቢው አካል ምክንያቱን ገልጾ ለአመልካቹ ወዲያውኑ ማሳወቅ አለበት።
ከቀረጥ ዋጋ አወሳሰን ጋር በተያያዘ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ተጨማሪ መግለጫ ወይም ሰነድ ከዲክላራሲዮን አቅራቢው ከተቀበለ በኋላ ስለግብይት ዋጋው ትክክለኛነት ያለውን ጥርጣሬ ማስወገድ ካልቻለ ወይም ዲክላራሲዮን አቅራቢው ምላሽ ካልሰጠ በጉምሩክ አዋጅ ቁ. 859/2006 አንቀጽ 90 መሰረት ዋጋውን መወሰን እንዳልተቻለ ይቆጠራል። በዚሁ መሰረት የቀረበው የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ ተቀባይነት ያላገኘበት ምክንያት በጽሑፍ ለአስመጭው ወይም ለወኪሉ ይገለጽለታል።i
በነዳጅ አቅርቦት ስራ ለመሰማራት የተጠየቀ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ተቀባይነት ካላገኘ ምክንያቱ ለአመልካቹ ይገለጽለታል።j
የስደተኝነት ዕውቅና እንዲሰጥ የሚቀርብ አቤቱታ ተቀባይነት ቢያገኝም ባያገኝም ውሳኔው ለአቅራቢው በጽሑፍ መገለጽ አለበት።k
የኢ-አድሎአዊነት መርህ
ከአድልኦ የፀዳ ፍርድ (The rule against bias) የሚለው መርህ በኮመን ሎው አገራት በስፋት የዳበረ መሰረተ ሀሳብ ሲሆን በአጭሩ ሲገለጽ አንድ ሰው በራሱ ጉዳይ ራሱ ከሳሽ ራሱ ዳኛ መሆን የለበትም እንደማለት ነው። ኢ-አድሎአዊነት አብዛኛውን ጊዜ ራሱን የቻለ የተፈጥሮ ፍትህ መርህ ተደርጐ ቢጠቀስም በተግባር ሲታይ ግን በመሰማት መብት ውስጥ የሚጠቃለል የፍትሐዊ ስነ-ስርዓት አንድ አካል ነው። አንድ ሰው በአስተዳደር ጉባዔ (Administrative Tribunal) ፊት ቀርቦ የመሰማት እድል ሊሰጠው ይገባል ሲባል በውስጠ ታዋቂነት ፍ/ቤቱ ከአድልኦ የፀዳ እንደሆነ ግምት በመውሰድ ነው።
ፍርደ ገምድል ያልሆነ፤ ያልተዛባ ውሳኔ መኖር ህዝቡ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ያለውን አመኔታ የሚያንፀባርቅ እንደመሆኑ ተፈፃሚነቱም /በተለይ በኮመን ሎው አገራት/ እጅግ ጥብቅ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ የታወቁት የእንግሊዝ ዳኛ ሎርድ ሄዋርት እንዲህ ብለው ነበር።
ፍትህ መሰራቱ ብቻ በቂ አይደለም። ፍትህ ሲሰራ ጭምር በማያጠራጥርና ግልጽ በሆነ አኳኋን መታየት መቻል አለበት።
የዳኛው ልጅ ‘ቀማኛ’ ተብሎ በአባቱ ፊት ችሎት ሲቀርብ በእርግጥም በህጉ መሰረት ጥፋተኛ ላይሆን ይችላል። ጥፋተኛ ካልሆነ መለቀቁ ፍትህ ነው። ግን ለማንም አይመስልም። ፍትህ ሲሰራ አይታይምና። ዋናው ቁም ነገር ዝምድና፤ የገንዘብ ጥቅም ወይም ሌላ ምክንያት በዳኛው ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተጽእኖ አለማድረጉ አይደለም። እነዚህ ሁኔታዎች እስካሉ ድረስ ዳኛው ምንም ያህል ንፁህና ጻድቅ ሰው ቢሆን እንኳን በችሎት ላይ ተቀምጦ ሲያስችል አመኔታ ያጣል። የኢ-አድሎአዊነት መርህ ዋና አላማ ውሳኔ ሰጭው አካል የተዛባ ፍርድ እንዳይሰጥ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም ራሱም ሳያውቀው እንኳን በንፁህ ህሊናው ላይ ተፅእኖ ሊያደርሱ ከሚችሉ ሁኔታዎች ነጻ ሆኖ ዳኝነት እንዲሰጥ ለማስቻል ነው።
ይህ የኢ-አድሎአዊነት መርህ በተለይ በመደበኛ ፍ/ቤት፣ በአስተዳደር ጉባኤ እና ዳኝነታዊ ውሳኔ በሚሰጡ የአስተዳደር መ/ቤቶች ጥብቅ ተፈጻሚነት አለው። ውሳኔ ሰጪው አካል በያዘው ጉዳይ በህሊናው ላይ ተፅእኖ ሊያመጣ የሚችል ሁኔታ መኖሩን በተረዳ ጊዜ ራሱን ከውሳኔ ሰጪነት ማግለል አለበት። ይህ ባልሆነበት ጊዜ በቂ ጥርጣሬ ያደረበት ወገን አቤቱታ አቅርቦ ዳኛው እንዲቀየርለት ማመልከት ይችላል። ሁኔታው መኖሩ የታወቀው ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ ከሆነ የዛ ውሳኔ እጣ ፈንታ ዋጋ አልባ መሆን ነው።
አድሎአዊ ውሳኔ ተሰጥቷል የሚባለው የውሳኔ ሰጭው ህሊና የተዛባ እንደሆነ ነው፡ ለመሆኑ የሕሊና መዛባት ምን ማለት ነው?
በጥሬ ትርጉሙ ሲታይ ማንኛውም ነገር በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ውሳኔ ሰጭው በነጻ ህሊናው ተመርቶ ሊሰጥ ይችል ከነበረው ውሳኔ በተቃራኒ የተለየ ውሳኔ ላይ ያደረሰ ከሆነ ህሊናው ተዛብቷል ብለን መናገር እንችላለን። ህሊና ከተዛባ የክርክሩ ውጤት (ማለትም ውሳኔው) ጉዳዩ ከመመርመሩ በፊት ድምዳሜ ተደርሶበታል። ዳኛው ከከሳሽ ወይም ተከሳሽ ጉቦ ከተቀበለ ፍርዱ ለማን እንደሚሰጥ አስቀድሞ ታውቋል። በዚህ መልኩ የሚሰጥ ፍርድ በተዛባ ህሊና የተሰጠ አድሎአዊ ፍርድ ነው።
የተዛባ ህሊና ከምንጩ አንፃር በተለያየ መንገድ ይገለጻል። በዋነኛነት ከሚጠቀሱት መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።
ዝምድና
ዝምድና ሲባል የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም በግል ግንኙነት፣ በሙያ ትስስር እንዲሁም በጓደኝነትና በትውውቅ ላይ የተመሰረተና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተፅእኖ ሊያመጣ የሚችል ዝምድና ወይም ጥላቻ ሁሉ ያጠቃልላል።
ውሳኔ ሲጪው ከአንደኛው ተከራካሪ ወገን ጋር ዝምድና ወይም ጥላቻ ያለው ከሆነ አሉታዊ ወይም አዎንታዊ በሆነ መልኩ አድሎአዊ ወይም የተዛባ ፍርድ የመስጠት እድሉ ከፍተኛ ነው። የፌደራሉ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ (1993 ዓ.ም.) በአንቀጽ 29/2/ ላይ የዝምድናን ጽንሰ ሀሳብ በጣም አጥብቦታል። ድንጋጌው የግል ጥላቻ እንዳለበት የሚገምት ውሳኔ ሰጪ ራሱን በክርክሩ ሂደት ከመሳተፍ እንዲያገል ግዴታ ይጥልበታል። ከግል ጥላቻ ባልተናነሰ ትውውቅ፣ ቅርበት፣ ጓደኝነት በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድራሉ። ይህ መሰረታዊ ቁም ነገር በረቂቅ አዋጁ ላይ ተረስቷል።
ከዚህ በተቃራኒ የ1967ቱ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ከዝምድና የሚመነጭ የተዛባ አመለካከት ከቀጥተኛ የግል ጥቅም እንዲሁም ከስጋ ወይም ከጋብቻ የሚመነጭ ዝምድና በሙሉ እንደሚያጠቃልል በግልፅ ያመለክታል። የአስተዳደር ስነ-ስር ዓት አዋጅ ቁ. 1183/2012 ከ 1967 ቱ ረቂቅ ጋር ተቀራራቢ ይዘት አለው። ውሳኔው ሰጭው ከጉዳዩ ላይ ቀጥተኛ ወይም ቀጥተኛ ያልሆነ ጥቅም ካለው ወይም ባለጉዳዩ የስጋ ወይም የጋብቻ ዝምድና ወይም በቅርብ የሚታወቅ ወዳጁ ሲሆን ወይም የእነዚህ ሰዎች የጥቅም ግጭት ያለበት ጉዳይ ከሆነ ራሱን ማግለል እንዳለበት አንቀጽ 38/1/ በፊደል ሀ እና ለ በውሳኔ ሰጭው ላይ ግዴታ ይጥላል።
በአስተዳደር ህግ ውስጥ ‘ዝምድና’ የሚለው ቃል ከስጋ ወይም ጋብቻ ዝምድና የዘለለ በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ የሚችል ማንኛውንም አሉታዊና አዎንታዊ ግንኙነት ያቅፋል። ነገሩን ለማብራራት ያህል በአይ.ፒ. ማሴይ ‘የአስተዳደር ህግ’ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሰ አንድ ጉዳይ እንደ መላምታዊ ምሳሌ አገራዊ መልክ በማስያዝ ማየቱ ጠቃሚ ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ አንድ ማዕድን የመፈለግና የማውጣት ስራ ላይ የተሰማራ ድርጅት ከተሰጠው ፍቃድ ውጪ ህገ ወጥ ድርጊት ፈጽሟል ተብሎ በመከሰሱ ፈቃዱ የማይሰረዝበት አጥጋቢ ምክንያት ካለ መከላከያውን ይዞ እንዲቀርብ በማዕድን፣ ነዳጅና ተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር መጥሪያ ተላከለት። ሆኖም የዚህ ድርጅት ባለቤት በአንድ ወቅት ሚኒስትሩ ለምርጫ በተወዳደሩበት ወቅት የተቃዋሚ ፖርቲ አባል ሆኖ ሚኒስትሩ እንዳይመረጡ በመጣር ከፍተኛ ተቃውሞና ቅስቀሳ አድርጓል። በሌላ ጊዜም የሚኒስትሩን ስም በማጥፋት ወንጀል ተከሶ በመጨረሻ ነጻ ወጥቷል። እንግዲህ ሚኒስትሩ የንግድ ፍቃዱን ቢሰርዝ ውሳኔው በግል ግንኙነት /ጥላቻ/ ላይ የተመሰረተና የተዛባ ነው ማለት ይቻላል?
ከህንድና ከሌሎች አገሮች ልምድ ለመረዳት እንደሚቻለው የግል ግንኙነትን ጨምሮ በሌሎች ሁኔታዎች ውሳኔ የተዛባ ነው ለማለት ተገቢ የሆነ ጥርጣሬ መኖር አለበት። የመጀሪያው መለኪያ ውጫዊ መልክ ወይም ገጽታ መሰረት ያደርጋል። ይህም ማለት የግል ግንኙነቱ ደረጃ በአንድ አስተዋይ ሰው እይታ አድሎአዊነትነት የሚፈጥር አይነት ከመሰለና ይህም ተገቢ የሆነ ጥርጣሬን የሚያሳድር ከሆነ ውሳኔው የተዛባ ስለመሆኑ መደምደም ይቻላል። ሁለተኛውና ‘ቅርብ የሆነ አጋጣሚ’ የሚባለው መለኪያ ደግሞ ትኩረት የሚያደርገው አድልኦ የሚፈጠር መሆኑ አይደለም። ከዚያ ይልቅ እያንዳንዱን ጉዳይ በነጠላ በማየት ግንኙነቱ ውሳኔው ላይ ተጽእኖ ለማሳደር ያለውን አጋጣሚ (ደረጃ) ይመረምራል።
ስለሆነም በውሳኔ ሰጪውና በባለጉዳዩ መካከል የስጋ ወይም ጋብቻ ዝምድና ቢኖርም እንኳን ሁለቱ ካላቸው ቅርርብ ወይም ርቀት እንዲሁም ትክክለኛ የግንኙነት ደረጃ አንጻር የተጽእኖው ደረጃ ኢሚንት የሚባል አይነት ከሆነ ውሳኔው አልተዛባም። በተቃራኒው የዝምድናው ደረጃ ሩቅ ቢሆንም እንኳን ውሳኔ ሰጪውና ባለጉዳዩ በማህበራዊ ግንኙነታቸው የጠበቀና ቅርብ ትስስር ያላቸው (ለምሳሌ ለብዙ ጊዜያት አብረው በአንድ ቦታ የኖሩና ሌላም መሰል ትስስር ያላቸው) ከሆኑ አድሎአዊ ውሳኔ የመስጠት አጋጣሚው በጣም የሰፋ መሆኑን ስለሚያሳይ የውሳኔው የመዛባት አጋጣሚ ከፍተኛ ነው።
ተገቢ የሆነ ጥርጣሬ ወይም ቅርብ የሆነ አጋጣሚ እንደ የተዛባ ውሳኔ /አድልዎ/ መለኪያነት እርስ በርስ በጣም የተለያዩ ቢመስሉም በተግባር ሲታዩ ዞሮ ዞሮ መድረሻቸው አንድ ነው። መሰረታዊው ጥያቄ ውሳኔ ሰጪው ህሊናው ተዛብቷል? የሚል አይደለም። የአንድን ሰው የህሊና ሁኔታ ማረጋገጥ ይከብዳል። መታየት ያለበት ውሳኔው የተዛባ ሊሆን የሚችልበት እድል ሰፊ ወይም ቅርብ ነው ብሎ ለማመን የሚቻልበት ተገቢ ጥርጣሬ ማሳደሩ ነው።
ተገቢ ጥርጣሬ ማንኛውም ተራ ስሜትና ሀሜት የሚጨምር ሳይሆን በአስተዋይ ሰው እይታ በቂ መረጃ ላይ ተመስርቶ ያሉትን አጋጣሚዎችና ሁኔታዎች በመመርመር ተገቢ ወይም ሚዛናዊ ሊባል የሚችል የጥርጣሬ ሁኔታ መፈጠሩና ይህም በ3ኛ ወገን ላይ የሚያሳድረው ምክንያታዊ ስሜት ነው።
የገንዘብ ጥቅም
ቀጥተኛ የሆነ የገንዘብ ጥቅም እንደ አድሎዎ መገለጫነቱ ሲታይ ሊገኝ የሚችለው የገንዘብ መጠን አነስተኛ ቢሆንም እንኳን ውሳኔውን ለመሻር አሳማኝ ምክንያት ነው። ሰዎች ከገንዘብ ጥቅማቸው በተጻራሪ ውሳኔ እንደማይሰጡ ከሰው ልጅ ባህርይና ከተፈጥሮ እውቀት መገንዘብ አያዳግትም። ጉቦ መቀበል ግልጽና ዓይን ያወጣ የገንዘብ ጥቅም መገለጫ እንደመሆኑ ከተከራካሪ ወገኖች ከአንዱ የገንዘብ ስጦታ የተቀበለ የአስተዳደር መ/ቤት ሹመኛ ወይም ሰራተኛ እንዲሁም የአስተዳደር ጉባዔ ዳኛ የሚሰጠው ውሳኔ ወዲያውኑ ሊሻር ይገባዋል። ሆኖም የገንዘብ ጥቅም የሚገለጽባቸው መንገዶች የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ ያህል አንድ የአስተዳደር ጉባዔ ዳኛ ከሳሽ ወይም ተከሳሽ ሆኖ በቀረበው ድርጅት ውስጥ የአክሲዮን ባለቤት ከሆነ ተገቢ በሆነ ጥርጣሬ ብሎም ቅርብ በሆነ አጋጣሚ መለኪያ የሚሰጠው ውሳኔ የተዛባ ነው ብሎ መደምደም ተገቢ ይሆናል።
በፌደራሉ ረቂቅ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ (1993 ዓ.ም.) መሰረት የአስተዳደር ውሳኔ ለመስጠት ስልጣን ያለው ሰው በጉዳዩ የመጨረሻ ውጤት ላይ የገንዘብ ጥቅም እንዳለው ከተረዳ ወዲያውኑ ራሱን ከውሳኔ ሰጪነት እንዲያገል ይጠበቅበታል። ይህ ካልተፈፀመ በክርክሩ ተካፋይ የሆነው ወገን አቤቱታ አቅርቦ ከችሎት እንዲነሳለት መጠየቅ ይችላል።l
ተደራራቢ (ቅይጥ) ሚና
በአንድ ጉዳይ ላይ በአጣሪነት፣ በመርማሪነት፣ በከሳሽነትና መሰል ኃላፊነቶች የተሳተፈ የመንግስት ባለስልጣን እንደገና ተመልሶ በተመሳሳይ ጉዳይ በውሳኔ ሰጭነት ስልጣኑ ከተሳተፈ የውሳኔውን አድሎአዊነት ያንፀባርቃል። አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመስጠት ስልጣን ያለው ተሿሚ ወይም ሠራተኛ ከውሳኔ በፊት አጣሪ፣ መርማሪ፣ ወይም በሌላ ሙያ ተሳታፊ በሆነበት ጉዳይ ተመልሶ በውሳኔ ሰጪነት ስልጣን የሚሳተፍ ከሆነ የተዛባ አድሎአዊ ውሳኔ የመስጠት እድሉ በጣም ከፍተኛ ነው። አንድ ሰው ራሱን የሚቃረን ውሳኔ የማይሰጥ መሆኑ ከሰው ልጅ ባህርይ የምንረዳው እውቀት ነው።
በአንድ ጉዳይ በተደራራቢ ሚና መሳተፍ በአስተዳደር ሂደቱ በውስጡ ያለ መገለጫ ቢሆንም ውጤታማ በሆነ መንገድ ቁጥጥር ካልተደረገበት የፍትሀዊነትንና የርትዐዊነትን ጽንሰ ሀሳብ ድራሹን ያጠፋዋል። የአንድን ድርጅት የንግድ እንቅስቃሴ ህጋዊነት ለማጣራት በመርማሪነት ሚና የተሳተፈ የመንግስት ሰራተኛ የድርጅቱን የንግድ ፈቃድ ለመሰረዝ በተካሄደው የአስተዳደር ክርክር ላይ በውሳኔ ሰጪነት ሚና በድጋሚ የሚሳተፍ ከሆነ ተደራራቢ ሚናው አድሎአዊ ለሆነ ውሳኔ መንስዔ መሆኑ አይቀርም። በተመሳሳይ መንገድ አንድ ሰራተኛ በተከሰሰበት የዲሲፕሊን ጉዳይ ላይ የመ/ቤቱ ኃላፊ የዲሲፕሊን ኮሚቴው አባል ሆኖ ከተሳተፈ በኃላፊነት ስልጣኑ የሚወስደው የዲሲፕሊን እርምጃ ከአድልኦ ያልፀዳ ነው።
ተደራራቢ ሚናን በተመለከተ ሁለቱም ረቂቅ አዋጆች ቁንጽል ድንጋጌ ቢኖራቸውም ከፍሬያማነታቸው ይልቅ ድክመታቸው ጐልቶ ይታያል። የፌደራሉ ረቂቅ አንቀጽ 29 /6/ እንዲህ ይነበባል።
በማናቸውም የአስተዳደር ተቋም ውስጥ በወንጀል ምርመራ ወይም ክስ በመመስረት ተግባር ተሰማርቶ የሚገኝ የመንግስት አስተዳደር ሰራተኛ በማናቸውም ሁኔታ በያዘው ጉዳይ ወይም ከዚሁ ጋር በፍሬ ነገር በተዛመደ ጉዳይ ላይ በሚሰጥ አስተዳደራዊ ውሳኔ በምስክርነት፣ የህግ ምክር በመስጠት መሳተፍ ወይም መምከር አይችልም።
የዚህ አንቀጽ ዋና ግድፈት የሚነጻጸሩት ተደራራቢ ሚናዎች አጣሪነት፣ መርማሪነት፣ ከሳሽነት ወዘተ… ከውሳኔ ሰጪነት ስልጣን ጋር ሳይሆን ከምስክርነት እና የህግ ምክር ሰጪነት ሚና ጋር መሆኑ ነው። የተደራራቢ ሚና ጽንሰ ሀሳብ ዋና አላማው ጉዳዩን ያጣራው ወይም የመረመረው ባለስልጣን ተመልሶ ውሳኔ ሰጪ ከሆነ ውሳኔው አድሎአዊ ሊሆን ስለሚችል ይህንኑ በመከላከል በአስተዳደር ክርክር ውስጥ ፍትህ ወይም ርትዕ ማስፈን ነው። ረቂቁ ይህን አላማ ለማሳካት ተጨባጭ ችግሩ ላይ ከማነጣጠር ይልቅ ለአስተዳደር ፍትህ አግባብነቱ ብዙም ፋይዳ በሌለው የወንጀል መርማሪነትና ከሳሽነት ሚናን ምስክር ከመሆንና የህግ እርዳታ ከመስጠት ሚና ጋር እንዳይደራረብ ገደብ ያስቀምጣል።
በ1967ቱ ረቂቅ አዋጅ መሰረት የመርማሪነት (ይህም በወንጀል መርማሪነት ሳይሆን በአስተዳደራዊ ሂደት ላይ ያሉ ሚናዎችን ያጠቃልላል።) እና የዐቃቤ ህግነት ሚና የነበረው ባለስልጣን ወይም ሰራተኛ በአስተዳደር ክርክሩ ላይ በዋናነት በውሳኔ ሰጪነት እንዳይሳተፍ ይከላከላል። ይሁን እንጂ በምስክርነት ወይም በአማካሪነት ከመሳተፍ እንደማይከለከል በልዩ ሁኔታነት በግልጽ ያስቀምጣል።
በንፅፅር ሲታይ አዋጅ ቁ. 1183/2012 የተሻለ ይዘት ያለው ቢሆንም ሁሉንም መሰረታዊ የተዛባ አመለካከት ምንጮች አልዳሰሰም። በአንቀጽ 38/1/ በፊደል ሐ እና መ ላይ የተጠቀሱት ሁለት ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው።
በመታየት ላይ ላለው ጉዳይ እንደ ባለሙያ፣ ወኪል ወይም የግል ጠበቃ ሆኖ ተሳትፎ ከሆነ፤
በመታየት ላይ ያለው ጉዳይ ሰራተኛው በስር ውሳኔ አይቶት በይግባኝ የቀረበለት ከሆነ
ከሁለቱ ውጭ በመመርማሪነት የተሳተፈ ሰው በውሳኔ ሰጭነት እንዳይሳተፍ በግልጽ የሚከለክል ድንጋጌ የለም።
 
ልዩ ሁኔታዎችና የተፈጻሚነት ወሰን
በፍርድ ቤቶች የዳበሩ መሰረታዊ መርሆዎች እንዲሁም አስገዳጅነት ያላቸው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ህጎች በሁሉም አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ወጥ ተፈጻሚነት የላቸውም። የእያንዳንዱ አስተዳደራዊ ውሳኔ ከግለሰቦች መብትና አንጻር ሲመዘን ከቀላል እስከ ከባድ የሚያስከትለው ውጤት እና ተፅዕኖ ይለያያል። የውሳኔውም ዓይነት እንዲሁ ወጥ መልክ የለውም። የመንግስት ሠራተኛን ከስራ ማባረር፣ አስተዳደራዊ ቅጣት መጣል፣ ለህዝብ ጥቅም ሲባል ከይዞታ ማፈናቀል፣ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት (ካርታ) መሰረዝ፣ የብቃት ማረጋገጫ፣ የሙያ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ፣ የስራ ፈቃድ መሰረዝና ማገድ፣ የሊዝ ውል ማቋረጥ፣ በአንድ የስራ ዘርፍ የተሰጠ ዕውቅና (ለምሳሌ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) መሰረዝ እና ሌሎች መሰል ውሳኔዎች ህገ መንግስታዊ ጥበቃ ያገኙ መብቶችን የመጣስ ከፍተኛ አዝማሚያ ስላላቸው ፍትሐዊ ስርዓት ተከትለው መወሰድ ይኖርባቸዋል። አስተዳራዊ ቅሬታ እና ይግባኝ የሚስተናገድበት መንገድ እንዲሁ ፍትሐዊ ስነ ስርዓት እና አንጻራዊ ገለልተኘነት ካላንፀባረቀ የይስሙላ ሆኖ ነው የሚቀረው።
ስለሆነም በእነዚህ በተጠቀሱት ምሳሌዎች ስር የሚወድቁና ሌሎች ተመሳሳይ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ለመሰማት መብት እና ኢ-አድሎአዊነት መርሆዎች ተገዢ ሊሆኑ ይገባል። እንደዛም ሆኖ ግትር ተፈጻሚነት ሊኖራቸው አይገባም። አስተዳደራዊ አመቺነትን ያላማከለ የሰነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታ ውጤታማነትን ያኮላሻል። ለምሳሌ በከፊል አስተዳደራዊ ክርክሮች በጠበቃ የመወከል መብት በአስተዳደሩ ላይ ከሚያመጣው ጫና አንጻር እንዲቀር ቢደረግ የመሰማት መብትን አያጣብብም።
ከላይ በምሳሌነት የተጠቀሱት አስተዳደራዊ ውሳኔዎች አንድ የአስተዳደር መ/ቤት በየዕለቱ ይቅርና በየወሩ የሚያከናውናቸው ተግባራት አይደሉም። በቁጥር በእጅጉ በልጠው የሚገኙት ውሳኔዎች ግዙፋዊ የመብት መጓደል አያስከትሉም። ሆኖም በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የግለሰቦችን መብትና ጥቅም የሚነኩ ከሆነ በዘፈቀደ መወሰድ የለባቸውም። ይብዛም ይነስም በተነካው መብት ልክ ፍትሐዊነት በገሀድ እንዲታይ ይጠበቃል።
እስካሁን የቀረበው ዳሰሳ አንድ መሰረታዊ ጥልቅ መልዕክት ያስጨብጠናል። ይኸውም፤ ሁሉንም የአስተዳደራር ውሳኔዎች ለአንድ ወጥ ስነ ስርዓት ተገዢ ማድረግ ሊሞከር ቀርቶ አይታሰብም። ፍርድ ቤት ብቻ ነው አንድ ወጥ ስነ-ስርዓት የሚከተለው። ያላደገ ሆነ የዳበረ የአስተዳደር ህግ ያላቸው አገራት በማንኛውም አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አንድ ወጥ ስነ ስርዓት የላቸውም። አንድ አስተዳደራዊ ውሳኔ ከቀላል እስከ ጥብቅ የትኛውን ስነ ስርዓት መከተል እንዳለበት ለመወሰን ለህግ አውጪው አስቸጋሪ ስራ ነው። ውስብስብ የሆነው የአስተዳደር ስራ ባህርይ በዚህ ረገድ የሚደረገውን ጥረት ፈታኝ ያደርገዋል። ያም ሆኖ ግን ፈተናው በወጉ ካልተመለሰ ፍትሐዊነትና ውጤታማ አስተዳደር ሚዛናቸውን ይስታሉ።
እንደ ፒተር ዎል አገላለጽ በአስተደደራዊ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ተፈጻሚ የሚሆኑት አነስተኛ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች እንደ ጉዳዩ ዓይነትና ውስብስብነት፣ የማስረጃዎችና የሚረጋገጡት ፍሬ ነገሮች ዓይነት፣ የውሳኔ ሰጭው ማንነትና የሚያከናውነው የአስተዳደር ተግባር ባህርይ እንዲሁም ውሳኔው በግለሰቦች ላይ ሊያስከትል ከሚችለው ጉዳት አንጻር ደረጃቸው ይለያያል።
[W]hat constitutes a minimum compliance with due process in the way of administrative hearing…will vary to a considerable extent with the nature of the substantive right, the character and complexity of the issues, the kinds of evidence and factual material, the particular body or official, and the administrative functions involved in the hearing.m
የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ፍትሐዊነት እንዲሰፍን ከዚያም አልፎ በህዝብ አስተዳደር ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነት በአጠቃላይ መልካም አስተዳደር እንዲያብብና እንዲጎለብት የሚያበረክተው አዎንታዊ አስተዋጽኦ በሀሳብ ሆነ በተግባር ደረጃ ተፈትኖ የተረጋገጠ ቢሆንም አፈጻጸሙ በጥንቃቄ ወሰን ካልተበጀለት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። የአስተዳደር ስነ ስርዓት ፍርድ ቤቶች እንደሚከተሉት የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት ጥብቅ እና መደበኛ በሆነ ቁጥር አስተዳደራዊው ሂደት እጅና እግሩ ይታሰራል። በዚህ የተነሳ ዜጎች ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ያጣሉ። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ደግሞ የዜጎችን ብሶት ‘ከፍትሕ ጥማት’ ወደ ‘አገልግሎት ረሀብ’ ቢቀይረው እንጂ ፍሬ አያስገኝም።
እ.ኤ.አ በ1946 በወጣው የአሜሪካው የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ (Administrative Procedure Act) የአስተዳደር ዳኝነት መደበኛ እና ኢ-መደበኛ በሚል ለሁለት ተከፍሏል። መደበኛው የአስተዳደር ዳኝነት ከክስ መስማት እስከ ውሳኔው ይዘት ድረስ በዝርዝር አስገዳጅ ደንቦች የሚገዛ ሲሆን ኢ-መደበኛው ግን በቀላልና ልል ስርዓት ይመራል። አስተዳደራዊ አመቺነትን ያማከለው ይህ አካሄድ በአንድ በኩል በዘፈቀደ በሚወሰድ እርምጃ ፍትሕ እንዳይጓደል በሌላ በኩል ደግሞ በጥብቅ ስነ ስርዓት ሳቢያ ውጤታማ አስተዳደር እንዳይሰናከል ህጉ የተከተለው አስታራቂ መስመር ነው።
በመደበኛው የአስተዳደር ዳኝነት ከክስ መሰማት (hearing) ጀምሮ አጠቃላይ ክርክሩ በመዝገብ (on the record) እንዲካሄድ የሚያስገድድ ሲሆን በይዘቱም ጠበቅ ያለ ስርዓት ነው። ይህ ስርዓት ተፈጻሚ የሚሆነው በልዩ ህግ በግልጽ ተደንግጎ ሲገኝ ብቻ ነው። የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህጉ የመደበኛውን የአስተዳደር ዳኝነት የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች በመደንገግ ተፈጻሚነቱን ግን ህግ አውጪው በዝርዝር ህግ በግልጽ በወሰናቸው ሁኔታዎች ላይ ብቻ ገድቦታል።n በዚህ መልኩ በመደበኛው የዳኝነት ሂደት የሚያልፉ የአስተዳደር ክርክሮች በቁጥር ከአምስት ፐርሰንት አይበልጥም።o የተቀሩት ኢ-መደበኛውን ስርዓት የሚከተሉ ናቸው። በሌላ አነጋገር መደበኛው አስተዳደራዊ ክርክር ተፈጻሚነቱ በልዩ ሁኔታዎች ብቻ ነው።
አሜሪካኖች ከሞላ ጎደል ሁሉም አስተዳደራዊ ክርክሮች ኢመደበኛ አካሄድ እንዲከተሉ የመረጡበት ምክንያት ንድፈ ሀሳባዊ ሳይሆን ተጨባጭና ተግባራዊ ነው። የአስተዳደር መ/ቤቶች እንደ መደበኛ ፍርድ ቤት ክስ እየሰሙ በማከራከር ውሳኔ የሚሰጡ ከሆነ የተቋቋሙለትን ዓላማ መቼም ቢሆን አያሳኩም። መደበኛ የአስተዳደር ክርክር ከሚፈጀው ጊዜ እንዲሁም ከሚያስፈልገው የሰው ሀይልና የገንዘብ ወጪ አንጻር በሁሉም አስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ ተፈጻሚ ቢደረግ ውጤታማ አስተዳደር ይቅርና ‘አስተዳደር’ የሚባል ነገር ራሱ አይኖርም።
በኢትዮጵያ በ1993 ዓ.ም. እና 2001 ዓ.ም. የተዘጋጁት ረቂቅ የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጆች ይህን መሰረታዊ ተጨባጭ እውነታ በቅጡ አልተረዱትም። ሁለቱም ረቂቆች አስተዳደራዊ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት መደበኛው የክስ መሰማት ስርዓት እንዲከናወን በአስተዳደር መ/ቤቶች ላይ ግዴታ ያስቀምጣሉ። ይሄ የገዘፈ ችግር በረቂቆቹ የተገታ ሳይሆን ህግ ሆኖ የፀደቀው የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግም የሚጋራው ችግር ነው።p ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በአሜሪካ በዚህ ዓይነት የክርክር ሂደት የሚያልፉ ጉዳዮች ከአምስት ፐርሰንት አይበልጡም። የተቀረው 95 ፐርሰንት ኢመደበኛ ነው። በረቂቅ ህጎቹ የተመረጠው አቅጣጫ ደግሞ ሁሉም (ማለትም 100 ፐርሰንት) አስተዳደራዊ ክርክሮች መደበኛ ስርዓት እንዲከተሉ ያስገድዳል። በዚህ ሁኔታ አስገዳጅ ህግ ሆነው በተወካዮች ም/ቤት ቢታወጁ ሊከተል የሚችለውን አስተዳደራዊ መንዛዛት ለመገመት ከወደሁ ያስቸግራል።
የመሰማት መብት እና ኢ-አድሎአዊነት መርህ ከአገራችን ህግ አንጻር
ህገ መንግስታዊ የመሰማት መብት?
የተፈጥሮ ፍትሕ በእንግሊዝና ሌሎች ኮመን ሎው አገራት በዳኞች የዳበረ የፍትሐዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርህ ነው። ይህ መርህ በህግ በግልጽ እንደ ቅድመ ሁኔታ ባይቀመጥም ዳኞች ተፈጻሚ እንዳያደርጉት አያግዳቸውም። በአሜሪካ እንዲሁ ህገ መንግስታዊ ዕውቅና ያገኘው ዱ ፕሮሰስ ኦፍ ሎው (Due Process of Law) በመባል የሚታወቀው ህገ መንግስታዊ መርህ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓትን የሚገዛ ልዩ ህግ ባይኖርም እንኳን ፍርድ ቤቶች እንደ አግባብነቱ ተፈጻሚ ያደርጉታል። ሆኖም በእነዚህ ሁለት አገራት ሆነ በሌሎችም ዘንድ አስተዳደር የሚመራበት ስነ ስርዓት ምንጩ በህግ አውጪው የሚወጣ ህግ ነው።
ግልጽ የህግ ድንጋጌ ካለ የስነ-ስርዓት ጉድለት ያለበት ውሳኔ በፍርድ ቤት ሊሻር ወይም ሊሰረዝ እንደሚገባው አያጠራጥርም። አስገዳጅ የህግ ድንጋጌ ከሌለስ? ፍርድ ቤቶቻችን እንደ እንግሊዝና አሜሪካ ፍርድ ቤቶች ፍትሐዊ የውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎችን ማዳበርና ተፈጻሚ ማድረግ አለባቸው? ካለባቸውስ አቋማቸው ህገ መንግስታዊ መሰረት አለው? በአስተዳደራዊ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት የመሰማት መብት እንዲሁም ኢ-አድሎአላዊነት መርህ በህግ በግልጽ ባልተደነገገበት ሁኔታ የስነ-ስርዓት ጉድለት ያለበት አስተዳደራዊ ውሳኔ ዕጣ ፋንታ መወሰን በብዙ መልኩ ከባድ ነው።
በአንድ በኩል ፍርድ ቤቶች የዜጎችን ፍትሕ የማግኘት መብት የማረጋገጥ ህገ መንግስታዊ ግዴታ ተጥሎባቸዋል። በሌላ በኩል ህጉን ከማንበብና ከመተርጎም ባለፈ ህግ መጻፍ ህገ መንግስታዊ ሚናቸው አይፈቅድላቸውም። በዚህ መልኩ የሚፈጠረው ‘ህገ መንግስታዊ አጣብቂኝ’ ብርታትና ጥንቃቄ ካልታከለበት በቀላሉ አይፈታም። በተጨማሪም ‘መርህ’ በተጨባጭ ‘መሬት ሲወርድ’ ከልዩ ሁኔዎች ጋር ሊጣጣምና የተፈጻሚነት ወሰኑ በአግባቡ ሊሰመር ይገባል። የመሰማት መብት የግድ የሚልበት ሁኔታ ቢኖርም ከተግባራዊ ፋይዳውና ውጤታማ አስተዳደር አንጻር የሚገደብባቸው ሁኔታዎች አሉ። በተጨማሪም የተፈፃሚነቱ ወሰን የግለሰብ መብት ወይም ጥቅም በሚነካ የዳኝነታዊ ባህርይ ባለው አስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ ብቻ ነው። ይህ የሚያሳየን አስቸጋሪው ስራ የፍትሐዊ ውሳኔ አሰጣጥ መርሆዎችን በጠቅላላው መቀበሉ ሳይሆን እንደ ጉዳዩ አይነት ልዩ ሁኔታዎችን ከግምት ባስገባ መልኩ የተፈጻሚነቱን አድማስ መለየቱ ላይ ነው።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 43511q በ2005 ዓ.ም. በሰጠው ፈር ቀዳጅ የህግ ትርጉም መሰረት አስገዳጅ የህግ ድንጋጌ ባይኖርም ከፊል የዳኝነት ስልጣን የተሰጠው አካል የመሰማት መብትን የማክበር ግዴታ አለበት። የችሎቱን አቋም በጥልቀት ለመረዳት በሐተታው ክፍል የሰፈረውን የሚከተለውን አስተያየት ማየቱ ተገቢ ነው።
…የመሰማት መብት በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ሊከበር የሚገባው መብት ነው። የመሰማት መብት ከመጀመሪያው ክርክር ጀምሮ እስከመጨረሻው የዳኝነት ሰጪ አካል መከበር ያለበት ስለመሆኑ በሕገ መንግስቱና ስለ ክርክር አመራር በተደነገጉት እንደፍትሐብሔር ስነ ስርአት አይነት ሕጎች ከተደነገጉት ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው።
የችሎቱ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ዜጎች ሀሳባቸው ሳይደመጥ መብትና ጥቅማቸውን የሚጎዳ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዳይሰጥባቸው ከለላ በማጎናጸፍ ረገድ ህገ መንግስታዊ ፋይዳው ‘ታሪካዊ’ ሊሰኝ የሚችል ነው። ከዚያም አልፎ ለአገራችን የአስተዳደር ህግ ዕድገት ችሎቱ ካደረጋቸው አስተዋጽኦዎች መካከል ቀዳሚውን ቦታ ይይዛል። በእርግጥ የውሳኔው ፋይዳ ብቻውን በቁሙ መለካት በተግባር ያስከተላቸውን ለውጦች በማጋነን ያስተቻል። የሰ/መ/ቁ. 43511 አስተዳደሩ አካሄዱን ከችሎቱ አቋም ጋር እንዲያስተካክል በዚህም የመሰማት መብትን የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ አካል አድርጎ እንዲያቅፍ የፈጠረው ጫና ሆነ በተግባር ያስከተለው ተጨባጭ ለውጥ የለም። አስገዳጁን የህግ ትርጉም መቀበልና መተግበር ያለባቸው የስር ፍርድ ቤቶችም ቢሆኑ በአስተዳደራዊ ክርክሮች የመሰማት መብትን በትጋት እንዲያስከብሩ የለውጥ ምንጭ አልሆነላቸውም። ምናልባትም ውሳኔው ስለመኖሩ ራሱ ገና አልሰሙ ይሆናል። የሰበር ውሳኔዎች የተደራሽነት ችግር እንዲሁም በውሳኔዎቹ ላይ ጠንካራ ምሁራዊ የሀሳብ ልውውጥ ባህል አለመዳበር በርካታ አስገዳጅ የህግ ትርጉሞች በቅጾች መጽሐፍ ውስጥ ተቀብረው እንዲረሱ ያደርጋቸዋል።
የሰ/መ/ቁ. 43511 ከህገ መንግስታዊ ፋይዳው ባሻገር ክርክሩ የተጓዘበት መስመር ትኩረት ይስባል። የክርክሩ መነሻ አመልካቾች ከአዋጅ ውጪ የተወረሰ ቤት እንዲመለስላቸው ለኢትዮጵያ ፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ያቀረቡት አቤቱታ ሲሆን ኤጀንሲውም ተጠሪ ምላሽ እንዲሰጡበት ካደረገ በኋላ ማስረጃና ክርክሩን ሰምቶ ቤቱ እንዲመለስላቸው ወስኗል። በውሳኔው ባለመስማማት ተጠሪ ለኤጀንሲው ቦርድ ይግባኝ በማቅረባቸው ቦርዱ የኤጀንሲውን ውሳኔ ሽሮታል። ከመሻሩ በፊት ግን አመልካቾችን ጠርቶ ክርክራቸውን አልሰማም።
በመቀጠል አመልካቾች የመሰማት መብታቸው አለመጠበቁን በመግለጽ በቀጥታ የሰበር አቤቱታ ለፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/ሰ/ችሎት ያቀረቡ ቢሆንም አጣሪ ችሎቱ የቦርዱን ውሳኔ የማረም ስልጣን እንዳልተሰጠው በመግለጽ ሳይቀበለው ቀርቷል። አመልካቾች ተስፋ ባለመቁረጥ ጉዳዩ ህገ መንግስታዊ ትርጉም እንደሚያስነሳ በመጠቆም ለህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ አመለከቱ። እዛም ተቀባይነት አጡ። አሁንም ሰሚ ፍለጋ ‘አቤት!’ ማለታቸውን ባለማቆም ጉዳያቸውን እንዲያይላቸው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይግባኝ አቀረቡ። በመጨረሻ ጥያቄያቸው ፍሬ አግኝቶ የአጣሪ ችሎቱ ውሳኔ ተሻረ።
አመልካቾች ተስፋ ባለመቁረጥ እስከ ፌዴሬሽን ም/ቤት ድረስ ዘልቀው ድል መጎናጸፋቸው በራሱ የተለየ ስሜት ቢያጭርም በተለየ መልኩ ትኩረት የሚስበው ግን የክርክሩ ሂደት ሳይሆን የም/ቤቱ ውሳኔ ይዘት ነው። የሰበር ችሎት የዳኝነት ስልጣንን በማስፋት አዲስ ህገ መንግስታዊ መልክ ያላበሰው ይኸው ውሳኔ የሰበር ችሎት የቦርዱን መሰረታዊ የህግ ስህተት የማረም ስልጣን እንዳለው አረጋግጧል። የም/ቤቱ ህገ መንግስታዊ ትርጓሜ መነሻ ያደረገው የኤጀንሲው ቦርድ ዳኝነታዊ ስልጣን ነው። ስለሆነም ቦርዱ የዳኝነት መሰል አካል (quasi judicial body) በመሆኑና ይህ አካል የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ በመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር ስልጣኑ ጉዳዩን የማየት ስልጣን አለው።
የስልጣን ጥያቄው እልባት ካገኘ በኋላ መዝገቡ ከፌዴሬሽን ም/ቤት ወደ ሰበር ችሎት ሲመለስ የቦርዱ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት መሰረታዊ ጭብጥ ሆኖ ተነስቷል። ጭብጡን ለመፍታት ችሎቱ የቦርዱን የማቋቋያ አዋጅr የተመለከተ ቢሆንም በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ቦርዱ የተከራካሪዎችን የመሰማት መብት እንዲጠብቅ የሚያስገድድ ድንጋጌ አላገኘም።
በአስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ የመሰማት መብት የሚጠብቅ ህግ በሌለበት ሁኔታ ውሳኔው ሰጭው አካል በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት መብቱን እንዲያከብር ግዴታ መጫን ለችሎቱ ፈታኝ ስራ እንደሆነ አያጠያይቅም። ምክንያቱም ከህግ የመነጨ ግዴታ በሌለበት ቦርዱ የመሰማት መብት መርሆዎችን እንዲከተል ማስገደድ በውጤቱ የችሎቱን ተግባር ከህግ መተርጎም ወደ ‘ህግ መጻፍ’ ያሸጋግረዋል። ስለሆነም ችሎቱ በስልጣን ክፍፍል መርህ የተሰመረውን ድንበር ሳይሻገር በራሱ የዳኝነት ስልጣን ዛቢያ ውስጥ ሆኖ ውሳኔውን በአሳማኝ ምክንያት ማስደገፍ አለበት። ከዚህ አንጻር ለአቋሙ መሰረት ያደረገውን ምክንያት ማየቱ ጠቃሚ ነው። በዚህ ነጥብ ላይ ዋናው የሀተታ ክፍል እንደሚከተለው ይነበባል።
ቦርዱ ከፊል ውሳኔ ሰጪ አካል እንደመሆኑ መጠን የሚሰጠው ውሳኔ የሕጉን ስርዓት ተከትሎ ሊሰጥ ይገባል። ከፊል የዳኝነት ስልጣን የተሰጠው አካል በሕጉ ተለይቶ የተቀመጠለት የክርክር አመራርና አሰጣጥ ስርዓት እስከሌለ ድረስ በኢ.ፌ.ዲ. ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት የተጠበቁትን ፍትህ የማግኘት፣ የመሰማትና በእኩል ሚዛን የመታየት መብት ሊያከብር ይገባል። በውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ሊጠበቁ ከሚገባቸው ሕገ መንግስታዊ መብቶች አንዱ ደግሞ ክርክር የማቅረብና ማሰረጃ የማሰማት መብት ነው። ይህ የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት የግድ ከሚላቸው የስነ ስርዓት አካሄዶች አንዱ ነው። ክርክሩን በአግባቡ እንዲያቀርብ እድል ያላገኘ ሰው በኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀፅ 37 የተከበረለት ፍትህ የማግኘት መብቱ ውጤታማ ሊሆን አይችልም።
ህጉን በፍሬ ነገሩ ላይ ተፈጻሚ በማድረግ አሳሪ ውሳኔ የሚያስተላልፍ አካል ተግባሩ ዳኞች በችሎት ተቀምጠው ከሚያከናውኑት የዳኝነት ተግባር አይለይም። ስለሆነም የዳኞችን ዓይነት የፍትሐ ብሔር ስነ-ስርዓት መከተል ባይኖርበትም ቢያንስ ቢያንስ አንደኛውን ወገን ብቻ ሰምቶ መወሰን የለበትም። ችሎቱ ይህን መሰረታዊ የአስተዳደር ህግ መርህ በአግባቡ ተረድቶታል። ‘ታሪካዊ’ መባሉም ለዚህ ነው። ምክንያቱም ይሄን የመሰለ ይቅርና የሚቀራረብ ውሳኔ ከችሎቱ መንጭቶ አያውቅም።
ቀደም ብለው የተሰጡ ተመሳሳይ ውሳኔዎች ባይኖሩም ከአንድ ዓመት በኋላ በታየ መዝገብ የመሰማት መብት ህገ መንግስታዊ ዕወቅና አግኝቷል። በሰ/መ/ቁ. 92546s በዲሲፕሊን ጉዳይ የተከሰሰ ዓቃቤ ህግ በዓቃቤ ህግ አስተዳደር ዋና ጉባዔ ውሳኔ መከላከል ሳያስፈልገው ከክሱ ነጻ ከተደረገ በኋላ በድሮው አጠራር የፍትሕ ሚኒስትር (በአሁኑ ጠቅላይ ዓቃቤ) ዴኤታ ፊርማ መከላከያውን ሳያሰማ በመሰናበቱ የሚኒስትሩን እርምጃ በመቃወም በቀጥታ ለሰበር ችሎት ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት አግኝቷል። ችሎቱ በውሳኔው ሚኒስትሩ ከህግ የመነጨ ከፊል የዳኝነት ሰልጣን እንዳለው በመጠቆም የማሰናበት እርምጃው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት ጥበቃና ዋስትና የተሰጠውን የእኩልነትና ፍትሕ የማግኘት መብት እንደሚጻረር በመጠቆም ሽሮታል።
በህግ የተቀመጠ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት
በአገራችን ወጥ የአስተዳደር ህግ ባይኖርም የአስተዳደር መ/ቤቶች በግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ እርምጃ የሚወስዱት ሁልጊዜ በዘፈቀደ አይደለም። ይብዛም ይነስም በተለያዩ ዝርዝር ህጎች ላይ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች ተደንግገዋል። ጠቅለል ተደርጎ ሲታይ ከክስ መሰማት ጀምሮ እስከ መጨረሻው ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ድረስ የአስተዳደር መ/ቤቶች የሚከተሉት ስነ ስርዓት በዚህም ፍትሐዊነት የሚገለጽበት መንገድ ደረጃው ይለያያል። በአንዳንዶቹ ጠበቅ ያለና መደበኛነት የሚታይበት ሲሆን በሌሎቹ ደግሞ ቀላል እና ‘ልል’ ተብሎ ሊገለጽ የሚችል ነው።
ከሞላ ጎደል ሁሉንም የመሰማት መብት እና የኢአድሎአዊነት መርሆዎች ያሟላ በዓይነቱ በአሜሪካው የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ ላይ ‘መደበኛ’ ተብሎ የተገለጸውን የአስተዳደር ዳኝነት የሚመስል የክርክር ስርዓት የሚገኘው የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁ. 847/2006 ላይ ነው። ስርዓቱ የተዘረጋው ህግን በመተላለፍ ጥፋት በሚፈጽም ኦዲተር ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ነው። ከክስ አመሰራረት እስከ ውሳኔ አሰጣጥ ድረስ የክርክሩ አመራር ስርዓት በአዋጁ ከአንቀጽ 38-43 ባሉት ድንጋጌዎች የሚመራ ሲሆን ሂደቱ አጠር ተደርጎ ሲጠቃለል የሚከተለውን ይመስላል።
አዋጁ የኢ-አድሎአዊነት መርህን ለማረጋገጥ የሚና መደበላለቅን አስቀርቷል። የመርማሪነት፣ ከሳሽነት እና ውሳኔ ሰጭነት ሚናዎች በኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ሰራተኛ/ተሿሚ ተለይተው ተከፋፍለዋል። በዚሁ መሰረት ‘መርማሪ ሹም’ የሚባል የቦርዱ ተቀጣሪ ሠራተኛ ወይም ከቦርዱ ጋር የቅጥር ግንኙነት ያልመሰረተ ብቃት ያለው ባለሞያ የምርመራ ተግባር ያከናውናል። መርማሪ ሹሙ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ሲያምንበት ክስ እንዲመሰረት ለቦርዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ የውሳኔ ሀሳብ ከማቅረብ ውጪ በራሱ ክስ አያቀርብም። በአዋጁ የከሳሽነት ሚና የተሰጠው ለስራ አስፈፃሚው ነው። ስራ አስፈፃሚው ክስ ለመመስረት ከወሰነ በምርመራ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ ያልነበሩ ከመካከላቸው አንዱ የህግ ባለሞያ የሆነ ሶስት የቦርዱን ሰራተኞች በክስ ሰሚነት ይሰይማል። እነዚህ ክስ ሰሚዎች (hearing examiners) ክርክሩን ሰምተው የመጨረሻ ውሳኔ የማስተላፍ ስልጣን አላቸው።
የዲሲፕሊን ክስ የቀረበበት ሰው ስለቀረበበት ክስ ይዘት የማወቅ እና በራሱ ወይም በጠበቃው አማካኝነት ቀርቦ ማስረጃውን የማቅረብ፣ ምስክሮቹን በመጥራት ቀጥተኛ ጥያቄ መጠየቅና እና ለከሳሽ ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ መብቱ በአዋጁ አንቀጽ 39/2/ ተጠብቆለታል። በግራ ቀኙ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች በተጨማሪ ክስ ሰሚዎች ለጉዳዩ አወሳሰን ጠቃሚ ማስረጃ ይዞ የሚገኝ ማንኛውም ሰው በመጥሪያ በመጥራት በቃለ መሀላ የማረጋገጫ ቃሉን መቀበልና አግባብነት ያላቸውን ሰነዶችና ማስረጃዎች እንዲያቀርብ የማስገደድ ሰፊ ዳኝነታዊ ስልጣን ተጎናጽፈዋል። ክስ ሰሚዎች በክርክሩ ሂደት የቀረቡትን ማስረጃዎችና ክርክሩን ከመረመሩ በኋላ ክስ የቀረበበት ተከሳሽ አዋጁንና በአዋጁ መሰረት የወጣን ደንብና መመሪያ መተላለፍ አለመተላፉን ይወስናሉ። የህግ መተላለፍ ከተፈጸመ ማስጠንቀቂያ ከመስጠት ጀምሮ እስከ ፈቃድ መሰረዝ ብሎም እስከ ብር 25,000 (ሃያ አምስት ሺ ብር) የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እና ሌሎች በአዋጁ ላይ የተዘረዘሩ አስተዳደራዊ ቅጣቶችን ማስተላለፍ ይችላሉ።
ከሞላ ጎደል ተቀራራቢ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በሚወስዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች ላይ ተፈጻሚ ይደረጋል። በሲቪል አቪዬሽን አዋጅ ቁ. 616/2001 አንቀጽ 80/1/ ላይ እንደተደነገገው ባለስልጣኑ አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ሊወስደው ስላሰበው እርምጃ ለሚመለከተው ሰው ማሳወቅና እርምጃው ሊወሰድ አይገባም የሚልበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ዕድል መስጠት አለበት። ማስታወቂያው ጥፋት መፈጸሙን የሚገልጽ ክስ ሳይሆን በምርመራ ግኝት ባለስልጣኑ ድምዳሜ ላይ ከደረሰ በኋላ ድምዳሜውን ለማስተባበል የሚደረግ ጥሪ ነው። ስለሆነም በምርመራ ሂደት ባለስልጣኑ የሚሰማቸውን ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ ዕድል አይኖርም። ሆኖም ቀጣይ የአዋጁ አንቀጽ 80/4/ ድንጋጌ በጠበቃ ወይም ባለጉዳዩ በራሱ ክርክር የማሰማት መብትን የሚፈቅድ እንደመሆኑ ማስረጃ የማቅረብና ምስክር ማሰማት የስነ ስርዓቱ አካል አድርጎ መቁጠር ይቻላል። በተጨማሪም የባለስልጣኑ ሠራተኛ የግል ጥቅሙን በሚነካ ጉዳይ በምርመራ ሂደት እንዳይሳተፍ ገደብ የሚጥለው የአዋጁ አንቀጽ 80/3/ በከፊልም ቢሆን ከአድልኦ የፀዳ ውሳኔ እንዲሰጥ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ህግን በማስከበር ስልጣናቸው በቀጥታ ከሚያስተላልፏቸው ውሳኔዎችና ከሚወስዷቸው እርምጃዎች በተጨማሪ በአማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴ ዳኝነታዊ ተግባራት ሲያከናውኑ ጠበቅ ያለ ስርዓት ይከተላሉ። በኢትዮጵያ የውሀ ሀብት አስተዳደር አዋጅ ቁ. 197/1992 የማዕከል ውሀ ሀብት አስተዳደርን አስመልክቶ የቁጥጥር ተግባራት እንዲያከናውን ስልጣን የተሰጠው ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የውሀ ግልጋሎት ፈቃድ የተሰጣቸው ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ከፈቃዱ ጋር የተያያዙ መብትና ግዴታዎችን አስመልክቶ በመካከላቸው የሚነሱ ክርክሮችን እንዲሁም በባለ ፈቃድ እና በሌላ ሶስተኛ ወገኖች መካከል የሚፈጠሩ ማናቸውንም ክርክሮች ሰምቶ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። አዋጁ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት በውክልና በሰጠው የህግ አውጭነት ስልጣን መሰረት ክርክሮቹ የሚመሩበት ስርዓት በደንብ ቁ. 115/1997t ተደንግጓል።
በተቆጣጣሪው ባለስልጣን ዘንድ በሚካሄደው የክርክር አመራር ስርዓት ላይ መደበኛው የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት ህግ ተፈጻሚነት አለው። በደንቡ ላይ ተለይተው የተቀመጡት ጥቂት የስነ-ስርዓት ድንጋጌዎችም ቢሆኑ ጠበቅ ያሉ ናቸው። በዚህ የተነሳ በተቆጣጣሪው አካል የሚካሄደው ክርክር በይዘቱ ፍርድ ቤቶች ከሚከተሉት የሙግት ስርዓት ጋር ይቀራረባል።
ክርክሩ የሚጀመረው አቤት ባዩ በሚያቀርበው ማመልከቻ ነው። ማመልከቻው የክርክሩን ፍሬ ሀሳብ (በእንግሊዝኛው ቅጂ memorandum summarizing the dispute) እና ማስረጃ እንዲሁም የአቤት ባዩን ቅሬታ እና እንዲሰጥለት የሚፈልገውን ውሳኔ አካቶ መያዝ ይኖርበታል። ስለሆነም በይዘቱ ከመደበኛው የክስ አቤቱታ ብዙም አይለይም። ተቆጣጣሪው አካል ማመልከቻውን እንደተቀበለ ክርክሩ የሚሰማበትን ቦታና ጊዜ የሚገልጽ መጥሪያና የማመልከቻ ቅጂ ለተከሳሹ እንዲደርሰው ያደርጋል። በቀጠሮ ቀን ባለጉዳዮች በቀጠሮ ሰዓትና ቦታ ተገኝተው ጉዳያቸውን ያስረዳሉ። ማስረጃም ያቀርባሉ። በሁለቱም ወገኖች የሚቀርቡ ማስረጃዎች በተቆጣጣሪው አካል ይመዘገባሉ። ተከሰሹ መጥሪያ ደርሶት ካልቀረበ ጉዳዩ በሌለበት ይሰማል። ተቆጣጣሪው ጉዳዩን ሰምቶ የሚሰጠውን ውሳኔ ባለጉዳዮች እንዲያውቁት ማድርግ ያለበት ሲሆን በተጨማሪም የውሳኔውን መዝገብ ግልባጭ የመስጠት ግዴታ አለበት። በደንቡ ላይ ለውሳኔ ምክንያት መስጠት እንደ ቅድመ ሁኔታ አልተቀመጠም። ይሁን እንጂ ተቆጣጣሪው እንደ አግባብነቱ የፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህጉን ተፈጻሚ የማድረግ ግዴታ ያለበት እንደመሆኑ ምክንያት የጎደለው ውሳኔ በፍርድ ቤት መሻሩ አይቀርለትም።
ከላይ ያየነው ዓይነት ከመደበኛ ፍርድ ቤት ጋር የሚቀራረብ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት አፈጻጸሙ በውስን አስተዳደራዊ ክርክሮች ላይ ብቻ ነው። በጣም በርካታ መ/ቤቶች ለስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች የሚገዙት በጣም በስሱ ነው። አብዛኛው ቀዳሚ ውሳኔ /initial decision/ በአስተዳደራዊ የሙግት ሂደት ስር አያልፍም። ውሳኔ አሰጣጡ በባህርዩ መርማሪ ሲሆን ጉዳዩ የሚመለከተውን አካል አያሳትፍም። ህግ መጣሱ የሚረጋገጠው መ/ቤቱ በሚቀርብለት ጥቆማ ወይም በራሱ አነሳሽነት በሚያካሂደው ምርመራና ማጣራት አማካይነት ነው። በዚህ መልኩ ጥፋት መፈጸሙ አስቀድሞ አቋም ይያዝበታል። ሆኖም መ/ቤቱ የደረሰበት ድምዳሜ አስገዳጅነት ወዳለው የመጨረሻ ውሳኔ ከመሸጋገሩ በፊት የሚመለከተው አካል አስተያየት ወይም ምላሽ እንዲሰጥበት ይደረጋል። መልስ ሰጭው የቀረበበትን ማስረጃ የማስተባበል አሊያም ተቃራኒ ማስረጃ የማቅረብ በህግ የተጠበቀ መብት የለውም።
ልል እና ኢ-መደበኛ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ከሚደነግጉ ህጎች መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በመድን ሰጪ ድርጅት ያካሄደው ምርመራ የመጨረሻ ሪፖርት ከመዘጋጀቱ በፊት ለተመርማሪው መድን ሰጪ ድርጅት እንዲደርሰው ተደርጎ በሪፖርቱ ላይ አስተያየቱን እንዲያቀርብ ዕድል ይሰጠዋል።u
/ንግድና ኢንዱስትሪ/ ሚኒስቴሩ ወይም የእርሱ ተወካይ የአንድ ባለዕቃ ማከማቻ ቤት የግብርና ምርት ውጤቶች ተቆጣጣሪ፣ መዳቢ፣ ደረጃ ሰጪ፣ መዛኝ ወይም ናሙና አውጭ የሥራ ፈቃድ ለዘለቄታው እንዲሰረዝ ከመወሰኑ በፊት አጥፍቷል የተባለው ጥፋት በጽሑፍ እንዲገለጽለትና በቂ ጊዜ ተሰጥቶት በጉዳዩ ላይ ምላሽ እንዲሰጥበት ወይም መቃወሚያ እንዲያቀርብበት ዕድል ሊሰጠው ይገባል።v
የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ በማንኛውም ድርጅት ላይ የትኛውንም ዓይነት አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ድርጅቱ መከራከሪያዎቹንና ማስረጃዎቹን የማቅረብና የመሰማት መብት አለው።w
የጉምሩክ ኮሚሽን ማንኛውም ዕቃ ወይም ማጓጓዣ በዚህ አንቀጽ መሠረት ውርስ ሆኖ ለመንግሥት ገቢ ከመደረጉ በፊት የዕቃው ወይም የማጓጓዣው ባለቤት በአዋጁ አንቀጽ 143(3) ወይም (4) መሠረት የመያዝ እርምጃውን አንዲያውቀው ከተደረገበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ ተቃውሞውን እንዲያቀርብ ዕድል መስጠት አለበት፡፡x
በተጨማሪም ኮሚሽኑ በኤሌክትሮኒክስ መረጃ ልውውጥ ሥርዓት የመጠቀም መብትን ከማገዱ ወይም ምዝገባውን ከመሠረዙ በፊት እርምጃው የሚወሰድበትን ምክንያት ለተጠቃሚው በጽሑፍ በማሳወቅ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ አስተያየቱን እንዲያቀርብ ዕድል መስጠት አለበት፡፡y
የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አንድን ፈቃድ ከማገዱ ወይም ከመሠረዙ በፊት እርምጃውን የሚወስድበትን ምክንያት ለባለፈቃዱ በጽሑፍ በመግለጽ ባለፈቃዱ ጽሁ በደረሰው በሰባት ቀናት ውስጥ የበኩሉን አስተያየት በጽሑፍ እንዲሰጥ ያደርጋል፡z
የመሰማት መብት በህግ ቢፈቀድም በጥቅል አነጋገር በሚገለጽበት ጊዜ የመብቱን ወሰን አፈጻጸም አስቸጋሪ ያደርገዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የክፍያ መፈጸሚያ ተቋምን ወይም የግብይት ፈጻሚዎችን ወይም የማህበራቸውን ዕውቅና ከማገዱ ወይም ከመሰረዙ በፊት መጀመሪያ የተቋሙ ኃላፊዎች በማስታወቂያ እንዲያውቁት ማድረግና ለባለጉዳዩ የመሰማት ዕድል መስጠት ይኖርበታል፡a የድንጋጌው አነጋገር የጠቅላላነት ባህርይ ቢታይበትም የመሰማት መብት መሰረታዊ የአስተዳደር ፍትሕ ጥያቄ እንደመሆኑ ዕውቅና ከመታገዱ ወይም ከመሰረዙ በፊት ቅድመ ክስ ማስታወቂያ፣ ማስረጃ የማቅረብ መብትና ተቃራኒ ማስረጃ የማስተባበል መብት ተሟልተው ሊገኙ ይገባል።
በአንዳንድ ህጎች ላይ ደግሞ የመሰማት መብት ውሳኔውን በማሳወቅ ላይ ብቻ ይገደባል። በእርግጥ ውሳኔው አግባብ እንዳልሆነ በቃል ሆነ በጽሑፍ ማስተባበል ካልተቻለ የመሰማት መብት መነፈጉን እንጂ በከፊል መገደቡን አይደለም የሚያሳየው። የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴሩ የዕፅዋት አዳቃዮችን መብት ለመሰረዝ ውሳኔ ላይ ከደረሰ ለመሰረዝ የበቃበትን ምክንያት በመግለጽ ለባለመብቱ የጽሑፍ ማስታወቂያ መስጠትና መብቱ የተሰረዘ መሆኑን ለሕዝብ ማስታወቅ አለበት።b ማስታወቂያው የመሰረዝ ውሳኔውን ከማሳወቅ የዘለለ ውጤት የለውም። ባለመብቱ የእርምጃውን ህጋዊነት ለመቃወም የሚችልበት ቀዳዳ የለም።
አንዳንድ ጊዜ የመሰማት መብት የሚፈቀደው ከውሳኔ በኋላ ይሆናል። የዘር አስመጪ፣ ላኪ፣ የዘር አምራች፣ አዘጋጅ፣ ጅምላ ሻጭ፣ አከፋፋይ ወይም ቸርቻሪ በዘር አዋጅ ቁ. 782/2005 አንቀጽ 21/1/ እና /2/ መሰረት የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀቱ በእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር ወይም በክልል ባለስልጣን ከመታገዱ ወይም ከመሰረዙ በፊት በድንጋጌው ላይ የተጠቀሱት በቂ ምክንያቶች እውነት ስላለመሆናቸው ለማስረዳትና ተቃራኒ ማስረጃ ለማቅረብ ዕድል አልተሰጠውም። ሆኖም ከውሳኔው በኋላ ውሳኔውን ለሰጠው አካል አስተዳደራዊ ቅሬታ የማቅረብ መብቱ በአንቀጽ 25/1/ ተጠብቆለታል። አመልካቹ በተሰጠው ምላሽ ካልረካ ቅሬታውን ለሚመለከታው የፍትሕ አካል ሊያቀርብ እንደሚችል በድንጋጌው ንዑስ አንቀጽ 2 ተመልክቷል።
የመሰማት መብት በዝምታ የታለፈባቸው ድንጋጌዎች
ምክንያቱ ባይታወቅም በዜጎች መብት ላይ ቀጥተኛ እና አሉታዊ ውጤት የሚያስከትሉ አንዳንድ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ሳይዘረጋላቸው በዝምታ ታልፈዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ስራ ፈቃድ የተሰጠው ኩባንያ አሰራሩ ለአደጋ ያልተጋለጠ፣ አስተማማኝና ጤናማ መሆኑን ለማረጋገጥ የኩባንያውን ዳይሬክተር፣ ዳይሬክተሮች ወይም ዋና ስራ አስፈፃሚ ከስራ ማገድ ወይም ማሰናበት ይችላል።c ባንኩ በምን ዓይነት ሁኔታዎችና በቂ ምክንያቶች እርምጃውን እንደሚወስድ ስልጣን በሰጠው አዋጅ ቁ. 807/2005 ላይ አልተመለከተም። በተጨማሪም እርምጃው የሚወሰድባቸው የኩባንያው ኃላፊዎች የተከሰሱበትን ጉዳይ ባንኩ ፊት ቀርበው ለማስረዳትና ማስተባበያ ማስረጃ ለማቅረብ በአጠቃላይ የመሰማት መብታቸው በአዋጁ አልተጠበቀም።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን በማስታወቂያ አዋጅ ቁ. 759/2004 አንቀጽ 31/3/ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር የውጭ ማስታወቂያን ሳይጨምር የአዋጁን ድንጋጌ በመተላለፍ የተሰራጨን ማንኛውንም ማስታወቂያ ይመረምራል፣ ያግዳል፣ የአፀፋ ማስታወቂያ እንዲወጣ ያዛል። ነገር ግን እርምጃውን ከመውሰዱ በፊት የማስታወቂያውን ባለቤት የመስማት ግዴታ አልተጣለበትም። በእርግጥ ለእርምጃው ምክንያት የሆኑት አብዛኛዎቹ ጉዳዮች ህሊናዊ ፍርድ የሚጠይቁ እንደመሆኑ ማስረጃ-ነክ ክርክሮች አይኖሩም። ሆኖም በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ተቃራኒውን ወገን መስማት የተዛባ አመለካከትን በማጥራት ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል። በተጨማሪም ባለስልጣኑ የማስታወቂያ ባለቤቶችን እይታ በጥልቀት ይረዳል። ለምሳሌ በአዋጁ ክልከላ ከተደረገባቸው ህግን ወይም መልካም ስነ ምግባር እንደሚጻረሩ የሚቆጠሩ ማስታወቂያዎች መካከል በአንቀጽ 7/6/ እና /8/ የሚከተሉት ተጠቅሰዋል፡
የህብረተሰቡን አካላዊና አእምሯዊ ጤንነትና ደህንነት ለጉዳት የሚያጋልጥ ድርጊት እንዲፈጸም የሚያነሳሳ ማስታወቂያ
ለመልካም ፀባይ ተቃራኒ የሆነ የጽሑፍ መልዕክት፣ ምስል፣ ስዕላዊ መግለጫ፣ ፊልም ወይም መሰል አቀራረብን የያዘ ማስታወቂያ
የአንድን ማስታወቂያ ይዘት በተጠቀሱት የተከለከሉ ተግባራት ስር ለመፈረጅ ጥንቃቄ የተሞላበት ህሊናዊ ፍርድ ይጠይቃል። በእንዲህ ዓይነቱ የውሳኔ አሰጣጥ ውጫዊ ሁኔታዎች ለምሳሌ የውሳኔ ሰጭው ግላዊ፣ ባህላዊና ስነልቡናዊ አቋም ይብዛም ይነስም ተጽዕኖ ያሳድራሉ። ስለሆነም ከአድልኦ የፀዳና ያልተዛባ ውሳኔ ለመስጠት የተቃራኒው ወገን አመለካከትና እይታ ማዳመጥ ወደጎን ሊተው አይገባም።
የአስተዳደር ውሳኔ አሰጣጥ በአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ
የአሜሪካው የአስተዳደር ስነ ስርዓት ህግ አስተዳደራዊ ክርክር /adjudication/ መደበኛ ወይም ኢመደበኛ በሚል የተከፈለ ሲሆን መደበኛው ስርዓት በጣም ውስን በሆነ ጉዳዮች ላይ የተገደበና ተፈጻሚነቱም ህግ አውጭው ባመለከታቸው ሁኔታዎች ላይ ብቻ ነው።d በጀርመን እንዲሁ አስተዳደራዊ ክርክሮች መደበኛ እና ኢ-መደበኛ በሚል የሚከፈሉ ሲሆን መደበኛው ተፈጻሚ የሚሆነው ህግ አውጭው በግልጽ ካመለከተ ብቻ ነው።e በየትም አገር ቢሆን በቁጥር ከፍተኛውን ቦታ የሚይዘው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ኢ-መደበኛውን ስርዓት ይከተላል። በአሜሪካ 90 ፐርሰንት የሚሆኑት አስተዳደራዊ ጉዳዮች ውሳኔ የሚያገኙት በኢ-መደበኛ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ነው። በእንግሊዝ በዳኞች የዳበረው የመሰማት መብትንና የኢ-አድሎአዊነት መርህ አካቶ የያዘው የተፈጥሮ ህግ መሰረታዊ መርህ በሁሉም ውሳኔ ሰጭ አካላት ላይ ወጥ ተፈጻሚነት የለውም። በህግ ያልተቀመጠ የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታ ባለመሆኑም ዳኞች እንደየሁኔታው እያጠበቡና እያሰፉ በትርጉም በአስተዳደር ውስጥ ኢመደበኛነት እንዲሰፍን አድርገዋል። ወጥነት የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ መገለጫ ባህርይ ስላለመሆኑና መደበኛው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት የኢ-መደበኛው ልዩ ሁኔታ እንደሆነ እንዲሁም ህግ አውጭው የአስተዳደር ውሳኔዎችን እንደ ዓይነታቸው፤ ውስብስብነታቸው፤ በመብት እና ጥቅም ላይ የሚያስከትሉት ክብደት እና ሌሎች ተገቢ መመዘኛዎችን በመለየት ከልል እስከ ጥብቅ የትኛውን ስነ-ስር ዓት መከተል እንዳለባቸው ሊወስን እንደሚገባ በዚህ መጽሐፍ (ክፍል 5.3 ልዩ ሁኔታዎችና የተፈጻሚነት ወሰን) በስፋት የተብራራ በመሆኑ መድገሙ አስፈላጊ አይሆንም። እዚህ ላይ የሚዳሰሰው አዲስ የወጣው የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ የኢ-መደበኛነትን ፅንሰ-ሀሳብ በምን መልኩ እንዲሁም እስከምን ደረጃ የህጉ አካል እንዳደረገው ይሆናል።
የአገራችን የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ ለሁሉም ተቋማት በሁሉም ሁኔታዎች ተፈጻሚ የሚሆን ወጥ እና መደበኛ ስርዓት ዘርግቷል። እንዲህ ዓይነቱ አካሄድ የአስተዳደር ተቋማት ሊሸከሙት ከሚችሉት በላይ ጫና መደረብ ነው።
ለመሆኑ መደበኛ ሲባል ምን ለማለት ነው? አንባቢ ግልጽ መረዳት ይኖረው ዘንድ በሚከተሉት ህጎች ላይ ያሉትን መደበኛ የሚባሉ የክርክር ሂደቶች ቀንጨብ አድርገን እናያለን።
የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁጥር 847/2006 ከአንቀጽ 38 እስከ 42
የፌደራል መንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ ስርዓት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 77/1994
የዓቃብያነ ህግ የዲሲፕሊን ክስ አቀራረብ፣ ማጣራትና ውሳኔ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት በተመለከተ የፌደራል የዓቃብያነ ህግ መተዳደሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁ 443/2011 ከአንቀጽ 91 እስከ 94 ድረስ የተዘረጋው ስርዓት
መደበኛው የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት በመደበኛ ፍርድ ቤት የሚካሄደው ሙግት አምሳያ ነው። ጉዳዩን ሰምቶ አከራክሮ ፍርድ መስጠት ለፍርድ ቤቶች መደበኛ ስራቸው ነው። ስለሆነም እያንዳንዱ የክርክር ሂደት በዝርዝር በተጻፈ የስነ-ስርዓት ድንጋጌዎች ይመራል። ድንጋጌዎቹ ልዩነት ሳይደረግ በሁሉም ተከራካሪዎች ላይ ተፈጻሚነት አላቸው።
ሆኖም ለአንድ የአስተዳደር ተቋም ማከራከር ተጉዳኝ እንጂ ዋና ተግባሩ አይደለም። ተቋሙ የተቋቋመበት የራሱ የሆነ ዓላማና ተግባር አለው። ተልዕኮው ይህን ዓላማ በብቃት እና ውጤታማ በሆነ መንገድ ማሳካት ነው። ተቋሙ በህግ የተሰጠውን ተግባር ሲያከናውን በግለሰቦች መብትና ጥቅም ላይ አሉታዊ ውጤት ሊያስከትል የሚችል አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ይገደዳል። እንደ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሁሉ የተቋሙ ውሳኔ በማስረጃ የተደገፈ እና ህጉን መሰረት ያደረገ እና ፍትሐዊ ሊሆን ይገባል። ይህ በተግባር የሚረጋገጠው እርምጃ የሚወሰድበት ግለሰብ ወይም ድርጅት ጥፋተኛ እንዳልሆነና ተጠያቂነት እንደሌለበት በማስረጃ አስደግፎ ማስረዳት ሲችል ነው። በአግባቡ ማስረዳት ይችል ዘንድ ፍሬነገሩና ህጉ የሚጣራበት ይብዛም ይነስም የተወሰነ የክርክር ስርዓት መወሰን ያስፈልጋል። ስርዓቱ መደበኛ ከሆነ ፍርድ ቤት የሚከተለውን ስነ-ስርዓት ይመስላል። ይመስላል እንጂ ግን ግልባጭ አይደለም። የአስተዳደር ተቋም በውሳኔ አሰጣጥ ረገድ መደበኛውን የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት የሚከተል ከሆነ ሙሉ ጊዜና ሀብቱን የሚያጠፋው የተቋቋመበትን ዓላማ በማሳካት ሳይሆን በማከራከከር ብቻ ይሆናል። ከዚህ አንጻር መደበኛ በሚባል የአስተዳደር ክርክር ላይ ተፈጻሚነት የሚሆኑት የስነ-ስርዓት ቅደመ ሁኔታዎች ውስንና በይዘታቸውም ጠቅላላነት የሚስተዋልባቸው ናቸው።
በተቃራኒው ሂደቱ ኢ-መደበኛ ከሆነ በጣም ልል ከመሆኑ የተነሳ የክርክር ስርዓት ብሎ ለመጥራት እንኳን ይከብዳል። በዛ ላይ በይዘቱ እና በአፈጻጸሙ ከተቋም ተቋም ከውሳኔ ውሳኔ ሊለያይ ይችላል። ይህን በምሳሌ ለማስረዳት ያክል የግብርና ሚኒስቴር የሰጠውን የዕፅዋት አዳቃይ መብት ለመሠረዝ ሲወስን፦
•ሀ) ለባለመብቱ መብቱ ሊሰረዝ እንደሆነ በጽሑፍ ያሳውቃል፤
•ለ) ባለመብቱ ተቃውሞ ካለው የጽሑፍ ማስታወቂያ እንደደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ማስረጃ እንዲያቀርብ በጽሑፍ ያሳውቃል፤ እና
•ሐ) ተቃውሞ ቀርቦ ከሆነ ክርክሩን ሰምቶ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል
ይህንን እላይ ካየናቸው መደበኛ የክርክር ስርዓት ጋር ስናስተያየው ሚናቸው የተለያየ መርማሪና ከሳሽ እንዲሁም ጥፋትን የሚያስታውቅ የክስ አቤቱታ የለም። ባለመብቱ መብቱ ሊሰረዝ እንደሆነ ሚኒስቴር መ/ቤቱ የራሱን ማጣራት አድርጎ ህጉን አመሳክሮ አስቀድሞ ድምዳሜ ላይ ደርሷል። ለዚህም ነው የመከላከያ መልሱን ሳይሆን ማስረጃውን እንዲያቀርብ የተጠየቀው። ሚኒስቴሩ ውሳኔ የሚሰጠው ክርክሩን ሰምቶ ቢሆንም ተከራካሪ ወገኖች (ከሳሽና ተከሳሽ) የሉም። ስለሆነም ክርክሩን ሰምቶ ሲባል ባለመብቱ የሚያቀርበውን ተቃውሞ ሰምቶ ለማለት ነው። በሚኒስቴሩ ፊት ማስረጃ ከማቅረብና ተቃውሞ ከማሰማት የዘለለ የክርክር ስርዓት የለም።
በመደበኛው የፍርድ ቤት ክርክር ከክስ መሰማት በፊት የተለያዩ ጉዳዮችን የሚወስኑ በርካታ የስነ ስርዓት ድንጋጌዎች አሉ። በፍርድ ቤት ክርክር ተፈጻሚ የሚሆኑት የስነ ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች በባህርያቸው የማያወላዱ ግትር እንደመሆናቸው ለአስተዳደር ክርክር አይመቹም። በአንድ አገር ውስጥ የሚወጣ የአስተዳደር ህግ ውጤታማ አስተዳደርን ሳያሰናክል የዜጎችን መሰረታዊ የመሰማት መብት የሚያስጠብቅ ተለማጭ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት ይኖርበታል። ከዚህ አንጻር አዋጁ ሁለት ጉልህ ግድፈቶች ይታዩበታል። በአንድ በኩል የመሰማት መብትን ከክስ መሰማት ጋር አምታቶታል። በዚህ የተነሳ መሰረታዊ የሚባሉትን የመሰማት መብት ድንጋጌዎችን አልያዘም። በሌላ በኩል ተፈጻሚ የሚሆነውን ስርዓት እንደ ጉዳዮች ዓይነት /ማለትም እንደ አስተዳደራዊ ውሳኔው ዓይነት/ መደበኛ እና ኢመደበኛ ስነ ስርዓት መዘርጋት ቢኖርበትም አንድ ወጥ ቅድመ ሁኔታ በመደንገግ ሁሉንም በአንድ ሙቀጫ ወቅጧቸዋል። ይህ ደግሞ በቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥ እና ውጤታማ አስተዳደር ላይ የሚያስከትለው ግዙፍ ተደራራቢ ችግር በቀላሉ የሚገመት አይሆንም።
በአዋጁ የሚታዩ የውሳኔ አሰጣጥ አጀማመር ብዥታዎች
በመጀመሪያ ደረጃ ውሳኔ /initial decision/ ሆነ በቅሬታ ስርዓት /review decision/ የአስተዳደራዊ ክርክር የሚጀመረው ከማስታወቂያ ነው። በመጀመሪያው ውሳኔ ሰጭው ባለስልጣን ለባለጉዳዩ /ለተከሳሹ/ የክስ ማስታወቂያ ይሰጠዋል። በሁለተኛው ደግሞ የባለጉዳዩ የቅሬታ አቤቱታ ለውሳኔ ሰጭው አካል ይደርሰዋል። የክስ ሆነ የቅሬታ አቤቱታ ለሚመለከተው ወገን እንዲደርስ ግልጽ የሆነ የማስታወቂያ አሰጣጥ ስርዓት ሊኖር ይገባል። በዚህ መጽሀፍ በክፍል 5.3 እንደተመለከተው ማስታወቂያ ተከራካሪው እንዲቀርብ የሚሰጥ መጥሪያ ነው። በይዘቱ ባለጉዳዩ የቀረበበትን ክስ በሚገባ ተረድቶ መልሱን አዘጋጅቶ እንዲያቀርብ የሚያስችለው ሊሆን ይገባል።
የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጁ ከክስ መሰማት በፊት ያሉ ወሳኝ ሂደቶችን በዝምታ አልፏቸዋል። ሙሉ ትኩረቱን ያደረገው ባለጉዳዩ የአስተዳደር ጉዳይ በሚሰማበት ጊዜ በክርክ ሂደት ሁሉ ተገኝቶ ስለሚከናወነው የአስተዳደር ክርክር ብቻ ነው። በዚህ የተነሳ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓቱን ጎዶሎ አድርጎታል።
የቅድመ ክስ ማስታወቂያ ስርዓትን አስፈላጊነት በተመለከተ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአንድ ውሳኔ ላይ እንዳለው
The right to a hearing embraces not only the right to present evidence, but also a reasonable opportunity to know the claims of the opposing party and to meet them. The right to submit argument implies that opportunity; otherwise the right may be but a barren one.f
የፌደራል መንግስት ሰራተኞች የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነ ስርዓት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 77/1994 በአንቀጽ 11 ላይ ክስን ስለማሳወቅ ከአዋጁ በጣም በተሻለ የሚከተሉትን ድንጋጌዎች ይዟል።
1. የዲስፕሊን ኮሚቴ ክስ የቀረበበት ሠራተኛ መልሱን ይዞ እንዲቀርብ የክሱን ጽሁፍና ማስረጃዎች ቅጅ አያይዞ የክስ ማስታወቂያ ይልክለታል።
2. የክስ ማስታወቂያው ክሱ የሚሰማበትን ቦታ፣ ቀንና ሠዓት የሚገልጽ ሆኖ ክሱ ከሚሰማበት ቀን ቢያንስ ከ 10 ቀናት በፊት ለተከሣሹ መድረስ አለበት።
3. ሠራተኛው ሊገኝ ባለመቻሉ ወይም ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆኑ የክስ ማስታወቂያውን ለመስጠት ያልተቻለ አንደሆነ በመሥሪያ ቤቱ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ተለጥፎ ለ15 ቀናት እንዲቆይ ይደረጋል።
የአዋጁ ችግር የክስ ማስታወቂያን የሚደነግግ ነጠላ ድንጋጌ አለመያዙ ብቻ አይደለም። በአጠቃላይ ከክስ መሰማት በፊት በዝርዝር መካተት የነበረባቸው የአስተዳደር ክርክር መሰረታዊ ድንጋጌዎች በሙሉ ተረስተዋል። የውሳኔ አሰጣጥ አጀማመር በተመለከተ አዋጁ ብዥታ ይነበብበታል። የውሳኔ አሰጣጥ አጀማመር በተመለከተ የሚስተዋለው መሰረታዊ ችግር መንስዔም ይኸው ነው።

ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ስለሚኖረው ውጤት


ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ስለሚኖረው ውጤት

አንቀጽ ፵፱ መከባበር መተጋገዝና መደጋገፍ

 

፩. ባልና ሚስት እርስ በርሳቸው መከባበር፣ መተጋገዝና መደጋገፍ አለባቸው፡፡

፪. በጋብቻው ውል ውስጥ ይህንን የሚቃረን ስምምነት ማድረግ አይችሉም፡፡

 

አንቀጽ ፶ የቤተሰብ የጋራ አመራር (፩) ጠቅላላ

 

፩. በቤተሰብ አመራር ረገድ ባልና ሚስት እኩል መብት አላቸው፡፡

፪. ባልና ሚስቱ በማናቸውም ረገድ የቤተሰቡን ደህንነትና ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ለልጆቻቸው በመልካም ሥነምግባር እንዲታነፁ፣ ተገቢ ትምህርት እንዲቀስሙና ኃላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ሆነው እንዲያድጉ ለማድረግ መተባበር አለባቸው፡፡

 

አንቀጽ ፶፩ (፪) ከተጋቢዎቹ አንዱ ቤተሰቡን ለመምራት ስላለመቻሉ

 

፩. ከባልና ሚስት አንደኛው ችሎታ ያጣ፣ የጠፋ ወይም ቤተሰቡን ጥሎ የሔደ ወይም ከመኖሪያ ሥፍራው በመራቁም ሆነ በማናቸውም ሌላ ምክንያት ፈቃዱን ለመስጠት በማይችልበት ሁኔታ በሚገኝበት ጊዜ፣ በአንቀጽ ፶ የተመለከተውን የቤተሰብ አመራር አንደኛው ተጋቢ ብቻውን ይፈጽማል፡፡

፪. ባልና ሚስት በጋብቻ ውላቸው ውስጥ ይህንን የሚቃረን ስምምነት ማድረግ አይችሉም፡፡

 

አንቀጽ ፶፪ ከጋብቻ በፊት ከሌላ ስለተወለዱ ልጆች

 

፩. ከባልና ከሚስቱ አንዱ ከጋብቻው በፊት ከሌላ የወለዳቸውን ልጆች መልካም አስተዳደግ በሚመለከት በራሱ አሳብና መሪነት የፈቀደውን ውሳኔ ለማድረግ ሙሉ መብት ይኖረዋል፡፡

፪. ይህንን የሚቃረን ማናቸውም ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡

 

አንቀጽ ፶፫ አብሮ መኖር

 

፩. ባልና ሚስት አብረው እንዲኖሩ ይገደዳሉ፡፡

፪. ለጤናቸው አደገኛ ካልሆነ በስተቀር ባልና ሚስት ከጋብቻ የሚጠበቀውን መደበኛውን የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸም አለባቸው፡፡

፫. ይህንን የሚቃረን ማናቸውም ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡

 

አንቀጽ ፶፬ የመኖሪያ ሥፍራን ስለመወሰን

 

ባልና ሚስት የሚኖሩበትን ሥፍራ በጋራ ይወስናሉ፡፡

 

አንቀጽ ፶፭ በስምምነት ተለያይቶ ስለመኖር

 

፩. በዚህ ሕግ በአንቀጽ ፶፫ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተመለከተው ቢኖርም ባልና ሚስቱ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተለያይተው ለመኖር መስማማት ይችላሉ፡፡

፪. ስለዚህ ጉዳይ የተደነገገውን ስምምነት መለወጡ የማይገባ ካልሆነ በስተቀር ከሁለቱ ተጋቢዎች አንደኛው አስቦ ሊሰርዘው ይችላል፡፡

 

አንቀጽ ፶፮ የመተማመን ግዴታ

 

ባል ለሚስቱ፣ ሚስት ለባልዋ ታማኝ የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡

 

በክብር መዝገብ ሹም ፊት ስለሚፈጸም ጋብቻ


በክብር መዝገብ ሹም ፊት ስለሚፈፀም ጋብቻ

 

አንቀጽ ፳፪ ሥልጣን ያለው የክብር መዝገብ ሹም

 

ጋብቻ ከተጋቢዎቹ አንዱ ወይም ከተጋቢዎቹ ወላጆች ወይም የቅርብ ዘመዶች አንዱ ጋብቻው ከሚፈጸምበት ጊዜ በፊት ቢያንስ ለስድስት ወራት ያህል ሳያቋርጥ በሚኖርበት ቦታ በሚገኘው የክብር መዝገብ ሹም ፊት ይፈጸማል፡፡

 

አንቀጽ ፳፫ ጋብቻ ለመፈፀም ጥያቄ ስለማቅረብ እና ስለሚቀርብበት ጊዜ

 

ተጋቢዎች ጋብቻ ለመፈፀም ማሰባቸውን እጅግ ቢዘገይ ጋብቻቸውን ለመፈፀም ከወሰኑበት ቀን ከአንድ ወር በፊት ለክብር መዝገቡ ሹሙ ማስታወቅ አለባቸው፡፡

 

አንቀጽ ፳፬ ጋብቻ የሚፈፀምበትን ቀን ስለመወሰንና ስለማስታወቅ

 

የክብር መዝገብ ሹሙ ጥያቄው እንደቀረበለት ከተጋቢዎቹ ጋር በመነጋገር ከወሰነ በኋላ ጋብቻው የሚፈፀምበትን ቀን በመግለጽ አመቺ በሆነው መንገድ ማስታወቂያ ያወጣል፡፡

 

አንቀጽ ፳፭ የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓት እና ጋብቻው መፈፀሙን ስለማስታወቅ

 

፩. ጋብቻው ሁለቱ ተጋቢዎች እና ከእያንዳንዱ ተጋቢ በኩል ሁለት ሁለት ምስክሮች በተገኙበት በግልጽ ይፈፀማል፡፡

፪. ተጋቢዎችና ምስክሮቹ ጋብቻ ለመፈፀም አስፈላጊ የሆኑት ሁኔታዎች አለመጣሳቸውን በቃለ መሐላ ያረጋግጣሉ፡፡

፫. ተጋቢዎችና ምስክሮቹ የመሐላ ቃል ከመስጠታቸው በፊት የሚሰጡት ቃል ስለሚያስከትለው ኃላፊነት የክብር መዝገብ ሹሙ በግልጽ ማስረዳት አለበት፡፡

፬. ሁለቱም ተጋቢዎች ጋብቻ ለመፈፀም መፍቀዳቸውን ለክብር መዝገብ ሹሙ በግልጽ ያረጋግጣሉ፡፡

፭. ሁለቱም ተጋቢዎችና ምስክሮቻቸው በክብር መዝገብ ላይ መፈረም አለባቸው፡፡

፮. ከዚህ በላይ የተገለጹት ሥርዓቶች የተፈፀሙ መሆናቸውን ሲያረጋግጥ የክብር መዝገብ ሹሙ ተጋቢዎቹ በሕጋዊ ጋብቻ የተሳሰሩ መሆናቸውን አስታውቆ ለተጋቢዎቹ የጋብቻ የምስክር ወረቀት ይሰጣቸዋል፡፡